ከአመታት በፊት በአዲስ አበባችን ውቧ ቅዳሜን በውቧ አዲስ ነገር ጋዜጣ በምናጣጥመበት ግዜ አንድ በጣም የማከብረው አምደኛ በኢትዮጲያ ስላለው የጋዜጠኝነትና የመፃፍ ነፃነት ያለው ቃል በቃል ባይሆንም በጥቅሉ ይህ ነበር፣ “ . . . በኢትዮጲያ የጋዜጠኝነት ሞያ በአግባቡ የተተገብረው እንዲሁም በነፃነት መፃፍና መተንተን የሚቻለው ስለ አውሮፓ እግር ኳስ በተለይም ስለ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት ነዳጅ ጨመረ ፖለቲካ ነው ፣ ነዳጅ ቀነሰም ፖለቲካ ነው ፣ ኑሮ ተወደደ ፖለቲካ ነው ፣ ታክሲ ጠፋ ፖለቲካ ነው ፣ ምርጫ ደረሰ ፖለቲካ ነው ፣ ሁሉ ነገር ፖለቲካ ነው። ታዲያ በጋዜጠኝነት የተመረቁ ፣ በፅሁፍና በትንተና የተካኑ ስለምን ይፃፉ ሰው መቼም ቋንቋ እያለው ሳያወራ ፣ ሳይፅፍ አይኖር . . . “ ይህ ፀሃፊ ያለው እውነቱን ነው አብዛኛው የሃገራችን … [Read more...] about መናገርና መፃፍ ወንጀል የሆነባት ሃገራችን
Opinions
የኔ ሃሳብ
የኦሮሞ ህዝብ ትግል ከጭቁን የአማራ ህዝብ ጋር ሳይሆን ከገዢው መደብና ከቀድሞው ሥርዓት ነፋቂዎች ጋራ ነው።
በአርዕስቱ ለመጥቀስ እንደሞከርኩኝ የኦሮሞ ህዝብ ትግል ከትውልድ ለትውልድ ሲተላለፍ የመጣው ከገዥዎችና ከረዳቶቻቸው የውጪ ኃይላት ጋር ነው። ይህ ህዝብ በነፍጥ አንጋቾች ቅኝ (አቅኝዎች) ሥር ከቀደቀበት ጊዜ አንስቶ አስከ ዛሬ ድረስ ትግሉን ያቁዋረጣበት ጊዜ የለም። ይህም የሆነበት ወቅት ብናስብ ሴሜቲኮች (ሓበሾች) ወደ ምስራቅ አፍሪካ ከመጡበት ጊዜ አንስቶ ነው። እነዚህ ህዝብ ወደ ምስራቅ አፍሪካ የመጡት በተለያየ ጊዜ ሲሆን፣ ሰበባቸውም የተላያየ ነው። ከመጡም በኃላ በኩሾች ንጉሥ (አባ ገዳ) “ኩሳ” በተባለ የሥልጣን ወይም የንግሥና ስም ስር በመተዳደር ነው። ቀስበቀ እየበረከቱ ሲሄዱ በተንኮልና በኃይል የነበረውን የኩሽ ህዝቦችን መስተዳድር ደምስሳው ሥልጣኑን ተቆጣጠሩ። የዛጉዌዎች ሥርወመንግስት መሃል ገብ እንጂ እስካሁን በሥልጣኑ ሲፈራረቁበት ቆዩ። እስኪ አቶ አምሳሉ ገ/ኪዳን … [Read more...] about የኦሮሞ ህዝብ ትግል ከጭቁን የአማራ ህዝብ ጋር ሳይሆን ከገዢው መደብና ከቀድሞው ሥርዓት ነፋቂዎች ጋራ ነው።
ኢህአዲግ/ወያኔ ሕዝብ ለማፋጀት የገነባውን “የመርዝ ብልቃጥ”
ኢትዮጵያን እየመራ የሚገኘው ኢህአዲግ/ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከቀን ወደ ቀን እርስ በርሱ እንዳይተማመን፣ እንዲነቃቀፍ፣ እንዲጠራጠር ከእዚህ ባለፈ ደግሞ ግጭት እንዲፈጠር እያደረገ 22 ዓመታትን ዘለቀ። ህዝቡ እለት ከእለት በገዢው መንግስት የሚወጠኑለትን የእርስ በርስ ማጋጫ ተንኮሎች እየተመለከተ ልቦናው በእጅጉ እየደማ ነው። አንድ ወራሪ የውጭ ጠላት ሊሰራ የሚችለውን ያህል ህዝብን ከሕዝብ ጋር የማጋጨት ሥራ ኢህአዲግ/ወያኔ በትክክል ሰርቶበታል። የሃገሪቱን ፌድራል አስተዳደር በየትኛውም ዓለም ያልታየ ቋንቋን መሰረት ያደረገ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ደገሰላት። ፌድራላዊ አስተዳደር በዘመናዊው ዓለም አንዱ እና አማራጭ የአስተዳደር ዘይቤ ይሁን እንጂ በየትኛውም ሀገር መሰረት የሚያደርገው የመልክዓ ምድርን አቀማመጥ እና ታሪካዊ አሰፋፈርን ነው። እርግጥ ነው ጣልያን ሀገራችንን በወረረ … [Read more...] about ኢህአዲግ/ወያኔ ሕዝብ ለማፋጀት የገነባውን “የመርዝ ብልቃጥ”
ወፈ ግዝት!
መግቢያ ወያኔ የማትሞክረው የለም። አንዳንዴ አቅሟን አታውቅም ልበል? በዚያን ሰሞን፣ ቺፍ ሳጂን ዘመድኩን የተባለ የወያኔ ጉደኛ የፖሊስ ባለጊዜ፣ የቮኤውን ጋዘጠኛ፣ ሰሎሞን ክፍሌን በስልክ ሲያስፈራራ፣ “ዋሺንግተን አይደለም፣ ሰማይ ቤት ብትሆን መጥቼ እወስድሀለሁ” ነበር ያለው[1]። የወያኔ ካድሬ ጉዶች፣ በለስ አንዴ ከቀናቸው፣ ሁሌ የሚቀናቸው ይመስላቸዋል። ከኢትዮጵያው ውጪም፣ የኢትጵያውያንን ሕልውና ለመቆጣጠር ያምራቸዋል። ሲያምራቸው ይቅር። ኢትዮጵያ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጽሙት ግፍ አንሶአቸው፣ ባህር ማዶም የቁጥጥራቸውን መረብ አሻግረው ለመዘርጋት የኢትዮጵያን ገንዘብ እንደ ጉድ ይረጩታል። ኬኒያና ጂቡቲ ቀንቶአቸው ይሆናል። እንግሊዝ ግን፣ ኬኒያም፣ ጂቡቲም አይደለችም። ሆድ-አደሮችን ወያኔ ትቆጣጠራቸው እንደሆን እንጂ ሌሎቻችን ዕምነታችንንም ሆነ መብታችንን አናስነካም። … [Read more...] about ወፈ ግዝት!
አምባገነናዊውን ስርዓት አቅፈውና ደግፈው የያዙት ምዕራባዊ አገራት
በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ጭቆና፣ ስቃይ እና መከራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ካደረጉት ምክንያቶች መካክል አንዱ፣ የወያኔ መንግስት ከምዕራባዊያን የሚያገኘው ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ሙገሳ ትልቅ ቦታ ይይዛል። ከነዚህ መንግስታት የሚያገኘው ድጋፍ እና ሙገሳ ምክንያት የማን አለብኝነት ስሜት ስርዓቱ እንዲሰማውና የኢዴሞክራሲያዊ ስርዓት በህዝቡ ላይ እንዲንያሰራፉ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ስርዓቱም ከነችግሩ ለረዥም ጊዜ በስልጣን እንዲቆይ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የምዕራባዊያን ድጋፍ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። እነዚህ ሀገራት የራሳቸውን ብሄራዊ ጥቅም ብቻ ትኩረት በመስጠታቸው ላለፉት 25 ዓመታት የኢትዮጵያ ህዝብ በጭቆና ውስጥ እንዲያሳልፍ አድረገውታል። የሀገሪቱ መልካምድር\ጅኦግራፍያዊ አቀማመጥ፣ የመንግስት ለምዕራባዊያን ፍላጎት አጎብዳጅነት እና … [Read more...] about አምባገነናዊውን ስርዓት አቅፈውና ደግፈው የያዙት ምዕራባዊ አገራት
የሰላማዊ ሰልፍ መንፈስ መመለስ
በበርካታ ኢትዮጲያዊያን ትውስታ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ሲባል ወደ አእምሮአቸው የሚመጣው በምርጫ 97 ሰሞን የነበሩት ህዝባዊ የመብት ጥያቄዎች ናቸው። በወቅቱም ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው ከአሁን በውሃላ ማንም ሰው አደለም ተሰልፎ ሰብሰብ ብሎም መቆም አይችልም ብለው ማስጠንቀቂያ በመስጠት ህዝቡን በየእስር ቤቶ ካጎሩት በውሃላ መብትን በሰልፍ የመጠየቅ ነገር በዛ በይስሙላ ህገ መንግስት ላይ ብቻ ተወስኖ በሰልፍ መብትን የማስከበር መንፈስም በእጅጉ ተቀዛቅዞ ነበር። እንደውም በአንድ ወቅት ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳን ከእስር መፈታት አስመልክቶ ለተጠራው ሰልፍ መንግስት ከሁለት መቶ ሃምሳ ሰው በላይ መሰለፍ አይፈቀድም የሚል ብዙዎችን በግርምት ያስደመመ ተሰምቶ የማያውቅ የሰላማዊ ሰልፍ ፍቃድ አሰጣጥ ሂደትንም አስተውለን ነበር። ምንም እንኳን በራሱ በወያኔ … [Read more...] about የሰላማዊ ሰልፍ መንፈስ መመለስ
ኢትዮጵያ ውስጥ የመገንጠል ጥያቄ ማንሳት ይቻላልን?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት በቅድሚያ ሀገር ማለት ራሱ ምን ማለት ነው? እንዴትስ ትፈጠራለች? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይኖርብናል፡፡ ሀገር ማለት በአንድ ጥላ ስር የሚኖርባት ትልቅ ቤት ማለት ናት፣ ሀገር ማለት ጋርዮሽ ማለት ናት፣ ሀገር ማለት ከመንደር ከቀየ የገዘፈች የጋራ ጥቅም የፈጠሩ ሕዝቦች የራሳችን የግላችን የሚሉት የተከለለ ምድርና በውስጡ ያሉ ሁሉ ነገሮች ማለት ናት፡፡ ሀገር እንዴት ትፈጠራለች? ሀገር በሦስት መንገድ ትፈጠራለች የተለያየ ቋንቋ ባሕል ሃይማኖት ወዘተ ያላቸው ሕዝቦች በመልክአ ምድር አቀማመጥ በአየር ንብረት መመሳሰልና ተጽዕኖ ሊጋሩት በሚፈልጉት ወይም በሚገደዱት የተፈጥሮ ሀብት አጣማሪነት በስምምነት ትፈጠራለች፡፡ የጋራ ጥቅም ባላቸው ወይም በፈጠሩ አንድ ዓይነት ቋንቋ ባሕል ሃይማኖት ወዘተ ባለው ሕዝብ ያንን የጋራ ጥቅም ለራሳቸው ብቻ … [Read more...] about ኢትዮጵያ ውስጥ የመገንጠል ጥያቄ ማንሳት ይቻላልን?
Open Letter to Italian Minister of Foreign Affairs
Ufficio Relazioni con il Pubblico The Honorable Minister of Foreign Affairs, Federica Mogherini Ministero Affari Esteri Piazzale della Farnesina, 00135 Roma ITALY Your Excellency: The Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause presents its compliments to the Honorable Foreign Minister of Italy, Federica Mogherini. Our Alliance recalls, with deep appreciation, the long and historic relations between our two nations, Ethiopia and Italy, and wishes to draw Your Excellency’s kind … [Read more...] about Open Letter to Italian Minister of Foreign Affairs
ዲፕሎማቱ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ት/ቤትን ተቆጣጠሩ
ከ1500 በላይ በሆኑ ወላጆች በባለቤትነት እንደሚተዳደር የሚታወቀው በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት በዲፕሎማቱ ቁጥጠር ስር መዋሉን የሚገልጹ ምንጮች ማርች 28 2014 በኤምባሲው ደብዳቤ የስብሰባ ጥሪ ተላልፎላቸው የነበሩ ወላጆች ባለመገኝታቸው የስብሰባው አዳራሽ ባዶ ሁኖ መዋሉን አክለው ገልጸዋል። ንብረትነቱ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር እንደነበር የሚነገርለትን ት/ቤት ኤምባሲው ለመቆጣጠር እያደረገ ያለው ጥረት ከግል ጥቀም የመነጨ መሆኑንን የሚናገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ት/ቤቱን ከኮሚኒቲው በመነጠል ከወላጆች በሚመረጥ የቦርድ አስተዳደር ይመራል በሚል ሽፋን ላለፉት 5 አመታት በት/ቤቱ ጥሬ ገዝንዘብ ላይ ግልጽ የሆነ ምዝበራ መፈጸሙን ይናገራሉ። ይህን አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ዲፕሎማቱ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ያልፈነቀሉት ድንጋይ ያልበጠሱት ቀጠል … [Read more...] about ዲፕሎማቱ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ት/ቤትን ተቆጣጠሩ
አባ ፋኑኤል አዲስ ተክል ናቸው
“ወኢይኩን ተክለ ሐዲሰ ከመ ኢይትዐበይ ወኢይደቅ ውስተ ፍትሀ ዲያብሎስ። (፩ኛ ጢ ፫፡፮) የክርስቶስን ትህትና ጠልቆ ያልተረዳ ክርስቲያን በዲያብሎስ ትእቢት ይሸነፋልና በመንፈሳዊ አመራር ላይ አታስቀምጥ።” አዲስ ተክል ማለት አዲስ ገና ያልበሰለ አማኝ ማለት ነው። መግቢያ አባ ፋኑኤል ባዲስ ተክልነታቸው ነቢዩ ኢሳይያስ ስለ ጾም ከተናገረበት ምዕራፍ አንዲትን ሀረግ በጥሰው፤ በምእመናን እና በሶስት ቀሳውስት በቀድሞው ቄስ ታደሰ ሲሳይ ላይ የተላለፈውን ቃለ ውግዘት በቀላጤ ለማንሳት ባደረጉት ሙከራ “የከሳሾች ካህናት ጥላቻ ችግርና አለማመን ከዚህ ላይ ይጀምራል” በማለት የጻፉት ወረቀት ህዝቡን እንዳያደናብር ይህችን ጽሁፍ በማዘጃገት ላይ ሳለሁ፤ ይሄይስ አእምሮ የተባሉ ወገን “የሃይማኖት እርጅና አያድርስ” በሚል ርእስ March 9/ 20014 የጻፏትን መልእክት ሁለት ወዳጆቼ ላኩልኝ። … [Read more...] about አባ ፋኑኤል አዲስ ተክል ናቸው








