• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘ-ሃበሻ! እባክሽ “ሙድ” አትያዢብን!

December 21, 2016 10:51 am by Editor Leave a Comment

አንድ ሰው በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን በሚናገራቸው/በሚጽፋቸው ጽሁፎች አስተሳሰቡ እና ብቃቱ ይገመታል፤ የሚመራውን ድርጅት/ተቋም ብቃትም ይናገራል። እንደ ግለ-ሰብ ስለ ራስ፣ ስለ ቤተሰብ እና ስለ ጓደኛ የሚናገራቸው ወይም የሚጽፋቸው ጽሁፎች ከሙያዊ ብቃት እና ችሎታ አኳያ ብዙም የሚያስከትለው ተጽዕኖ አይኖርም። ጋዜጠኛ ነኝ ያለ ሁሉ ጋዜጠኛ እንዳልሆነ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የጋዜጣ አዘጋጅ ስትሆን፣ ከዚያም ብዙ ተከታዩች ሲኖሩህ እና ስለ አገር እና የማህበራዊ ጉዳይ የምትጽፋቸው ሲሆን ግን ቢያንስ ከጋዜጠኛነት ሙያ፣ ከጭብጥም ሆነ ከቋንቋ አጠቃቀም አኳያ ይሄን ያህል መወረድ በ“ሙደኞች” (“ሙድ” የዘ-ሃበሻ የራሷ አማርኛ ነው) ቋንቋ ሙያዊ “ቅሽምና” ነው። ስለዚህ እኛም ዘ-ሃበሻን በ“ሙድ” ልንተች ነው።

“ወያኔ በየቀኑ ህዝባችንን እየገደለና እያሰረ ሙድ ሲይዝብን…” እንዳለችው ሁሉ፣ ዘ-ሃበሻም ሙድ እየያዘችብን ነው የምር! ከሰሞኑ በሳይበር ጥቃት “ከአላማየ ተሰናከልኩ” የምትንለን ዘ-ሃበሻ “በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ከዓላማችን አላሰናከለንም” በማለት “ሙድ” ይዛብናለች።henok-zehabesha

እስቲ ይሄን በሳጥን ውስጥ የተጻፈውን የዘ-ሃበሻን የፌስቡክ “ርዕስ አንቀጽ?” … እና … እባክሽ! ስለ እዝጊሃር ብለሽ፤ ዘ-ሃበሻ! የጋዜጣ ቋንቋ ተናገሪ።

ደሞስ “የሸኖ እና የማረቆ የነጻ አውጪ መንግስት…” የሚባል ተፈጥሯል እንዴ? እውነትም “ከዚህ በላይ የሚያም ነገር” የለም! ዘ-ሃበሻ እውነት ብለሻል። እኛ በቅርቡ የሰማነው “የአማራ ነጻ አውጪ ግንባር” ነው። “ሸኖ” እና “ማረቆ” እያሉ ማድበስበስ ከአንጋፋ፣ በየእስር ቤቶች ተፈትና ከወጣች ጋዜጣ አይጠበቅም።

“…ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በመራመድ” ተግታ የምትሰራው ዘ-ሃበሻ እንዴት በሃከር እንደተሰናከለችም እግዜር ይወቅላት። ለነገሩ ግን ድረ-ገጻችንን “እንዳሰናከለችብን”፣ የ“ማጀቴ ቆሌ አድባር መጀን” ወያኔን ስንክል ያድርጋት አቦ!… እንዲህ ታምረኛ የሆነችው እና ቀን ተሌት በወያኔ ስትሳደድ የምትውለው ጋዜጣችንን….ባይሆን በአማርኛችን ላይ ሙድ ባትይዝብን ይሻላታል፣ የምር!

ይሄ ከዚህ በታች የሰረፈው በአንዱ ድረ-ገጽ ላይ “ዘ-ሃበሻ” በሙድ የለቀቀችብን ጽሁፍ ነው። አላግባብ የገባውን እና ግድፈቱን በቀይ፣ ጠማማውን ስናቃና እና/ወይም ትክክለኛ አማርኛ ነው ያልነውን ደግሞ በአረንጓዴ፤ በጣም “ሙድ ስንይዝባት” ደግሞ በወይነ-ጠጅ እያቀለምን እና እንዲህ {እያቀፍን} ሽንፍላ ማጠባችንን ልንጀምር ነው–በዘ-ሃበሻ ጭብጥ፣ ቋንቋ እና ሰዋሰው ላይ።

“በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ከዓላማችን አላሰናከለንም” – ከዘ–ሐበሻ የተሰጠ መግለጫ

“እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ይቅርና የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም {ይህ እንግዲህ በጋዜጠኝነት ቋንቋ በእንግሊዝኛው “lead” የምንለው መሆኑ ነው። “lead” በአንድ ዜና/ዜና ሃተታ ውስጥ የጽሁፉ ጠቅላላ ሃሳብ በመጀመሪያው አንቀጽ  በአጭሩ የሚገለጽበት፣ አንባቢ ቀድሞ የሚያነበው እና ወደፊት ገፍቶ ለማንበብ ወይም ላለማንበብ የሚወስንበት ወሳኝ ክፍል ነው።}– ከዘ–ሐበሻ የተሰጠ መግለጫ {ድግግሞሽ ነው}

ዘ-ሐበሻ ሃክ በተደረገበት ወቅት መረጃዎቻችን ጠፍተው እንዲህ [ገጹ ጠፍቶ ይታያል] ነበር ድረ-ገጻችን የሚታየው {ጾታዋ ወንድ ነው እዚህ]:: የዘ-ሐበሻ ድረ-ገጽ ከተመሰረተች {transgender surgery …? ሴት ሆነች] 9 ዘጠኝ ዓመት ሆኗታል። ባለፉት 9 ዘጠኝ {እንዲያውም ድግግሞሽ ነው፣ እናም}  በነዚህ ዓመታት ውስጥ {ቢባል የተሻለ ነበር} በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎችን መረጃ ከሚያቀብሉ የመረጃ መረቦች መካከል አንዷ በመሆን በአማራጭነት ሚድያነት አገልግላለች እያገለገለች ትገኛለች:: በየዕለቱ ድክመቶቻችንን በማረም ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በመራመድ {ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር የምትራመድ ዘ-ሃበሻ በ“ሃከር” ስትጠቃ መኖሯ ምነው?} አሁንም ተመራጭና ተአማኒ ሚዲያ ለመሆን ተግተን እየሰራን ነው:: እንደሚታወቀው የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች የሚዲያን ሥራ የጀመሩት እዚህ ስደት ላይ ከወጡ በኋላ አይደለም {ይቺን እንኳን ለ“Resume” ብትጠቀሚ ይሻልሻል ዘ-ሃበሻ}:: በሃገር ቤት በኢትዮጵያ ነጻው ፕሬስ ውስጥ መስዋዕትነት የበከፈሉ፣ የበታሰሩ፣ የበተገረፉና ብዙ መስዋዕትነት በከፈሉ ጋዜጠኞች የምትዘጋጅ ድረ-ገጽ ናት {መገረፍ፣ መታሰሩ እውነት ሆኖ፣ ያኔ በቅንጅት ጊዜ “ጋዜጠኛ ነኝ” ይል የነበረው ሁሉ ጋዜጠኛ አልነበረም። በሽምግልና ስም ህወሃትን አፈር ከላሰበት በማስነሳት የሚታወቁት ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ እና ቡድናቸው ስለ እርቅ ያወሩ በነበረበት እና ትልቅ ዜና ሆኖ በነበረበት ጊዜ “…እንዴ! ሁለቱ ከታረቁማ እኛ {ጥቂት ጋዜጠኞች}  ምን ሰርተን ልንበላ ነው…?} ይሉ የነበሩ እንደነበሩ እና የታሰሩ እንደነበሩም እናውቃለን፣ የታሰረ ሁሉ ብቃት ያለው ጋዜጠኛ ነበር ማለት ግን አይደለም። በጋዜጠኝነት ትምህርትም፣ በልምድም፣ በሁለቱም ጥምረት እና ጥረት በሂደት የተማሩ፣ የተካኑ ያኔም አሁንም በህወሃት በግፍ የተገደሉ፣ የታሰሩ፣ ተሰደው የሚገኙ ጋዜጠኞች እንዳሉ ግን ሃቅ ነው። … ወደ ሽንፊላ አጠባዬ ልግባ እናቴ….} ዘ-ሐበሻ ድረ-ገጽ በተለይ ዕድሜያቸው ከ18 – 45 ዓመት ክልል ውስጥ [በሆኑ አንባቢያን] በብዛት የምትጎበኝ {“ጎብኚ” ናት “ተጎብኚ?” መጥበቅ እና መላላትን መለየት ያስፈልግ ነበር እዚህ}፣ ወቅታዊ መረጃዎችንም በፍጥነት የምታደርስ መሆኗ የሕወሓትን መንግስት ሁሌም እንዳስደነገጠች እንዳሳሰበች ነው {ህወሃት በድንጋጤ “ስትሮክ” ሳይዛት አይቀርም መቼም}:: ባለፉት 9 ዘጠኝ ዓመታት በተለይ በእነዚህ ዕድሜ ክልሎች ውስጥ ባሉ ወገኖች ድረ-ገጻችን በመጎብኘቷና በአብዛኛው በግምት 75% የሚሆነው የዘ-ሐበሻ ድረ-ገጽ ጎብኚም ከኢትዮጵያ መሆኑ ያበሳጨው ያሳሰበው {መንግስት “ተበሳጨ” አይባልም። አቤት! ከጭብጡ ሙትነት፣ የቋንቋው ድህነት!} የሕወሓቱት መንግስት በርካታ ብሮችን በማፍሰስ {1ኛ) ህወሃት ብሩን እያፈሰሰ አይደለም፤ ፤  ዘ-ሐበሻ የምታስተላልፈውን ነጻና ያልተገደበ መረጃ ለማፈን ብዙ ጥረቶችን አድርጓል {እውነት ዘ-ሃበሻን ብቻ ለይቶ ለማጥቃትም ያን ያህል የሚደክም ማስመሰለም አግባብ አይመስለኝም}:: ዘ-ሐበሻ ድረ-ገጽን በሶስተኛ ወገን እንዲሸጥለት ከመጠየቅ አንስቶ ኮምፒውተሮቻችንን ከማጥቃት እስከ አዘጋጆቹ ቤተሰብ ድረስ ሄዶ የሕወሓት መንግስት ያላደረገው ያልሞከረው ነገር የለም:: በአዘጋጆቹን በአካልና በንብረቶችቻቸው ላይ ለማጥቃትም ጥቃት ለማድረስም ብዙ ተሞክሮም ነበር:: ባለፉት 9 ዘጠኝ ዓመታት የደረሰብን ፈተና {እነ እስክንድር፣ ርዕዮት፣ ተመስገን ደሳለኝ እና ሌሎቹ አሁንም ድረስ ዋጋ እየከፈሉ ያሉ ጋዜጠኞች ምን ይበሉ?} በእንዲህ በትንሹ {በትላልቅ ፊደላት አትጽፊውም ኖሯል?} በግማሽ ገጽ ተጽፎ {ወይም “በአጭሩ ተዘርዝሮ የሚያልቅ ብቻ አይደለም:: ዘ-ሐበሻ ድረገጽን ሃክ ለማድረግ ብዙ ወጪዎችን የሚያፈሰው የሕወሓት መንግስት {ዘሃበሻን ለይቶ? የምር?} ከድረገጻችን በተጨማሪ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ተከታይ ያለውን የፌስቡክ ገጻችንን ሃክ እስከማድረግ ደርሶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን {“…ትዝታ በፖስታ ልኬልሻለሁ…” አለ ያ ዘፋኝ} ነው:: የፌስቡክ ገጻችንን ሃክ አድርገው የነበሩ የሕወሓት ተላላኪዎችም በሕግ የሚገባቸውን እርምጃ አግኝተዋል {ርምጃ ተወሰደባቸው? ትልቅ ዜና ከእጅሽ ላይ አምልጦሻል ዘ-ሃበሻ! ይኼን ዜና ነበር መጻፍ የነበረብሽ፤… ለመሆኑ ተላላኪዎቹ እነማን ይባላሉ? ቅጣቱ ግርፋት ነው? ወይስ ስቅላት?…. ሙድ አትያዢብን ባክሽ! ይሄ እንኳን አቶ ማርክ ዙከርበርግን እና ቡድናቸውን ማሳጣት ይመስለናል}::

ይህን በሕወሓት መንግስት የሚደርሰውን የሳይበር ጥቃት ለማምለጥ ዘ-ሐበሻና አዘጋጆቿ በየ6ስድስት ወሩ ኮምፒውተሮቻቸውን ይቀያይሩ ነበር {“የማይመስል ነገር ለሚስትህ አትንገር” አለ ያገሬ ሰው… ከሳይበር ጥቃት ለመዳን በየስድስት ወሩ ኮምፒውተር መቀያየር እንዴት እንደሚያዋጣ የገባት ዘ-ሃበሻ ብቻ መሆን አለባት። እኛ መቼም “how to prevent cyber attack” ብለን ጎልጉለን ካገኘናቸው በአስራዎች ከሚቆጠሩት ዘዴዎች ውስጥ፣ “ኮምፒውተር መቀያየር” የሚል አንድም አላገኘንም።… ይልቅየ ኪሳችንን ዳበስ ዳበስ እናድርግ ጎበዝ!}:: ብዙ ገንዘብ  በማውጣትም {ይኼው! ያልነው ነገር፣ ዳበስ ዳበስ …} የሳይበር ዘገበኛዎችን (ሴክዩሪቶቲዎችን) {“ዘገበኛ” ማለት (“ሴክዩሪቲ” ማለት መሆኑን ገና ዛሬ ተማርኩ፤ “Thank You Ze-habesha)} በመጫንም ጥቃቱን ስንከላከል ቆይተናል:: በዚህም መሃከል ግን ዘወትር ነጻ ሚዲያዎችን ለማፈን የማይተኛው የሕወሕሃት መንግስት እንደገና በዛሬው ዕለት ራሳቸውን “ጋዛ ሃከርስ” ብለው የሚጠሩ ሃከሮችን በመቅጠር {እንደ ህወሃት ያለ ፈሪ መንግስት በምድር አለም ያለ አይመስለኝም የምር! ይኼ ነገር እውነት ከሆነ} የዋና አዘጋጁን ኢሜይል ሃክ በማድረግ እንዲሁም ድረገጹን ሃክ አድርገው በመቆጣጠር ለተወሰነ ሰዓታት ሲያውኩን ውለዋል:: የሕወሓት መንግስት የአዘጋጆቹን ኢሜይል ሃክ ቢያደርግ የሚያገኘው ምንም ምስጢራዊ መረጃ አይኖርም {ምስጢር እና ጉዳት ከሌለው ታዲያ ይሄ ሁሉ “ኢሜል ሃክ ተደረገ” ዋይታ ምን ያደርጋል እዚህ?}:: ዘ-ሐበሻ መረጃን ለሕዝብ ከማድረስ ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት ተልዕኮ የሌላት በመሆኑ ምናልባት ወያኔዎች ኢሜሎቻችንን ቢበረብሩ የሚያገኙት ዞሮ ዞሮ በድረ-ገጻችን ላይ በይፋ ተጽፈው የሚያገኟቸውን ጽሁፎች ብቻ ናቸውና ነውና ለልፋታቸውና ላጠፉት ገንዘብ ኪሳራቸው አስደስቶናል {Adios! Journalism}:: ድረገጻችንን ግን ሃክ ባደረጉትና ጥቃት በፈጸሙበት ቁጥር ግፋ ቢል እኛን የሚያስወጣን ገንዘብና መረጃ ልናደርሰበት የምንችልበትን ውድ ጊዜ ብቻ ነው::

ስለሆነም የሕወሓት መንግስት አንድ ሊገነበዘበው ሊገነዘበው የሚገባው ትልቅ ነገር አለ:: የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች {ስንት ናችሁ? መቼም ዋና አዘጋጅዋ አቶ ሄኖክ ታስረው እንደነበረ በሳይበር ላይ መከላከያ ሚ/ር የነበሩቱ ሲናገሩ ሰምተናል! አዘጋጁ ከህወሃት ግፍ እና መከራ ባጭሩ በመገላገላቸው እንኳን ደስ ያላቸው እንላለን} በሃገር ቤት የስርዓቱን ማሰቃያ እስር ቤቶችንና ጨለማ ክፍሎችን እነማዕከላዊን፣ ከርቸሌን፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያንና ሌሎችንም በመቅመስ {በህወሃት የመታሰር ጣዕሙ ጉድ ነው! …ግን ምን ምን ይላል? ከሆነ አይቀር ጣዕሙም ይነገረን እንጂ! እንደ እሬት ይምረራል? ወይስ ይጎመዝዛል?} የቆሙለትን ዓላማ ያጠነከሩ እንጂ በደረሰባቸው እስር የተፍረከረኩ አይደሉም {…ዘ-ሃበሻን ግን “… ስለ መታሰርሽ ሁሌም ስላወራሽ፣ ብቁ ጋዜጣ አያደርግሽም” የሚል መልዕክት ቢያስተላልፉልን ደግ ነው}:: ሕወሓት ዛሬም በሳይበር ሕወሓት በየሚያደርስብን ጥቃት ከአቋማችን ምንም ፍንክች እንደማያደርገን፣ እንደዲያውም በተጠቃን ቁጥር እንደምንጠነክር {‘አቻዩ ዲፌሮ’ አለ ጥልያን} እንዲገነዘቡት ለመግለጽ እንወዳለን:: ለዚህም ነው በመግቢያችን ላይ “እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም {ይሄን የእስራት ወሬ መስማት አሁንስ ደከመኝ፣ የምር! ይኼን የ“ታስረን ነበር” ዜና/ር ዕስ አንቀጽ ሆኖ ስናነብ ምናልባትም አሁን ለ10ኛ ጊዜ ይሆናል። ካገር የተሰደደው ጋዜጠኛ ሁሉ ለሙያው ክብር ሲል እንዲህ አይነቱን የወረደ ነገር እየሰማ እና እያነበበ ዝም ማለት አልነበረበትም} ከዓላማችን አላሰናከለንም” ያልነው::

ዕውነት ያሸንፋል!

የዘ-ሐበሻ ኤዲቶሪያል ቦርድ

ዘ-ሃበሻ ምናልባትም ከሁሉም የኢትዮጵያ ሜዲያዎች በላይ ጎብኚ እንዳላት እርግጥ ይመስለናል። ምክንያቱ ደግሞ በራሷ ቋንቋ ከዚህ ቀደም “ብዙ ጎብኚ ያለን … ድረ-ገጻችንን በኢንፎርሜሽን በማጨቃችን  ነው” እንዳለችው ነው። ይኼው ነው። በዘጠኝ አመት ታሪኳ፣ አንድም የራሷን ዜና፣ ዜና ሃተታ እና ርዕስ አንቀጽ ሰርታ አታውቅም (እስከማውቀው ድረስ፣ ጥቂት ሚዲያዎች አልፎ አልፎ እንደ መግቢያ አይነት ጽሁፎችን የሚያወጡ ከመሆናቸው በስተቀር፣ በመደበኛነት የራሳቸውን ዜና እና ርዕስ አንቀጽ የሚጽፉ ጋዜጦች ብዙም የሉንም። ከማናቸውም ከአገር ውጭ ከሚገኙ/ከተመሰረቱ እና እኔ ከማውቃቸው የድረ-ገጽ ጋዜጦች/ሜዲያዎች ውስጥ የራሱን ዜና በተለይም የራሱን ርዕስ አንቀጽ በመደበኛነት በመጻፍ “ኢሳት {ሪሶርሱም  የሰው ሃይሉም የተሻለ ስለሆነም ጭምር ነው} እና “ጉልጉል” የመጀመሪያውን ደረጃ የሚይዙ ይመስለኛል። የሪሶርስ መኖር እና አለመኖር በተወሰነ መልኩ ሊረዳ ቢችልም፣ የሃገር፣ የሙያ፣ እና የአላማ ጽናትና ፍቅር ካለ እንደ ፕ/ር አል-ማርያም ለአስር አመት ሙሉ፣ አንዲትም ሰኞ ሳያጓድሉ መጻፍ … እኔ የሚገርመኝ የፕሮፌሰሩ የዕለት ከዕለት የሙያ እና ህይወት ዲሲፕሊኑ ነው። …

ጎልጉል ለምሳሌ የወቅቱን ፖለቲካችንን እና በጋምቤላ ዜጎቻችን ላይ የደረሰውን እልቂት አስመልክቶ በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ጽሁፎችን አውጥቷል። “ጎልጉል” በአንድ ነገሩም ልዩ ነው–የ“ጎግል”ም ሆነ የሌላ ሰርጎ-ገብ  ማስታወቂያ ድንገት የምታነበው ገጽ ላይ እየተደቀነ “አንጎል” አያደርግህም። ዘ-ሃበሻን እኮ በመደበኛነት ማየት በጣም ያስፈራኝ ጀምሯል፣ ቀድሞ ነገር ምንነቱን የማታውቀው ማስታወቂያ ድንገት ገጹ ላይ ይደቀናል። ሲመስለኝ ዘ-ሃበሻ ሃክ የመደረጓ ምክንያት፣ ካለ ምርጫ የምታግበሰብሰው የሶሻል ሜዲያ ጓደኛ፣ RRS feed, ወዘተ ሊንክ መዐት ይመስለኛል። ህወሃት ዘ-ሃበሻን ብቻውን ለይቶ ሃክ ለማድረግ የማይተኛ መንግስት አድርጎ ማቅረብ መሰረት የለውም።

በተረፈ ዘ-ሃበሻ “ስትታሰር፣ ከርቼሌ ስትወርድ፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ዘብጥያ ወርዳ፣ ስትሰቃይ ወዘተ…” መክረሟን እና መከራዋን ያየችበት ጋዜጠኝነት እንዲያው መና ይቅር አይባልም! ይሁን። ነገር ግን ከተመሰረተች ከዘጠኝ አመታት በኋላም እንኳን እንዲህ ያለ ጋዜጠኝነት ያሳየችን ዘ-ሃበሻ፣ ያኔ የሰራችው ጋዜጠኝነት እንዴት ቢሆን ይሆን? እንላለን መቼም ሙድ ስንይዝባት! ዘ-ሃበሻ እባክሽ ሰከን በይ ትንሽ! … ይሁኔ በላይን …።

በታፈሰ ወርቁ

tafeseworku2016@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule