• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አምባገነናዊውን ስርዓት አቅፈውና ደግፈው የያዙት ምዕራባዊ አገራት

March 30, 2014 05:57 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ጭቆና፣ ስቃይ እና መከራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ካደረጉት ምክንያቶች መካክል አንዱ፣ የወያኔ መንግስት ከምዕራባዊያን የሚያገኘው ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ሙገሳ ትልቅ ቦታ ይይዛል። ከነዚህ መንግስታት የሚያገኘው ድጋፍ እና ሙገሳ ምክንያት የማን አለብኝነት ስሜት ስርዓቱ እንዲሰማውና የኢዴሞክራሲያዊ ስርዓት በህዝቡ ላይ እንዲንያሰራፉ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ስርዓቱም ከነችግሩ ለረዥም ጊዜ በስልጣን እንዲቆይ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የምዕራባዊያን ድጋፍ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። እነዚህ ሀገራት የራሳቸውን ብሄራዊ ጥቅም ብቻ ትኩረት በመስጠታቸው ላለፉት 25 ዓመታት የኢትዮጵያ ህዝብ በጭቆና ውስጥ እንዲያሳልፍ አድረገውታል። የሀገሪቱ መልካምድር\ጅኦግራፍያዊ አቀማመጥ፣ የመንግስት ለምዕራባዊያን ፍላጎት አጎብዳጅነት እና ሃገሪቱ በአካባቢው ብሎም በአፍሪካ ፖለቲካ ያላት ማእከላዊ ስፍራ የለጋሽ ሀገራትን ትኩረት ሊስብ ችሏል። በዚህ ምክንያት ምዕራባዊያን የወያኔ ስርዓትን አቅፈውና ደግፈው በመያያዛቸው ህዝቡ ከዚህ አስከፊ ስርዓት ነጻ ለመውጣት የሚያደርገውን ትግል አስቸጋሪ አድርጎታል።

የወያኔ መንግስት በህዝብ ላይ እያደረሰ ካለው ዘርፈ ብዙ ወንጀሎች እና የስርዓቱ ልዩ መለያ ባህርያት መካከል በዋናነት፣ በሀይል ህዝቦችን ለዘመናት ከሚኖሩበት መሬት ማፈናቀል እና መሬታቸውንም በርካሽ በኢንቨስትመንት ስም መቸብቸብ፤ የጸረ-ሽብር ህግ በማውጣት የፖለቲካ አመራሮችን እና ጋዜጠኞችን ማፈን፤ ከፍተኛ ሙስና እነዲሁም ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በማስገባት የስልክ እና የኢንተርኔት ክትትል እና ጠለፋ ማድረግ ተጠቃሽ ናቸው። የምዕራባዊያን በወያኔ ላይ ያላቸው ቸልተኝነትና ለዘብተኛ አቋም መንግስት የማናለብኝነት ስሜት እንዲሰማውና በህዝብ ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃና ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ መጠኑና ስፋቱን እየጨመረ በመሄድ የሀገሪቱን ብሎም የአካባቢውን መጻይ ዕድል አሳሳቢ አድርጎታል።

ከምዕራባዊያን የሚገኝ እረዳታ በመጠቀም ብዙ የአፍሪካ መንግስታት አምባገነናዊ ስርዓትን በሰፊዊ የማጠናከራቸው ሁኔታ አዲስ ነገር አይደለም። ከሰሞኑም የወጣው የHuman Rights Watch ሪፖርት እንዳመለከተው መንግስት ህዝቡን እንዴት ጠፍንጎ እና ጨቁኖ እንደያዘው ምናልባት ለውጭ ማህበረሰብ አዲስ ነገር ሊመስል ቢችልም ለኢትዮጵያ ህዝብ ግን አዲስ አይደለም። በተለያዩ ወቅቶች የተቃዋሚ ሓይሎች፣ ጋዜጠኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ሲገልጹት የቆዩት ጉዳይ ነው። ነገር ግን እዚህ ላይ መጠቆም የሚገባን፤ ወቅታዊ ሪፖርቶችን በተከታታይ በማቅረብ፣ ሰፋ ያለ ማብራሪያና መረጃወችን የሚያቀርበውን የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት( Human Right Watch) ማመስገን ይገባናል።

ድርጅቱ ከጥቂት ድርጅቶች መካከል አምባገነናዊ ስርዓቶችን በማጋለጥ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው። በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን እንዲሁም የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ስለ ወያኔ ፍጹም አምባገነናዊ ስርዓት ሲነገር ቢቆይም ሰሞኑን የወጣው የ Human Rights Watch ሪፖርትም የዚህን ስርዓት አስከፊነትና ከምእራባዊያን ከሚያገኘው ዳጎስ ያለ የገንዘብ ድጋፍ ዘመናዊ የስለላና የክትትል ቴክኖሎጂዎችን በማስገባት ስርዓቱ ፍጹም አምባገነናዊ እንደሆን አመላክቷል። በረቀቀ እና ጊዜውን በጠበቁ ቴክኖሎጂዎች አማካኝነት መንግስት በህዝቡ ላይ እያደረጋ ባለው ጭቆና የምዕራባዊያን ሀገራት እና ድርጅቶች በተዘዋዋሪ ተሳታፊና ተባባሪ አድርጓቸዋል። በመሆኑም የ Human Rights Watch ሪፖርት እንደሚያመልክተው የምዕራባዊያን የቴክኖሎጂ ድርጅቶች ለጨቋኝ ስርዓት ተባባሪ በመሆናቸው ሊጠየቁ እንደሚገባ በማሳሰብ ቴክኖሎጂውን የሚያቀርቡ፣ የሚሸጡ፣ እና አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች የቴክኖሎጂ ውጤታቸው ለሰብዓዊ መብት ጥሰት ተግባር በተደጋጋሚ ክስ የሚቀርብባቸው እንደ ኢትዮጵያ መንግስት ላሉ መንግስታት ጥቅም ላይ እንዳይውሉ መቆጣጠር እንዳለባቸው ይጠቁማል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከተለያዩ ለጋሽ አገራት በአመት ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ በውጭ እርዳታ መልክ ድጋፍ ያገኛል። ይህ ከፍተኛ ድጋፍ በአግባቡ ለልማት ቢውል በደሃው ህብረተሰብ የኑሮ ሁኔታ ላይ የሚያመጣው ለውጥ ቀላል አይደለም። ነገር ግን አምባገነናዊው መንግስት ለፖለቲካ ፍጆታ ከመጠቀም አልፎ ህዝቡን ለማፈን፣ ለመጨቆን እና ለመሰለል እንዲረዳው ዘመናዊ እና የረቀቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለማስገባት ይህን ድጋፍ ያውለዋል። ድጋፉን ለሚሰጡት ምዕራባዊያን ግን ይህ ድርጊት ከእይታቸው የተሰወረ አይደለም።የ Human Right Watch እና የተላያዩ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት ጋዜጠኞች፣ ዳኞች፣ ምሁራን፣ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ታስረዋል፣ ተገርፈዋል፣ ተሰደዋል። እነዚህንም መረጃዎች ለጋሽ አገራት አንብበዋል፤ የጉዳዩንም ክብደት ከማንም በተሻለ ሁኔታ ያውቃሉ። ነገር ግን ምዕራባዊያን በጉዳዮ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር ለዘብተኛ መሆናቸው ሳያንስ በአሳፋሪ ሁኔታ ጉዳዩን አይተው እንዳላዩ በመሆንና የመንግስትን ፕሮፖጋንዳ ተቀብለው በማቀንቀን የበሰበሰው ስርዓት በህዝቡ ላይ እንዲንሰራፋ አድረጎታል።

በተጨማሪም ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር በህይወት እያሉ የምዕራባዊያንን ፍላጎት በማስቀደም በሰላ ምላሳቸው የምዕራባዊያንን ቀልብ መሳብና ማማለል ችለው ነበር። የለጋሽ ድርጅቶች ቡድን (The Donors Assistance Group) እንደሚያመለክተው የወያኔ መንግስትን በተመለከተ በተከታታይ የሚወጡትን ሪፖርቶች መርምሮ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ጉዳዩን ወደጎን በመተው ምንም እንዳልተፈጠረ በመቁጠር የለት ተለት ተግባራቸውን መቀጠል እንደሚመርጡ አመልክቷል። ከዚህ በፊት ካለን ልምድ እንደምንረዳው ለጋሽ ድርጅቶች ወይም ሀገራት ከወያኔ መንግስት ጋር ፊት ለፉት ከመላተም ይልቅ ከገለልተኛ ወገኖች እንደ ከ Human Right Watch የሚወጡ ሪፖረቶችን ውድቅ ማድረግን ይመረጣሉ። ከተቻለም የራሳቸውን ሪፖርት በማዘጋጀት በመንግስት ላይ የሚቀርበውን ውንጀላ የሚያጠናክር መረጃ እንዳላገኙ በመግለጽ ጉዳዩን ያለዝባሉ ወይም ከገለልተኝ ወገኖች የሚወጡ ሪፖረቶች የተፋለስ ድምዳሜ እንዳላቸው በመጥቀስ መሬት ያልያዙና እውነታውን እንደማያሳይ ማመልከት ይመርጣሉ። ይህ ሁኔታ እነዚህ የውጭ ሀገራትና ድርጅቶች ምን ያህል ለሰፊው ህዝብ መብት እና ጥቅም ደንታ እንደሌላቸው ያመላክታል።

የምዕራባዊያን ከአምባገነናዊ ስርዓት ጋር ያላቸው አጋርነት እና ቁርኝት በኢትዮጵያ ወይም በአፍሪካ ብቻ የተወሰነ ክስተት ሳይሆን በተለያዩ አገሮችም የሚስተዋል ነው። ምዕራባዊያን ለምን ይህን ድጋፍ እንደሚያደረጉ ሲገልጹ፤ እረዳታ መስጠት ብናቆም ዞሮ ዞሮ ተጎጂው ድሃው ህብረተሰብ ስለሆነ ያለው ብቸኛ አማራጭ ባለው ስርዓት አማካኝነት እርዳታ መስጠቱን መቀጠል እንደሚመረጡ ይናገራሉ። ይህ አስተሳሰብ ለጋሽ ሀገራት ለሰብአዊ መብት ክብር እና ለዴሞክራሲያዊ እሴቶች ባይተዋር እንደሆኑ ያሳያል። ለሚሰጡት እርዳታ ቁጥጥርና ክትትል ተአማኒነትና ግልጽ ያሰራር ስርዓት በመዘርጋት የሚሰጡትን ገንዘብ ላልተፈለገ አላማና ፍጆታ ሲውል  እርዳታውን ማቆም የሚቻልበትን መንገድ የሚጠፋቸው አይመስለንም።

መንግስትም ማንኛውንም አማራጮች የሚዘጋ ከሆነም ከነጭራሹ እረዳታውን በማቆም ጠንከር ያለ ተጽዕኖ መፍጠር ይችሉ ነበር። እረዳታ ብናቆም ደሃዉ ህብረተሰብ ይጎዳል የሚባለው ምክንያት አጥጋቢ መነሻ ሊሆን አይችልም፤ ምክንያቱም በመጀመሪያ ደረጃ ህብረተሰቡ ከእርዳታው ተጠቃሚ እየሆነ አይደለምና። ስለሆነም ማነኛውም ምዕራባዊ አገር ለአምባገነናዊ መንግስት የሚሰጡትን እርዳታ ለማቆም ዝግጁ ባለመሆናቸው የሚሰጡት የገንዘብ ድጋፍ አላማውን ስቶ በተቃራኒው ንጹሃንን ህዝቦች ለማፈን እና ለመጨቆን ትልቅ መሳሪ እንደሆነ ሊረዱ ይገባል።

ጸሃፊውን ለማግኘት ከፈለጉ eyobekebede1@gmail.com ይጠቀሙ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule