• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአጋንንት ፖለቲካ – ውጣ!!

December 15, 2016 11:50 pm by Editor Leave a Comment

ልብ ማለት ያቃተን ለምን ይሆን? የማንሰለጥነውስ ለምንድን ነው? በፖለቲካ ትግል ውስጥ ዕድሜ ገፍተን የማንበስለው እስከመቼ ነው? አድሮ ቃሪያ፣ አድሮ ጥሬ … እንዲሉ በጫጫታ ትውልድን የምናሰቃየው ስለ ምንድን ነው? ብዙ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል። ይህ በድህነትና በችጋር የሚቃጠለው ህዝብስ ማን ያስብለት? ማን ይድረስለት? በእነማን ብርሃን ይመልከት? ማን ከጨለማ እንዲወጣ ይምራው? ሩብ ምዕተ ዓመት እንደተባላን እንቀጥል? ያሳዝናል? ያስለቅሳል፣ እጅግ ያንገበግባል … ንስሃ የማያውቅ የአጋንንት ፖለቲካ ይሏል እኛ ነን!!

ችግሩ አንድ ወገን ዘንድ ብቻ አይደለም። ችግሩ ሁሉም ዘንድ በውጭም በውስጥም ነው። በውስጥ የተመቸ የመፎካከሪያ ሜዳ የለም። እያደር ይሻላል ሲባል ጭራሹኑ ህወሃት/ኢህአዴግ ሌሎችን “አያገባችሁም” አለና አረፈው። ይህ አልበቃ ብሎ ምክንያት እየተፈለገ ማሳደድና በበትር መግዛትን መረጠ። እያከረረ ሲሄድ ከረረበትና “በጥልቁ ልታደስ፣ ታድሼ መልስ እሰጣለሁ፣ ስልጣን ህዝብን ማገልገያ እንጂ …” እስከማለት፣ ከዚያም አልፎ አስቸኳይ አዋጅ እስከማውጣት ደረሰ። የሆነውንና የሚሆነውን እያየነው ነው!!

በውስጥ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞች አንድ ርምጃ ወደፊት ተራምደው ብዙ ርምጃ ወደኋላ መመለስ ባህላቸው ሆኖ የደጋፊዎቻቸው ማፈሪያ፣ ለሚጠሏቸው መሳለቂያ ሲሆኑ ማየት የተለመደ ነው። እርስ በእርስ ሙግት እየገጠሙ የሚታገሉትን ኢህአዴግን ገላጋይ አድርገው አውጫጪኝ መቀመጥን መሰረታዊ መርሃቸው ይመስላል። ስም አንዘረዝርም። “ወጣ ወጣና” የተባለው ሰማያዊ ፓርቲ የቅርብ ማሳያ ነው (ግፍ እየተጋቱ ያሉትን ወገኖች ሳይሆን የፓርቲውን አመራር)። ነገም ሌላ ይሰማል። እዚህ ላይ ኢህአዴግ “ሰርጎ እየገባ ነው” የሚል ምክንያት ሲሰጥ ይሰማል። በራቸውን ከፍተውለት አይደለም ሳይከፍቱለት በርግዶ ለሚገባው ኢህአዴግ ለምን ክፍት ይሆናሉ? ከተደለሉ ይደልላል። ከተሸጡ ይገዛቸዋል። ከረከሱ የበለጠ ያረክሳቸዋል። እየተከታተለ ተቃዋሚዎቹን ማስለሉ ራሱን ዞሮ የሚጎዳውና አገሪቱንም ወደማይጠቅም ችግር መጎተቱ የማይቀር ቢሆንም፣ ለምን “እምቢ” የሚሉ ቆፍጣና ታጋዮች አይፈጠሩም? ይህንን ስንል በአገር ውስጥ እስከ አሁኑ ደቂቃ ድረስ የህይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉትን ዘንግተን እንዳልሆነ ስተዋልልን። እያልን ያለው እንደ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ድርጅት ነው!

በውጭ አገር የሚሆነውን ላስተዋለ የሚገርም፣ የሚደንቅ፣ የሚዘገንን፣ የሚሰለች፣ ምን እየሆን እንደሆነ እስከማይገባ ድረስ አንጎል የሚያዞር ትዕይንት ነው የሚታየው። መነጋገር የሚባል ነገር በአዋጅ የተከለከለ ይመስላል። “አማራ ይደራጅ” የሚሉ ይደመጣሉ። እነሱን የሚቃወሙ ይደመጣሉ፤ “ሁሉም በአንድ ማዕቀፍ ሥር ይሁኑና ትግሉን ወጥ ያድርጉት” የሚሉ አሉ። ጽንፈኝነት አፍንጫቸው ደርሶ ሜንጫና ቢላ የሚሉ ደግሞ “ለአማራ ብሄርተኛነት ወደፊት” በማለት እውቅና ሲሰጡ … ጉዱ ብዙ ነው። በፌስቡክ የሚወርደው ስድብና የእርስ በርስ አተካሮ እንደ እሳተ ጎመራ የሚንተከተክ ነው። ይህ ሁሉ የሚያርፈው ኢትዮጵያችን ላይ ነው!! ያሳዝናል።

ነጻ አመለካከት ያላቸው ሲተነፍሱ ይፈረጃሉ። ወያኔ ወይም ግንቦት 7 ይባላሉ። በሁሉም አቅጣጫ ነጻ ሚዲያ እንዳያብብ ከውስጥ ህወሃት/ኢህአዴግ፤ ከውጭ የዳያስጶራው ኃይል የመጀመሪያ ተከፊ ይሆናሉ። በዚህ መልኩ እንዴት ይቀጥላል? መሻሻልስ እንዴት ይመጣል?

ይህንን ሁሉ ያነሳነው አዲስ ጉዳይ ሆኖ ሳይሆን እንደዜጋ ግራ መጋባታችንን ለመግለጽና የመፈትሄው አካል ለመሆን በማሰብ ነው። ሁሉም በፈለገው መንገድ ይደራጅ፣ ይታገል፣ ህዝብ ፈራጅ ነውና!! አማራ ሲፈለግ በነጻ አውጪ፣ ሲፈልግ ራስን በመከላከል፣ ሲያሻው በብሄራዊ ደረጃ፣ አለያም በከፋኝ ስም ይዋቀር … አስር ድርጅቶች ይሁኑ፣ መቶም ይሙሉ ሌላው ለምን የራሱን ስራ አይሰራም? የራስን ሥራ በመሥራት የሕዝብን አእምሮና ልብ የራስ ማድረግ ይቻላል። ወቀሳና ውርጅብን ላይ ከማተኮር ሥራን መሥራት በሕዝብ ዘንድ ተዓማኒ ደርጋል። ሕዝብ ይሰማል፣ የሚሸጥለትን ሐሳብ ይመረምራል፣ የሚያሳምነው ሲሆን ይገዛል። ሐሳባቸው ያልተገዛላቸው ይከስራሉ፤ ከጨዋታው ውጭ ይሆናሉ። ነገርግን “ለፍቼ ያከማቸሁት በግ እንዳይሰረቅብኝ” በሚል አስተሳሰብ ሳይተኮስበት ዘራፍ ማለት፤ የሌሎችን አሠራርና አደረጃጀት መቃወም፣ ማብጠልጠል፣ ማዋረድ፣ … “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ አቢዮታችንን እንገነባለን” የሚለው የደርግ መፈክር ብቻ ሳይሆን የግራው ልክፍት መሆኑን ማረጋገጫ ነው፡፡ ልክፍቱ ደግሞ አሁን ድረስ በውርስ እንደተላለፈብን የሚያሳይ ንሰሃ የማያውቅ የአጋንንት ፖለቲካ ለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡

ኢትዮጵያን ብለው የሚታገሉ ስራቸውን ይስሩ፣ ከተራ ጉንጭ አልፋ ንትርክ ይልቅ ሰርተው ያሳዩ፤ በውጤት አፍ ማስያዝ ስለሚቻል ተግባር ላይ ይትጉ። ሁሉም ወገኖች በህዝብ እይታ የራሳቸው ደረጃና ዋጋ ስላላቸው፣ ዞሮ ዞሮ ይሁንታ የሚሰጣቸው ህዝብ ስላለ አስቀድሞ የሚደረገው ውዝግብ ማንንም አያራምድምና ይቁም። ሁሉም እምነቱን ይዞ ጠረጴዛ ዘንድ ይቀመጥ፤ መገንጠል የሸዋው፣ የሃረሩ፣ የወለጋው፣ የአርሲው፣ የጅማው፣ የባሌው፣ የቦረናው …. ኦሮሞ ልባዊ እምነት ከሆነ ወደፊት የሚታይ ነውና በጽንፈኛነት እንቀጥል የሚሉትም ይቅናቸው። ስድብ፣ ማግለል፣ ጥላቻ፣ ለኔ መኖር የሌላው መጥፋት ወሳኝ ነው በማለት መትጋት፣ ሃሳብን ሸጦ ሕዝብን ከማሳመን ይልቅ በግለሰብም ሆነ በድርጅት ላይ ማኅበራዊ ድቅር በመፍጠር አድልዖና መድልዖ ማድረስ፣ ከሃሳብን ከመሞገት ይልቅ ዘር፣ ማንነት፣ የፖለቲካ አመለካከት፣ እና ሌሎችም ላይ በማተኮር በተቀናቃኝ ስም የሚደረጉ የማያባሩ ጥቃቶች በሙሉ የአጋንንት ፖለቲካ ውጤት ነው፡፡ ከዚህ መውጣት የማይፈልጉ መኖራቸው የማይካድ ቢሆንም መውጣት ግን የግድ ነው፡፡ ሐሳብን ሸጦ፣ ዓላማን በተግባር አሳይቶ የህዝብን ቀልብ መሳብና ልቡን ማሸነፍ ንሰሐው ነው፡፡


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule