• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ይቅርና የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም”

December 14, 2016 08:20 pm by Editor 1 Comment

ዘ-ሐበሻ ድረገጽ ከተመሰረተች 9 ዓመት ሆኗታል:: ባለፉት 9 ዓመታት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎችን መረጃ ከሚያቀብሉ የመረጃ መረቦች መካከል አንዷ በመሆን በአማራጭነት ሚድያነት አገልግላለች:: በየዕለቱ ድክመቶቻችን በማረም ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በመራመድ አሁንም ተመራጭና ተአማኒ ሚዲያ ለመሆን ተግተን እየሰራን ነው::

እንደሚታወቀው የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች የሚዲያን ሥራ የጀመሩት እዚህ ስደት ላይ ከወጡ በኋላ አይደለም:: በሃገር ቤት በኢትዮጵያ ነጻው ፕሬስ ውስጥ መስዋዕትነት የከፈሉ፣ የታሰሩ፣ የተገረፉና ብዙ መስዋዕትነት በከፈሉ ጋዜጠኞች የምትዘጋጅ ድረገጽ ናት::

ዘ-ሐበሻ ድረገጽ በተለይ ዕድሜያቸው ከ18 – 45 ዓመት ክልል ውስጥ በብዛት የምትጎበኝ፣ ወቅታዊ መረጃዎችንም በፍጥነት የምታደርስ መሆኗ የሕወሓትን መንግስት ሁሌም እንዳስደነገጠች ነው:: ባለፉት 9 ዓመታት በተለይ በእነዚህ ዕድሜ ክልሎች ባሉ ወገኖች ድረገጻችን በመጎብኘቷና በአብዛኛው 75% የሚሆነው የዘ-ሐበሻ ድረገጽ ጎብኚም ከኢትዮጵያ መሆኑ ያበሳጨው የሕወሓቱ መንግስት በርካታ ብሮችን በማፍሰስ ዘ-ሐበሻ የምታስተላልፈውን ነጻና ያልተገደበ መረጃ ለማፈን ብዙ ጥረቶችን አድርጓል:: ዘ-ሐበሻ ድረገጽን በሶስተኛ ወገን እንዲሸጥለት ከመጠየቅ አንስቶ ኮምፒውተሮቻችንን ከማጥቃት እስከ አዘጋጆቹ ቤተሰብ ድረስ ሄዶ የሕወሓት መንግስት ያላደረገው ያልሞከረው ነገር የለም:: አዘጋጆቹን በአካልና በንብረቶቻቸው ላይ ለማጥቃትም ብዙ ተሞክሮም ነበር::screen-shot-2016-12-14-at-7-51-21-pm

ባለፉት 9 ዓመታት የደረሰብን ፈተና እንዲህ በትንሹ ተጽፎ የሚያልቅ ብቻ አይደለም:: ዘ-ሐበሻ ድረገጽን ሃክ ለማድረግ ብዙ ወጪዎችን የሚያፈሰው የሕወሓት መንግስት ከድረገጻችን በተጨማሪ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ተከታይ ያለውን የፌስቡክ ገጻችንን ሃክ እስከማድረግ ደርሶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው:: የፌስቡክ ገጻችንን ሃክ አድርገው የነበሩ የሕወሓት ተላላኪዎችም በሕግ የሚገባቸውን እርምጃ አግኝተዋል::

ይህን በሕወሓት መንግስት የሚደርሰውን የሳይበር ጥቃት ለማምለጥ ዘ-ሐበሻና አዘጋጆቿ በየ6 ወሩ ኮምፒውተሮቻቸውን ይቀያይሩ ነበር:: ብዙ ገንዘብ በማውጣትም የሳይበር ዘገበኛዎችን (ሴክዩሪቶዎችን) በመጫንም ጥቃቱን ስንከላከል ቆይተናል:: በዚህም መሃከል ግን ዘወትር ነጻ ሚዲያዎችን ለማፈን የማይተኛው የሕወሕት መንግስት እንደገና በዛሬው ዕለት ራሳቸውን “ጋዛ ሃከርስ” ብለው የሚጠሩ ሃከሮችን በመቅጠር የዋና አዘጋጁን ኢሜይል ሃክ በማድረግ እንዲሁም ድረገጹን ሃክ አድርገው በመቆጣጠር ለተወሰነ ሰዓታት ሲያውኩን ውለዋል::

የሕወሓት መንግስት የአዘጋጆቹን ኢሜይል ሃክ ቢያደርግ የሚያገኘው ምንም ምስጢራዊ መረጃ አይኖርም:: ዘ-ሐበሻ መረጃን ለሕዝብ ከማድረስ ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት ተልዕኮ የሌላት በመሆኑ ምናልባት ወያኔዎች ኢሜሎቻችንን ቢበረብሩ የሚያገኙት ዞሮ ዞሮ በድረገጻችን ላይ በይፋ ተጽፈው የሚያገኟቸውን ጽሁፎች ብቻ ናቸውና ለልፋታቸውና ላጠፉት ገንዘብ ኪሳራቸው አስደስቶናል:: ድረገጻችንን ግን ሃክ ባደረጉትና ጥቃት በፈጸሙበት ቁጥር ግፋ ቢል እኛን የሚያስወጣን ገንዘብና መረጃ ልናደርሰበት የምንችልበትን ውድ ጊዜ ብቻ ነው::

ስለሆነም የሕወሓት መንግስት አንድ ሊገነበዘበው የሚገባው ትልቅ ነገር አለ:: የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች በሃገር ቤት የስርዓቱን ማሰቃያ እስር ቤቶችንና ጨለማ ክፍሎችን እነማዕከላዊን፣ ከርቸሌን፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያንና ሌሎችንም በመቅመስ የቆሙለትን ዓላማ ያጠነከሩ እንጂ በደረሰባቸው እስር የተፍረከረኩ አይደሉም:: ዛሬም በሳይበር ሕወሓት በሚያደርስብን ጥቃት ከአቋማችን ምንም ፍንክች እንደማያደርገን፣ እንደውም በተጠቃን ቁጥር እንደምንጠነክር እንዲገነዘቡት ለመግለጽ እንወዳለን:: ለዚህም ነው በመግቢያችን ላይ “እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም” ያልነው::

ዕውነት ያሸንፋል!
የዘ-ሐበሻ ኤዲቶሪያል ቦርድ

henocka2001@yahoo.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    December 22, 2016 05:38 pm at 5:38 pm

    If anybody is involved in oppressing people in the name of the people of Tigray,he isn’t ours,individual or collective.

    Reply

Leave a Reply to Tadesse Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule