“ወኢይኩን ተክለ ሐዲሰ ከመ ኢይትዐበይ ወኢይደቅ ውስተ ፍትሀ ዲያብሎስ። (፩ኛ ጢ ፫፡፮) የክርስቶስን ትህትና ጠልቆ ያልተረዳ ክርስቲያን በዲያብሎስ ትእቢት ይሸነፋልና በመንፈሳዊ አመራር ላይ አታስቀምጥ።” አዲስ ተክል ማለት አዲስ ገና ያልበሰለ አማኝ ማለት ነው።
መግቢያ
አባ ፋኑኤል ባዲስ ተክልነታቸው ነቢዩ ኢሳይያስ ስለ ጾም ከተናገረበት ምዕራፍ አንዲትን ሀረግ በጥሰው፤ በምእመናን እና በሶስት ቀሳውስት በቀድሞው ቄስ ታደሰ ሲሳይ ላይ የተላለፈውን ቃለ ውግዘት በቀላጤ ለማንሳት ባደረጉት ሙከራ “የከሳሾች ካህናት ጥላቻ ችግርና አለማመን ከዚህ ላይ ይጀምራል” በማለት የጻፉት ወረቀት ህዝቡን እንዳያደናብር ይህችን ጽሁፍ በማዘጃገት ላይ ሳለሁ፤ ይሄይስ አእምሮ የተባሉ ወገን “የሃይማኖት እርጅና አያድርስ” በሚል ርእስ March 9/ 20014 የጻፏትን መልእክት ሁለት ወዳጆቼ ላኩልኝ። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
Leave a Reply