የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንትና የገዢው የኤኤንሲ /የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ/ፓርቲ ሊቀመንበር የነበሩትን ኔልሰን ሮሊህላህላ ማንዴላ ከሦስት ትውልድ ያላነሰ አፍሪካዊና የሌላው አህጉር ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። እኝህ ሰው ይበልጥ ከሚታወቁባቸው ጉዳያቸው ውስጥ በአገሪቱ በነበረው አፓርታይድና ዘረኛ ስርዓት ለ27 ዓመታት መታሰራቸው ብሎም ከእስር በኋላ ለአሳሪዎቻቸውና በብዙ ሚሊዮን ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያንን አንገብግበው ለገዙ የዘር መድሎ ለፈፀሙ እንዲሁም የግርፋት የግድያና የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎችን ለሰሩ ነጭ በዝባዦቻቸው ይቅር ማለታቸው ዋነኛው ነው። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ኔልሰን ማንዴላና ህፀፆቹ
Opinions
የኔ ሃሳብ
አያስቅም! አጭር ወግ
በብሄራዊ ትያትር አካባቢ አንዲት አነስተኛ ምግብ ቤት ነበረች። «ገሊላ ምግብ ቤት» ትባል ነበር። በአዲስ አበባ «ቁምራ» ከመግባቱ በፊት በአካባቢው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች በምሳ ሰዓት ይህችን ምግብ ቤት ያጨናንቋት ነበር። ቁምራን የማታውቁ ካላችሁ፤ ለጽድቅ የሚደረግ መንፈሳዊ ጾም እንዳይመስላችሁ። እድገትና ትራንስፎርሜሽኑ ያመጣው አዲስ ክስተት ነው - ቁርስ ምሳና ራት በአንድ ጊዜ የመመገብ ዘዴ። «ኑሮ በዘዴ፣ ጾም በኩዳዴ» ይባል ነበር። ይህ አባባል አሁን መኖ በዘዴ በሚል ተቀይሯል። መቼም ሁሉም ነገር በነበር እየቀረ ነው። ጋዜጠኛ አቤል አለማየሁ በቅርቡ ባሳተመው "የአዲስ አበባ ጉዶች" የሚል መጽሃፉ ላይ ስለዚህች ታሪካዊ ምግብ ቤትም ትንሽ ብሏል። የምግብ ቤትዋ ባለቤት "ገሊላ ምግብ ቤት" የሚለው ጽሁፍ በከፊል አጥፍተውታል። አሁን ምግብ ቤት የሚለው ተነስቶ "ገሊላ" … [Read more...] about አያስቅም! አጭር ወግ
በአሁኑ ሰዓት ጦቢያን የሚመራት ማነው?
"በአሁኑ ሰዓት ጦቢያን የሚመራት ማነው “Who is in Charge?” የሚለው ጥያቄ ያሳሰባቸው ቧልተኞች የፈጠሩትን ቀልድ ላልሰማችሁ ላሰማችሁ፡፡ (ኮፒራይቱ የሰፊው ህዝብ እንደሆነ ይታወቅልኝ!) አንዱ ኤፍኤም ሬዲዮ ይደውላል - ዘፈን ለመምረጥ። ደዋይ - ዘፈን ለመምረጥ ነበረ፤ የእገሌን … ኤፍ ኤም- ማን እንበል? ከየት ነው? ደዋይ- የገዢው መደብ አባል ነኝ---- ከደቡብ! ኤፍ ኤም- (ደንገጥ ብሎ) ከደቡብ … እሺ ዘፈኑ ይቀጥላል … (የኤፍኤሙ ጋዜጠኛ ከድብልቅልቅ ስሜት ሳይወጣ ሌላ ዘፈን መራጭ ይደውላል) ኤፍ ኤም- ሄሎ … ማን እንበል? ከየት ነው? ደዋይ - ዘፈን ለመምረጥ ነበር ኤፍኤም- ራስህን አስተዋውቀን? ደዋይ - የገዢው መደብ አባል ነኝ - ከትግራይ! ኤፍኤም - እንዴትነው ነገሩ? አሁን ከደቡብ ደውሎ የገዢው መደብ አባል ነኝ … [Read more...] about በአሁኑ ሰዓት ጦቢያን የሚመራት ማነው?
“የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ”
ይኽን ጽሑፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ ዐርብ የካቲት 28 ቀን (March 7, 2014) አንድነቶች “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባቤትነት” የሚል ህዝባዊ ንቅናቄ (ህዝባዊ ሰላማዊ ዘመቻ) በ14 ከተሞች {አዲስ አበባ፣ ደሴ፣ አዋሳ፣ አዳማ/ናዝሬት፣ መቀሌ፣ ደብረታቦር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ድሬ ደዋ፣ ጅንካ፣ ቁጫ፣ አሶሳ፣ ነቀምት፣ ለገጣፎ፣ እና በተጓዳኝ ከተሞች ወልዲያ፣ ጋምቤላ፣ ም/አርማጨሆ(አብርሃ ጅራ)} እንደሚያደርጉ ማሳወቃቸው ነው። መግለጫቸውን እንዳነበብኩ ዘመቻው ለታሪካችን፣ ለተያያዝነው የነፃነት ትግል እና አይናችን ለተከልነበት የዴሞክራሲ ሽግግር የሚሰጣቸው ጠቀሚታዎች አሉን? የሚሉትን ጥያቄዎች አንስቼ ጥቂት ከራሴ ጋር ከተነጋገርኩ በኋላ ለዘመቻው ድጋፌን በመስጠት እና አንድነቶችን በማበረታት ተሳትፎዬን እንድገልጽ ህሊናዬ የግድ አለኝ። ስለዚህ የዚህ ጽሑፍ ግብ ዘመቻው … [Read more...] about “የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ”
Sexual Violence and Rape against Ethiopian Women!
Sexual violence and rape are weapons used indiscriminately by TPLF/EPRDF cadres, soldiers and federal police in Ethiopia. They targeted innocent people living in villages and towns who are caught in the crossfire. Ethiopia is often described as being 'the most dangerous place in the world to be a woman'. The UN estimates that a staggering more than 200,000 women and girls have been victims of rape and/or sexual violence in Ethiopia during the last 15 years. The worst of the violence is … [Read more...] about Sexual Violence and Rape against Ethiopian Women!
ሰላማዊ ወይስ የትጥቅ ትግል ወይስ ማንፈራጠጥ
የተማረ ወይም የእውቀት ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ክፍል ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ሰላማዊ ይሁን ወይስ በትጥቅ ትግል የሚለውን የጦፈ ክርክር ሲያደርግ ሃያ ሁለት ዓመታት ሆነው፤ ዳኛ የሌለበት ክርክር ስለሆነ የመደማመጥ ግዴታ ታይቶበት አይታወቅም፤ ስለዚህም በሁለቱ መሀከል ያለው ልዩነት ግልጽ ሆኖ አያውቅም፤ አንድ፣ ከሁሉ በፊት ሰላማዊ ትግል በሀሳብ ደረጃ መሆኑንና የትጥቅ ትግል ደግሞ በተግባር መሆኑን ለይቶ ለመረዳት ችግር ሆኖ ቆይቶኣል፤ በሌላ አነጋገር ሰላማዊ ትግል በሀሳብ፣ በንግግር፣ በተለያዩ ሀሳብን ለማስለወጥ መቀስቀሻ በሚሆኑ መንገዶች ተቃውሞን መግለጽ ነው፤ በአንጻሩ የትጥቅ ትግል በጠመንጃ ወይም በጉልበት ያለውን የአገዛዝ ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ ሙከራ ነው፤ ሁለት፣ እንዲህ ከሆነ በሰላማዊ ትግል ለሚያምኑ ሰዎች ያለምንም ጥርጥር በተለያዩ … [Read more...] about ሰላማዊ ወይስ የትጥቅ ትግል ወይስ ማንፈራጠጥ
በክርስትና ላይ ጥናታዊ ምርምር ሲያደርግ የነበረው ሰው በራሱ ሕይወት ላይ ምርመራ ተደርጎበት እጁን ሰጠ!!!
ወንድ ልጅ ሲወለድ አባት ለተወለደው ልጁ ጠብ - መንጃ (ጠመንጃ) ለመግዛት ደፋ ቀና ከሚባልበት አካባቢ ነው ተወልጄ ያደኩት፡፡ ይህ የሚደረገው ደግሞ በቂ ሃብት ስላለ ሳይሆን “ወንድ ልጅ ተወልዶ ካልሆነ እንደ አባቱ እንዝርት አቅርቡለት ይፍተል እንደ እናቱ” የሚለው የንቀት አባባል በልጁ ላይ ሲያድግ እንዳይደርስበት ከወዲሁ ለማዘጋጀት ነው፡፡ እንዲያውም ልጅ በልጅ ተሸንፎና ተመትቶ እያለቀሰ ወደ ወላጆቹ ለእርዳታ ሲቀርብ አልቃሻ ልጅ አልወድም/የለኝም ተብሎ በጥፊ ወይም በአለንጋ ይደገማል፡፡ በለው! ትሸነፍና ወዮለህ! እንዳታሳፍረኝ! የሴት ልጅ! (ከወንድ ብቻ የተወለደ ያለ ይመስል)፣ ሊጥ አትሁን!፣ አስለቅስ እንጂ አታልቅስ!፤ አትበለጥ! ኩራት እራቱ! ከአረባባ ግልድም ሙልጭ ያለ ቂ . . . ይሻላል! ከማን አንሼ!. . . ወዘተ እየተባልንና እያልን ነው እኛ ኢትዮጵያውያን … [Read more...] about በክርስትና ላይ ጥናታዊ ምርምር ሲያደርግ የነበረው ሰው በራሱ ሕይወት ላይ ምርመራ ተደርጎበት እጁን ሰጠ!!!
የገዢዎቻችን መጨረሻና የተከተላቸው ሀቅ
የመጨረሻውን በማያውቁት ያዘቀዘቀ ጨለማ መንገድ እየተውዘረዘጉ፤ መሪዉን በማስተካከል ከማያውቁት መጨረሻ ለመድረስ የሚጣድፉ መሪዎች፤ የድንቁርና ኒሻን ይገባቸዋል። በፈጠሩት የራሳቸው የመኖሪያ የገዢነት መኮፈሻ “ሀቅ” ተጀንነው በመቀመጥ፤ ፈንጠር ብሎ ርቆ ሌላውን ማየት ባለመቻላቸው፤ የተከተላቸውን ሳይውቁት እጃቸውን ሠጥተዋል። የተለዬ የመሰለ የራስ “ሀቅ” የብዥታ ጭጋግ፤ ሩቅ ማየትን ነፈጋቸው። ማስተዋልን ከአእምሮ መዝገባቸው ሰወረው። መደናበርን አነገሠባቸው። ካይናቸው ፊት በተገተረው የእብሪታቸው መነፅር፤ ዓለምን ግቢ ውጪ እያሉ በማስገደድ፤ ያለው የሌለ ሆኖ፣ ከተጨባጩ ይልቅ በምኞታቸው ዓለም ሲዳክሩ፤ የቆሙበት መሬት ከዳቸው። ከሕዝቡ መሆናቸው ቀርቶ ሕዝቡ የነሱ አገልጋይ ሎሌ ሆነና፤ የነሱ መኖሪያና የሕዝቡ መኖሪያ በአጥር ተለያዬ። መኖሪያቸው ዓለማቸው ሆነና ከሕዝቡ ዓለም ወጡ። ረጋ … [Read more...] about የገዢዎቻችን መጨረሻና የተከተላቸው ሀቅ
የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ አሳሳች መረጃዎችና የተምታታ አስተያየት
በመሠረቱ ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ስለ አብዮቱ “ እኛና አብዮቱ “ የሚል መጸሐፍ ጻፉ የሚል ዜና ስሰማ ፣ መጸሐፋቸው እንደ ሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያም መጸሐፍ በቅጥፈት የተሞላ አይሆንም ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር ፡፡ ግን ሳይሆን ቀረ፡፡ በነገራችን ላይ የሻምበሉን መጸሐፍ ገና አላገኘሁትም፣ ነገር ግን አንድ ወዳጄ ከምዕራፍ 13–16 ያሉትን ገጾች ፎቶ ኮፒ አድርጎ ስለሠጠኝ አየተገረምኩኝ አነበብኳቸው፡፡ ሻምበሉን ምን ነካቸው ብዬም እራሴን ጠየኩኝ፡፡ ደራሲው በትምህርታቸው እንዳልገፉ ይገባኛል ፡፡ ሆኖም ግን በትምህርት ያለመግፋት ትንታኔ ላይ ችግር ይፈጥር እንደሆን እንጂ ፤ “ በእጅ የገባን መረጃ ” አሳስቶ ማቅረብ ከምን ሊመነጭ እንደሚችል ፈጽሞ ሊገባኝ አይችልም፡፡ ፍቅረሥላሴ መረጃው በእጃቸው ከሌላቸው አርፈው መቀመጥ አለባቸው እንጂ ባልሆነ ማስረጃ አንባቢን ማሳሳት … [Read more...] about የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ አሳሳች መረጃዎችና የተምታታ አስተያየት
በኢንቨስትመንት ስም አፍሪካ ውስጥ የሚደረገውን የመሬት ቅርምት አስመልክቶ
Coalition for Equitable Land Acquisitions and Development in Africa በምህጻረ ቃል CELADA በመባል የሚታወቀው በካናዳ ኦታዋ ውስጥ የተቋቋመ ድርጅት በአፍሪካ እየተኪያሄደ ያለውን የመሬት ቅርምት አስመልክቶ በርካታ የፓርላማ አባላት፣ የተራድኦ ድርጅት ሃላፊዎች የዩኒቨርሲቲ መምህራን በተገኙበት በአፍሪካ በኢንቨስትመንት ስም የሚደረገውን የመሬት ቅርምትና ካናዳ ልትይዘው የሚገባትን ፖሊሲ በተመለከተ በኦታዋ ፌብሩዋሪ 25 ቀን 2014 ዓም የተሳካ ስብሰባ አድርገዋል። በሚሊየን የሚቆጠሩ በእርሻ የሚተዳደሩ ማህበረሰቦችን አግባብ በሌለው ሁኔታ የማፈናቀሉ ሥራ እጅጉን ተጧጡፎ ያለው በተለይ በአፍሪካ በመሆኑ CELADA የተሰኘው ድርጅት ይህ ጉዳይ አለም አቀፍ ትኩረት ያገኝ ዘንድ የበኩሉን ለማድረግ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህ ድርጅት በተለያየ … [Read more...] about በኢንቨስትመንት ስም አፍሪካ ውስጥ የሚደረገውን የመሬት ቅርምት አስመልክቶ










