• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ይቅርና የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም”

December 14, 2016 08:20 pm by Editor 1 Comment

ዘ-ሐበሻ ድረገጽ ከተመሰረተች 9 ዓመት ሆኗታል:: ባለፉት 9 ዓመታት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎችን መረጃ ከሚያቀብሉ የመረጃ መረቦች መካከል አንዷ በመሆን በአማራጭነት ሚድያነት አገልግላለች:: በየዕለቱ ድክመቶቻችን በማረም ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በመራመድ አሁንም ተመራጭና ተአማኒ ሚዲያ ለመሆን ተግተን እየሰራን ነው::

እንደሚታወቀው የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች የሚዲያን ሥራ የጀመሩት እዚህ ስደት ላይ ከወጡ በኋላ አይደለም:: በሃገር ቤት በኢትዮጵያ ነጻው ፕሬስ ውስጥ መስዋዕትነት የከፈሉ፣ የታሰሩ፣ የተገረፉና ብዙ መስዋዕትነት በከፈሉ ጋዜጠኞች የምትዘጋጅ ድረገጽ ናት::

ዘ-ሐበሻ ድረገጽ በተለይ ዕድሜያቸው ከ18 – 45 ዓመት ክልል ውስጥ በብዛት የምትጎበኝ፣ ወቅታዊ መረጃዎችንም በፍጥነት የምታደርስ መሆኗ የሕወሓትን መንግስት ሁሌም እንዳስደነገጠች ነው:: ባለፉት 9 ዓመታት በተለይ በእነዚህ ዕድሜ ክልሎች ባሉ ወገኖች ድረገጻችን በመጎብኘቷና በአብዛኛው 75% የሚሆነው የዘ-ሐበሻ ድረገጽ ጎብኚም ከኢትዮጵያ መሆኑ ያበሳጨው የሕወሓቱ መንግስት በርካታ ብሮችን በማፍሰስ ዘ-ሐበሻ የምታስተላልፈውን ነጻና ያልተገደበ መረጃ ለማፈን ብዙ ጥረቶችን አድርጓል:: ዘ-ሐበሻ ድረገጽን በሶስተኛ ወገን እንዲሸጥለት ከመጠየቅ አንስቶ ኮምፒውተሮቻችንን ከማጥቃት እስከ አዘጋጆቹ ቤተሰብ ድረስ ሄዶ የሕወሓት መንግስት ያላደረገው ያልሞከረው ነገር የለም:: አዘጋጆቹን በአካልና በንብረቶቻቸው ላይ ለማጥቃትም ብዙ ተሞክሮም ነበር::screen-shot-2016-12-14-at-7-51-21-pm

ባለፉት 9 ዓመታት የደረሰብን ፈተና እንዲህ በትንሹ ተጽፎ የሚያልቅ ብቻ አይደለም:: ዘ-ሐበሻ ድረገጽን ሃክ ለማድረግ ብዙ ወጪዎችን የሚያፈሰው የሕወሓት መንግስት ከድረገጻችን በተጨማሪ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ተከታይ ያለውን የፌስቡክ ገጻችንን ሃክ እስከማድረግ ደርሶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው:: የፌስቡክ ገጻችንን ሃክ አድርገው የነበሩ የሕወሓት ተላላኪዎችም በሕግ የሚገባቸውን እርምጃ አግኝተዋል::

ይህን በሕወሓት መንግስት የሚደርሰውን የሳይበር ጥቃት ለማምለጥ ዘ-ሐበሻና አዘጋጆቿ በየ6 ወሩ ኮምፒውተሮቻቸውን ይቀያይሩ ነበር:: ብዙ ገንዘብ በማውጣትም የሳይበር ዘገበኛዎችን (ሴክዩሪቶዎችን) በመጫንም ጥቃቱን ስንከላከል ቆይተናል:: በዚህም መሃከል ግን ዘወትር ነጻ ሚዲያዎችን ለማፈን የማይተኛው የሕወሕት መንግስት እንደገና በዛሬው ዕለት ራሳቸውን “ጋዛ ሃከርስ” ብለው የሚጠሩ ሃከሮችን በመቅጠር የዋና አዘጋጁን ኢሜይል ሃክ በማድረግ እንዲሁም ድረገጹን ሃክ አድርገው በመቆጣጠር ለተወሰነ ሰዓታት ሲያውኩን ውለዋል::

የሕወሓት መንግስት የአዘጋጆቹን ኢሜይል ሃክ ቢያደርግ የሚያገኘው ምንም ምስጢራዊ መረጃ አይኖርም:: ዘ-ሐበሻ መረጃን ለሕዝብ ከማድረስ ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት ተልዕኮ የሌላት በመሆኑ ምናልባት ወያኔዎች ኢሜሎቻችንን ቢበረብሩ የሚያገኙት ዞሮ ዞሮ በድረገጻችን ላይ በይፋ ተጽፈው የሚያገኟቸውን ጽሁፎች ብቻ ናቸውና ለልፋታቸውና ላጠፉት ገንዘብ ኪሳራቸው አስደስቶናል:: ድረገጻችንን ግን ሃክ ባደረጉትና ጥቃት በፈጸሙበት ቁጥር ግፋ ቢል እኛን የሚያስወጣን ገንዘብና መረጃ ልናደርሰበት የምንችልበትን ውድ ጊዜ ብቻ ነው::

ስለሆነም የሕወሓት መንግስት አንድ ሊገነበዘበው የሚገባው ትልቅ ነገር አለ:: የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች በሃገር ቤት የስርዓቱን ማሰቃያ እስር ቤቶችንና ጨለማ ክፍሎችን እነማዕከላዊን፣ ከርቸሌን፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያንና ሌሎችንም በመቅመስ የቆሙለትን ዓላማ ያጠነከሩ እንጂ በደረሰባቸው እስር የተፍረከረኩ አይደሉም:: ዛሬም በሳይበር ሕወሓት በሚያደርስብን ጥቃት ከአቋማችን ምንም ፍንክች እንደማያደርገን፣ እንደውም በተጠቃን ቁጥር እንደምንጠነክር እንዲገነዘቡት ለመግለጽ እንወዳለን:: ለዚህም ነው በመግቢያችን ላይ “እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም” ያልነው::

ዕውነት ያሸንፋል!
የዘ-ሐበሻ ኤዲቶሪያል ቦርድ

henocka2001@yahoo.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    December 22, 2016 05:38 pm at 5:38 pm

    If anybody is involved in oppressing people in the name of the people of Tigray,he isn’t ours,individual or collective.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule