ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ዘረኛው የትግሬ ወያኔ አገዛዝ በሕዝባችን ላይ፣ በተለይም በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጽመው የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በ«አርበኞች ግንቦት 7» እያመካኘ ነው። ለዚህም ምክንያት የሆነው አርበኞች ግንቦት ሰባት፣ በሚቆጣጠረው የብዙኃን መገናኛ ያላደረገውን አደረኩ፣ ያላዘመተውን ወታደር አዘመትኩ፣ «የክተት አዋጁ ፊሽካ ተነፋ»፣ በሁሉም ሕዝባዊ እንቢተኝነት እንቅስቃሴዎች እኔ አለሁበት፣ የምመራው እኔ ነኝ፣ የሚለው ወሬ ቀድሞ መነዛቱ ነው። ወሬው በትንሽ ተግባር ቢደገፍ ኖሮ ባልከፋ። ክፋቱ ምንም ዓይነት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሳይጀምር፣ ኤርትራ በረሃ ከትሟል የሚባለው ፋኖ፣ የተከዜን ወንዝ ሳይሻገር፣ የወያኔ አገዛዝ አንገሽግሾት ባመቸውና በመሰለው መንገድ ጥይት የተኮሰውን ሁሉ የእኔ ነው ማለቱ፣ «ለወያኔ ሊበሏት ያሰቧትን … [Read more...] about ለማንነታችን መከታ ያልሆነን፣ ለመጠቃታችን ምክንያት እየሆነ ነው!
Opinions
የኔ ሃሳብ
ሚዲያ አለኝ ተብሎ የሰው ስብዕና ላይ ክተት አይታወጅም
ሚዲያ እንደ ሰዎች አረዳድ የሚሰጠው ደረጃና አቅም የተለያየ ቢሆንም ያለ አንዳች ማመንታት “ኃይል” ወይም ኃይል ያላቸው መገልገያ መሆኑ ጥርጥር የለውም። ሁሉም ሚዲያ “የሕዝብ” መሆናቸውን ቢገልጹም ፍጹም ነጻና ገለልተኛ ሆነው አይታዩም። ወደ አገራችን ሚዲያ ስንመጣ በውጭ ያሉትም ሆኑ በአገር ቤት፣ የግል የሚባሉትም ሆነ የመንግሥት የራሳቸው ወገንተኛነትና መንሸዋረር ይታይባቸዋል። ይህ እውነት ባደጉት አገሮችም ቢሆን ረቀቅ ባለ መልኩ የሚዘወተር ነው። ከሁሉም የሚቀፈው ግን ፍጹም ጭፍንነት ነው። ምክንያቱም በጭፍንነት ውስጥ አንድ ሰው ከተነገረውና ከተሞላው በቀር አሻግሮ ማየት አይችልምና ነው። “መቃብር ቆፋሪው እና የሬሳ ሳጥን ሻጩ የሚለው ተውኔት የተሰረቀ ነው” የማለት አዝማሚያ በሚስተዋልበት ስሜት የተጀመረ ቃለ ምልልስ። ሲጠናቀቅም የተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ትገባለህ “የባከንክ ነህ” … [Read more...] about ሚዲያ አለኝ ተብሎ የሰው ስብዕና ላይ ክተት አይታወጅም
“እውነተኛው የዘር ምንጭ?”
ዶ/ር ፍቅሬ በ “የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” መጽሐፉ አዲስ እሳት ለኵሶልናል። እሳቱ ባጭሩ፣ ሁሉም የሚስማማውን ታሪክ ይጻፍ የሚል ነው። ቍጥራቸውና ማንነታቸው ያልታወቀ አወዳሾቹ፣ “ሐቀኛ የኦሮሞ ልጅ የኢትዮጵያ ልጅ” “የመከራ ቀን ደራሽ” “የመከራ ቀን ልጅ” “የታሪክና የፍቅር አባት” “የኢትዮጵያ መድን” “የህዝብ እርቅ አባት” “አስታራቂ” “የኢትዮጵያ ቤዛ” “ነብይ” ብለውታል። ሙገሳው የለመደበት “ካብ ካብ፣ ጣል ጣል” ባህላችን ነው ብለን እንለፈው። አንዳንድ “ምሑራን” ጭሱ አፍኗቸው መስኮት ለመክፈት ይሯሯጣሉ። አንዳንዶች የጎሳ ክልል መደብዘዝ የሥልጣን ወንበር እንዳያሳጣቸው ሠግተው። ሌሎች በአገር ወዳድነት። አንዳንዶችም ያልተፈጠረ ንጹሕ ጎሳ በስውር የሚያውጁ ናቸው። ከኢትዮጵያ መንደር ውጭ ማሰብ የተሳናቸው፤ በምድር ዙሪያ የሕዝቦች አሠፋፈር፣ መፍለስና … [Read more...] about “እውነተኛው የዘር ምንጭ?”
የሕወሓትን “ሌጋሲ” በጨረፍታ
የወያኔው መንግሥት ያላወረሰን ነገር የለም፡፡ ሁለመናችንን እከክ በእከክ አድርጎናል - በቀላሉ በማይድን እከክ አውርሶን ወያኔም እኛም ጣር ላይ እንገኛለን - አሸናፊው ባልለየለት እልህ አስጨራሽ የአውራ ዶሮዎች ጦርነት ተጠምደን፡፡ የመለስና የድርጅቱ የሕወሓት ውርስ (ሌጋሲ) በአሥራዎች ቀርቶ በመቶዎች ዓመታትም ተዝቆ የማያልቅ ዕዳ አሸክሞናል፡፡ በኢኮኖሚውና በትምህርቱ ረገድ የደረሰብን ኪሣራ ምናልባት በጊዜ ሂደትና ደጋግ ዜጎች የአስተዳደሩን ልጓም ሲይዙ ሊስተካከል ይችላል፡፡ ይህም ሲባል ሚሊዮኖችን በእሳት አለንጋው እየገረፈ የሚገኘው ድህነት ጥርሱን አግጥጦና ዐይኑን አፍጥጦ ዜጎችን የበይ ተመልካች በማድረግ ከማንኛውም ጨዋታ ውጪ እያደረጋቸው እንደሆነና በትምህርቱም በኩል በዘልማድ ከኢትዮጵያ ሕዝብ 85 በመቶው እንደሆነ ከሚነገርለት የሀገራችን ገበሬ በዕውቀት የማይሻሉ ምሩቅ ማይማን … [Read more...] about የሕወሓትን “ሌጋሲ” በጨረፍታ
STANDING TOGETHER AS ONE
This past year of 2016 may have been the worst year in recent history for Ethiopians within the country. Many families will be facing Christmas or the New Year without the presence of a beloved family member at their side. The reasons have been many and most point to the actions or lack of actions taken by the TPLF/EPRDF. Too many have been taken from this earth early due to the deadly violence perpetrated against them by TPLF/EPRDF security forces. The ruling regime used deadly force against … [Read more...] about STANDING TOGETHER AS ONE
Ethiopia: The Peril of Complacency in our Community
Hilary Clinton’s historical defeat is no doubt one for the history books, and it is going to be minced and diced for a while. No body, not even Trump and his supporters, saw it coming. Trump, despite his braggadocio, might even have agonized in his mind to himself, “I didn’t mean to win, I swear to God! Why is it happening to me?” For those who are fond of the outcome, it is a miracle that can be compared to hitting the jackpot at the Taj Mahal Casino that Trump himself once owned; and for those … [Read more...] about Ethiopia: The Peril of Complacency in our Community
ዘ-ሃበሻ! እባክሽ “ሙድ” አትያዢብን!
አንድ ሰው በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን በሚናገራቸው/በሚጽፋቸው ጽሁፎች አስተሳሰቡ እና ብቃቱ ይገመታል፤ የሚመራውን ድርጅት/ተቋም ብቃትም ይናገራል። እንደ ግለ-ሰብ ስለ ራስ፣ ስለ ቤተሰብ እና ስለ ጓደኛ የሚናገራቸው ወይም የሚጽፋቸው ጽሁፎች ከሙያዊ ብቃት እና ችሎታ አኳያ ብዙም የሚያስከትለው ተጽዕኖ አይኖርም። ጋዜጠኛ ነኝ ያለ ሁሉ ጋዜጠኛ እንዳልሆነ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የጋዜጣ አዘጋጅ ስትሆን፣ ከዚያም ብዙ ተከታዩች ሲኖሩህ እና ስለ አገር እና የማህበራዊ ጉዳይ የምትጽፋቸው ሲሆን ግን ቢያንስ ከጋዜጠኛነት ሙያ፣ ከጭብጥም ሆነ ከቋንቋ አጠቃቀም አኳያ ይሄን ያህል መወረድ በ“ሙደኞች” (“ሙድ” የዘ-ሃበሻ የራሷ አማርኛ ነው) ቋንቋ ሙያዊ “ቅሽምና” ነው። ስለዚህ እኛም ዘ-ሃበሻን በ“ሙድ” ልንተች ነው። “ወያኔ በየቀኑ ህዝባችንን እየገደለና እያሰረ ሙድ ሲይዝብን...” እንዳለችው … [Read more...] about ዘ-ሃበሻ! እባክሽ “ሙድ” አትያዢብን!
የዶ/ር መረራ መታሰር ሰላማዊው ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል የተደረገ ጥሪ ነው!!!!
መረራ ጉዲና ገና ከለጋ ወጣትነት ህይወቱ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ባልተቋረጠ ወኔና ጥራት ለአንዲት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ሲታገል የኖረ ዜጋ ነው፡፡ በዚህ ያልተቋረጠ ተጋድሎው በንገሱ ዘመን አምቦ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሆኖ በተማሪው ንቅናቄ በነበረው ንቁ ተሳትፎ ለአጭር ጊዜም ቢሆን እስር ቤት ተወርውሯል፡፡ በደርጉ ዘመን ደግሞ በመኢሶን ታጋይነቱ ለሰባት አመታት በእስር ተንገላቷል፡፡ ለአለፉት 25 አመታት ደግሞ የወያኔ ኢህአዴግን ግፈኛ አገዛዝ በመቃወም በሰላማዊና ህጋዊ የትግል ስልት ተሰማርቶ ከነዚህ የጥፋት ሃይሎች አንጻር እነሱ ከፋፍለህ ግዛን ሲያራመዱ የህዝቦች ወንድማማችነትን እየሰበከ፣ እነሱ ለስልጣናቸው ሲሉ በለየለት የአፋኝና የአመጽ ጎዳና ሲሰማሩ ዴሞክራሲን፣ ሰላምንና ህጋዊነትን እያነገበ ሲሞግታቸውና ሲታገላቸው በህዝባችን ፊት ተአማኒነትንና ተወዳጅነትን ያተረፈ ብርቅየ … [Read more...] about የዶ/ር መረራ መታሰር ሰላማዊው ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል የተደረገ ጥሪ ነው!!!!
ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፣ ሄኖክ የሺጥላ እና ሌሎች የፌስቡክ ታጋዮች!
አንዷ ያገሬ ሴት ደጋግማ ስታወራኝ ነው አንዱን የፌስ ቡክ ዝነኛ ታጋይ ያወቅሁት። እንዴት እስካሁን እንዳላየሁት ገርሞኝ በስሙ ፈልጌ ገባሁ። ጊዜየን አላጠፋሁም። ዘጋሁት። ካሁን ቀደም እንዴት የፌስ ቡክ ገጼ ላይ እንደመጣ ሳላውቀው ገጭ ብሎ ባገኘው ከፍቼ አይቸው፣ ሰምቼው... ወዲያው ነበር የዘጋሁት። ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ሳየው፣ ነብያችን ድንገት ተከስተውለት ኖሮ፣ አዲስ ሙስሊም (convert) ሆኖ ነው መሰለኝ፣ ጥቂት የማውቃቸው ሙስሊም የፌስ ቡክ ወዳጆቼ፣ ላይክ አድርገው “ኢንሻላህ! ሱብሃናሁ ወተዓላ...”፣ “... እንኳን ወደ እውነተኛው እምነት መጣህ ወንድማችን...” ... ወዘተ የሚሉ ጽሁፎች ገጹ ስር ተኮልኩለው አይቼ ሳምንት ሳይሞላኝ ነው ያቺው ያገሬ ሴት ስትነግረኝ እንደገና ፈልጌ የገባሁት። ላካንስ ሰውየው (ካሁን በኋላ “ሰውየው” ስል ይኸኑ ሰውየ ነው) ባንድ ሳምንት … [Read more...] about ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፣ ሄኖክ የሺጥላ እና ሌሎች የፌስቡክ ታጋዮች!
RECLAIMING AN ETHIOPIA FOR ALL ETHIOPIANS
It is time to reclaim Ethiopia for all of us. I, for one, will not stand by as the country we call home is tossed to and fro in the ethnic or sectarian battlefield of the ambitions and interests of a few vying groups. The competition— rather than cooperation—continues until whomever comes out on top takes over to dominate in a recycling of dysfunction that has been repeated again and again in Ethiopia. Once in power, that ethnic or sectarian group suddenly wants to claim leadership over the … [Read more...] about RECLAIMING AN ETHIOPIA FOR ALL ETHIOPIANS










