ከሰሞኑ የፖለቲካችን የስበት ማእከል ታሪክ እና የታሪክ ባለሙያዎች ሆነዋል። ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ የተባሉ የታሪክ ምሁር ከኢሳት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ በሶሻል ሚዲያው ከፍተኛ አዋራ ማስነሳቱ ሳያንስ፣ የተዳፈኑ የመሰሉ ጉዳዮችንም በመቀስቀስ ላይ ይገኛል። በመጀመሪያ የዶክተሩን ቃለምልልስ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በጽሞና ለመከታተል ሞክሬአለሁ። በዚህም ተጠያቂውን ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ከሙያም ሆነ ስነምግባር አንጻር የበቃ ችሎታቸውን ለመታዘብ ችያለሁ። ውዝግቡ ከተቀሰቀሰም በኋላ የኦሮሞ አክቲቪስት ነን ከሚሉ ሰዎች በተሰነዘረውን ክስ ላይ ተመስርቼ ቃለ-ምልልሱን በሂሳዊ አይን ለማየት ሞክሬአሁ። ህዝብ የተሰደበበት እና ወደ አንድ ሚዛን ያጋደለ አቀራረብ ፈልጌ ማግኘት ተቸግሬአለሁ። እንዳውም ዶ/ር ሃይሌ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አወዛጋቢ ቦታ ስለሚይዘው ግራኝ አህመድ በጎ የሆነ እይታ … [Read more...] about ታሪክን ምርኮኛ የማድረግ ዘመቻ
Opinions
የኔ ሃሳብ
ፕ/ር ኃይሌ ላሬቦ እና “የቁቤው ትውልድ” ፖለቲካ
ለሰሞኑ ግርግር መንስኤ የሆኑት ፕ/ር ኃይሌ የተጠቀሟቸው ሁለት ቃላት ናቸው ተብሏል። "ጋላ" እና "እረኛ" የሚሉ ቃላት። በኢትዮጵያ የታሪክ መዛግብት ውስጥ እነዚህ ቃላት "ሰፍረዋል" ወይንስ "አልሰፈሩም" የሚለውን ጉዳይ ለግዜው እንተወው። ፕሮፌሰር ኃይሌ ላሬቦ በቃለ-መጠይቁ እነዚህን ቃላት መጠቀማቸው "ስህተት ነው" ወይንም "ስህተት አይደለም" ወደሚለው ትንታኔም አልገባም። እነዚህን ጥያቄዎች ለታሪክ ለተመራማሪዎቹ ልተውላቸው። ፕሮፌሰሩ ከወንድማገኝ ጎሹ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ እነዚያን ቃላት ባይጠቀሙስ፣ ከስድብ እና ከአድማው ይድኑ ይሆን? የሚለው ጥያቄ ግን ትንሽ ወደ ኋላ እንድዞር አድርጎኛል። "ዳግማዊ ምኒልክና ታሪካዊ ክንውኖቻቸው" በሚል ርዕስ አንጋፋው ጋዜጠኛ ተክሌ የኋላ ከሁለት አመት በፊት ሦስት እንግዶችን በጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ጋብዞ አወያይቷቸው ነበር። … [Read more...] about ፕ/ር ኃይሌ ላሬቦ እና “የቁቤው ትውልድ” ፖለቲካ
ጻዕረ ሞትና መስፍን ወልደ ማርያም
አንደኛ፣ ገና በልጅነቴ አሥር ዓመት ግድም ሲሆነኝ አንድ በድቀድቂት ከእንጦጦ ወደታች የሚወርድ ኢጣልያዊና እኔ ተጋጠምን፤ እሱ በዚያ በጥቁር ድንጋይ ኮረት በረበረበበት መንገድ ላይ ሲጓዝ ወደ እንጦጦ የሚወጣ ወታደሮችን የጫነ ከባድ መኪና ቆሞ ነበር፤ በዚያ መኪና ላይ አንድ ዝንጀሮ ነበር፤ የኔ አትኩሮት በዚህ ዝንጀሮ ላይ ነበር! እንደሚመስለኝ ዝንጀሮውን እያየሁ ስሮጥ ከድቅድቂቱ ጋር ተገናኘን፤ እኔ ከስር በተረበረበው የጥቁር ድንጋይ ኮረት ላይ፣ ድቅድቂቱ ደግሞ የእኔን ራስ ጨፍልቆ! ምኒልክ ሀኪም ቤት ከስንት ቀኖች በኋላ የካቶሊክ መነኮሳት አስታማሚዎች ከነመለዮአቸው አልጋዬ አጠገብ ቆመው በትልቅ የበሽተኞች ድንኳን ውስጥ በአንዱ መደዳ ውስጥ ተኝቼ ነቃሁ፤ መድኃኔ ዓለም ማንን ልኮ የእኔን ጭንቅላት ከድንጋዩና ከድቅድቂቱ መክቶ እንዳዳነኝ አላውቅም፡፡ ሁለተኛ ከሶደሬ መውጫ ላይ በመቶ … [Read more...] about ጻዕረ ሞትና መስፍን ወልደ ማርያም
“ኮከብ ባየሁ ቁጥር እበረግጋለሁ” ዘ-ሃበሻ እግዜር ይይልሽ!
ከሶቅራጥስ ዘመን ጀምሮ ሲነገር የኖረውን “እውቀት እና መረጃ ሃይል መሆኑን” መንገር፣ እንዲሁም “...መረጃን መገደብ... የአምባገነኖች እና ህዝብን የሚበዘብዙ እና የሚጨቁኑ ...” ገዢዎች ስራ መሆኑን መጻፍም፣ አንባቢህን አለማወቅ/መናቅ ቢሆንም፣ ክፋት የለውም። “...መረጃዎች እንዳይወጡ ማድረግ የጨቋኞች ባህሪ ነው....”፣ በሚል መንደርደሪያ ተነስቶ፣ ከ“ጨቋኞች” የተጻፈ መሆኑን ለማሳየት/ለማጋለጥ አንድም ሃርግ መዘው ሳያወጡ እና ሳይተቹ፣ ባለፈው የለቀቅሁትን ጽሁፍ “የጨቋኞች ጽሁፍ ... የመንደርተኛ ወሬ ነው...” ማለት አግባብ አይደለም። ጽሁፉ፣ ሙያዊ ግምገማ/ትችት እንኳን ባይመስላቸው “ከጨቋኞች የመጣ ነው” ማለቱ ራሱ፣ የዘሃበሻን ኢዲቶሪያል ቦርድ ትዝብት ላይ ይጥላል። በመሰረቱ ከ“ጨቋኝ” ጋር እየታገልን ነው ማለታቸውም ነው። የዘሃበሻ “ኢዲቶሪያል ቦርድ”፣ ጋዜጠኝነት … [Read more...] about “ኮከብ ባየሁ ቁጥር እበረግጋለሁ” ዘ-ሃበሻ እግዜር ይይልሽ!
“የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!
ለረጅም አመታተ የጣልኩትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው እንድመዝ አስገደደኝ - በ ኢትዮ-ሚዲያ (Ethiomedia) እና በጎልጉል (Googlgule) ድህረ-ገፆች ላይ ከወራት በፊት በዶክተር ፍቃዱ በቀለ በተባሉ ግለሰብ በ"የተቆለፈበት ቁልፍ" መፅሐፉ ላይ የቀረበ አንድ ፅሑፍ። "ሃያሲው" በዘመናችን አቻ ያላገኙለት (ወደር የሌለው) መፅሐፉ መሆኑን ነው የገለፁልን። "...የስነ-ጽሁፍም ዋና ዓላማው በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉትን አስቀያሚም ሆነ ቆንጆ ነገሮች ስዕላዊ በሆነ መልክ መግለጽ ሲችሉና አንባቢውን በልዩ ሃሳብ ውስጥ ተመስጦ እንዲዋኝ ማድረግ ሲችሉ ብቻ ነው።..." በማለት ካብራሩ በኃላ ከ`ዚህ አንፃር "የተቆለፈበት ቁልፍ" እንደተዋጣለት መሰክርነታችውን ይሰጣሉ። አንዲህ ሲሉ "....በታሪካችን ውስጥ በመጀመሪያ ጊዜ በልዩ አቀራረብ የተዘጋጀና የተጻፈ ትምህርታዊ መጽሀፍ ነው … [Read more...] about “የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!
የኢትዮጵያ ወዳጅ ጆን ቤጀንት ዜና-ዕረፍት፣ የሃዘን መግለጫ
የኢትዮጵያ ወዳጅና የአፍሪካ ቀንድ አጋሮች [Partners in the Horn of Africa] የካናዳ ተራድኦ ድርጅት መስራች፤ በካናዳ የብሔራዊ መብቶችና ነፃነት ዋስትና ቻርተር በብሔራዊ ምክር ቤት እንዲፀድቅ አስተዋፅዖ ከተሳተፉት ጠበቃዎች አንዱ የነበረው ካናዳዊዩ ዮሐንስ ቤጄንት [John Baigent] ባደረባቸው ህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ቤተሰባቸው፣ Partners in the Horn of Africaና በመላው ኢትዮጵያና ካናዳ የሚገኙ ወዳጆቻቸው ከፍተኛ ሃዘን ተሰምቷቸዋል። ጠበቃ John Baigent ከአስራ ስድስት ዓመታት በፊት የመሰረቱት የግብረሰናይ ድርጅት በኢትዮጵያ በርካታ ሥራዎችን ሰርተዋል። የአፍሪካ ቀንድ አጋሮች ግብረሰናይ ድርጅትን ከሌሎች የዕርዳታ ድርጅቶች የተለየ የሚያደርገው ሁለት ዋና ዋና ቁም ነገሮች ይገኙበታል። እነርሱም:- 100% … [Read more...] about የኢትዮጵያ ወዳጅ ጆን ቤጀንት ዜና-ዕረፍት፣ የሃዘን መግለጫ
በነገራችን ላይ “ውይይቱ” የት ደረሰ?
የሙስናውን የመረጃ እጦት ኩምክና ሰምተን ስቀን ሳንጨርስ ሰሞኑን ደግሞ የውይይት ፉገራ አመጡ። ልክ እንደቀበሌ ስብሰባ ተቃዋሚዎችን በአዳራሽ ውስጥ አጉረው ሲያበቁ እነሱ ከመድረክ ሆነው ይቀልዱባቸዋል። የNBC ውን፤ የዴቭድ ሌተርማን ‘ሌት ናይት ሾው” (late night show) የሚመስል ነገር በቴሌቭዥን ለቀውብን ነበር። ሁለቱ ባለስልጣኖች፤ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ እና አቶ አስመላሽ ወልደሥላሴ መድረክ ላይ ጉብ በለዋል። በአነስተኛና በጥቃቅን የተደራጁ 21 የፓርቲ መሪዎች ደግሞ እንደ ቲያትር ተመልካች አዳራሹ ውስጥ ተሰይመዋል። እነዚያ ከላይ፣ እነዚህ ከታች ተቀምጠዋል። እነዚያ ይናገራሉ፣ እነዚህ ደግሞ ይሰማሉ።… ሌላ ምን አማራጭ ሊኖራቸው? ውይይት ብለውታል። ሌላው አይደለም። አቀማመጣቸው ብቻ የውይይቱን አቅም እና ያይል ያሳብቃል። በሙስናው የመረጃ እጦትት ኩምክና ስቀን ሳናበቃ … [Read more...] about በነገራችን ላይ “ውይይቱ” የት ደረሰ?
EALING AMNESTY GROUP DEMANDS THE RELEASE OF ESKINDER NEGA
The Ealing Amnesty Group has recently declared that it has adopted Eskinder Nega as a focus for campaigning in 2017. This must be highly appreciated by the freedom and peace-loving citizens of the world. We hope other Groups also adopt other journalists, such as Journalist Temesgen Desalegn, whose health is currently seriously damaged in captivity in Zeway Prison. On 27 Friday 2017, Ealing Amnesty Group held a successful vigil in front of 17th Princess Gate, London, from where the diplomatic … [Read more...] about EALING AMNESTY GROUP DEMANDS THE RELEASE OF ESKINDER NEGA
80ኛ የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀን መታሰቢያ
የካቲት 12 ቀን 1929 አ/ም በአዲስአበባ 30,000 ኢትዮጵያውያን በግፍ ተገድለዋል በኢትዮጵያ የሚፈለገው ፍትህ ቫቲካን ፋሽስት ኢጣልያን ደግፋ ስለነበር የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ የተባበሩት መንግሥታትድርጅት በኢትዮጵያ ላይ የደረሰውን ግፍ እንዲመዘግብ የኢጣልያ መንግስት ለኢትዮጵያ ተገቢውን ካሣ እንዲከፍል በቫቲካንና በኢጣልያ መንግሥት የተዘረፉ ንብረቶች ለኢትዮጵያ እንዲመለሱ በኢጣልያ በአፊሌ የተሠራው የጦር ወንጀለኛው የግራዚያኒ መታሰቢያ እንዲወገድ 80th Feb 19 Martyrs memorial Let us remember our Ethiopian martyrs massacred by Italian Fascists and demand justice Italian Fascists massacred over one million Ethiopians … [Read more...] about 80ኛ የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀን መታሰቢያ
ፎረም 65፦ ዕርቀ ሰላም በኢትዮጵያ
ዕርቅ ምንድን ነው? በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በዕርቀ ሰላም ላይ የሚመክርና የመፍትሔ ሃሳብ የሚያመነጭ ውይይት አድርጓል። ፎረም 65 በጉባኤው ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ተወያይቷል። ያድምጡት! * ለመጪው ትውልድ መግባባትን እናውርስ። * Dhaloota Dhufuuf Wal-ta'insa, Haa Dhaalchifnuu. * ንመፃኢ ወለዶ ምርድዳእ ነውርስ። ፎረም 65 (info@65percent.org) … [Read more...] about ፎረም 65፦ ዕርቀ ሰላም በኢትዮጵያ










