"ጀሃዳዊ ሐረካት" ዘጋቢ ፊልም "በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ከሃሳብ ያለፈ እቅድ አላቸው" የተባሉት ተጠርጣሪ አሸባሪዎችን ገመና አንጠርጥሮ ሊያሳየን መሆኑን ሞቀ ደመቅ ደመቅመቅ ያለው የኢቲቪ ማስታወቂያ ልባችን አንጠልጥሎት ከርሟል ። ሳምንት በደመጽና በምስል በለፈፉትና በናኙት ማስታወቂያ የሙሰሊማን የመፍትሄ አፈላላጊ ኰሚቴ አባላት "አሸባሪ" አካሄድ በተጨባጭ መረጃ እንደሚያሳዩን የነገሩን የመንግሰት መገናኛ ብዙሃንን የተለመደ ስራ የማውቀው ሳይቀር ነፈሴ በአንገቴ እሰክትወጣ ጉጉት አሳድሮብኛል። ይህ መሰሉ ስሜት ለጊዜው ምንጩ ከየት እንደሆነ ባውቀውም ስሜቴን ተቆጣጥሬ በሰአቱ ደረስኩ፡፡ ተመሳሳይ ስሜት አድሮባቸው እንደሁ በሚል እዚህ ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውንን እየደወልኩ ስሜታቸውን መጠየቅ ያዝኩ! (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል):: ጸሐፊውን በዚህ አድራሻ ማግኘት … [Read more...] about የ“ጃሃዳዊ ሐረካት” ዘጋቢ ፊልም መዘዝ!
Opinions
የኔ ሃሳብ
ለ ሃገር ሰው፣ የ“መድሃነ፥ኢትዮጵያ” ደወል፣ እውነቱም ይሰማ!
እስከመቼ እውነቱ ሳይወጣ ሊቀር ነው? ሆዱ እያረረ በብዙው ዘንድ መወለድ አቅቶት የሚጉላላው እውነት ምንድን ነው? አዎ! "እያንዳንዱን የዛሬውን የኢትየጵያ ሃገር ወዳድ ሊያሳስበው ብቻ ሳይሆን፣ ራሱን አስይዞ የሃሳብ ያለህ አሰኝቶ ሊያስጮኽው የሚገባው“፣ አፍጥጦ የመጣው አደጋ ምንድን ነው? እውነቱ ነገ ዛሬ ሳይባል ባደባባይ ተሰምቶ የእርቅ ዘመን ካልወረደ ፣ ከገባንበት ጭቃ ሳንወጣ ክፉዎች የደገሱልን ማጥ ውስጥ ሰጥመን እንቀራለን። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ለ ሃገር ሰው፣ የ“መድሃነ፥ኢትዮጵያ” ደወል፣ እውነቱም ይሰማ!
ልዩነት አያስፈራም
ባለፉት 21 ዓመታት በልዩነት ላይ የተመሰረተው፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የተነዛው የዘረኝነት መርዝ ቀላል አይደለም። መላ ኢትዮጵያን ቀስ በቀስ እየወረረው መጥቶ ማሰብ ይችላል ተብሎ የሚጠበቅበትን፣ ጥቂት ያልሆነ "ምሁር" የሚባለውን ሁሉ ሳይቀር በነጻ ጭንቅላት እንዳያስብ እያደረገው ነው። ሰለሆነም ነው፣ ማሰብ የሚገባው እንደዚህ ካሰባ፣ የፖለቲካና የስለላ ማዕከሎች ጥናቶች፣ አልፈው ተርፈው ረዥም ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያ ሃገራችንን ከእንግዲህ በሃያ ዓመታት ውስጥ ከሚወድቁት መንግስታት ተርታ ውስጥ ያስገቧት። ይህ መቼም፣ ሆነም አልሆነም፣ እራሱ መገመቱ እንኳን፣ እያንዳንዱን የዛሬውን የኢትየጵያ ሃገር ወዳድ ሊያሳስበው ብቻ ሳይሆን፣ ራሱን አስይዞ የሃሳብ ያለህ አሰኝቶ ሊያስጮኽው ይገባል። ደግሞም የመንግሥትንና የአባሪዋቹን ታሪካዊ አካሄድና ዛሬ የሚወስዱትን ኢትዮጵያን የማፈራረስ እርምጃዎች … [Read more...] about ልዩነት አያስፈራም
በ “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”
ከዝግጅት ክፍሉ፤ መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ በሚል ርዕስ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ባሳተሙት መጽሐፍ ላይ አቶ ዳንኤል ክብረት የራሳቸውን አስተያየት የሰጡ ሲሆን ይህንንም አስተያየት ተከትሎ ፕ/ር መስፍን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ሁለቱንም አስተያየቶች እንደሚከተለው አቅርበናቸዋል፡፡ መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ በዳንኤል ክብረት ከጥቂት ቀናት በፊት ታዋቂው ምሁር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ‹መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ› በሚል ርእስ አንድ አነጋጋሪ፣ አከራካሪና አመራማሪ መጽሐፍ አውጥተዋል፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ሃሳባቸውን በአደባባይ፣ ሕዝብ በሚረዳው መንገድና ቋንቋ ከሚገልጡ ጥቂት ኢትዮጵያውያን ልሂቃን አንዱ ናቸው፡፡ በሦስት የመንግሥት ሥርዓት ፕሮፌሰር መስፍን ሃሳባቸውን ሲገልጡ፣ ሲጽፉ፣ ሲከራከሩና፣ መልካም የመሰላቸውን ሁሉ ለሕዝብ ሲያቀርቡና ሲሞግቱ የኖሩ የአደባባይ … [Read more...] about በ “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”
ለ “የጣመ ውይይት” ምላሽ
"እኛ የመጨረሻዎቹ" የሚል አንድ ጽሁፍ በድረ ገጾች የሚሽከረከር አይቼ፣ እውን እንዴት ቀን ቀንን ዓመት ዓመትን እየተካው ዓለም ምንኛ በተጨባጭ በግብርም፣ በሃሳብ በመንፈስም እንደተሽከረከረች እንደገና ልብ ብዬ ነበር። እኔም የትላንት ሰው ስለሆንኩ። ነገር ግን እዚህ የውይይት መድረክ ውስጥ ሰገባ፣ የሃገሬ ልጆች አሁንም የዛሬ ሰላሳ ዓመት የፖለቲካ ቡድኖች የተከራከሩበትን፣ የተናቆሩበትን፣ ከዚያም ብዙ መዘዝና መዓት ሃገራችን የገባችበትን የፖለቲካ ልዩነቶችና ነጥቦች (ለምሳሌ የትጥቅ ትግል ዛሬ ያስፈልጋል፣ አያስፈልግም፣ ወይንም ግንባር፣ አንድነት፣ ወዘተ) አንስተው ዛሬም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሲከራከሩበት ስሰማና ሳነብ፣ ጉድ ነው፣ ዛሬም እዛው የዛሬ ሰላሳ ዓመት ከገባንበት ጭቃ፣ ይቅርታ ይደረግልኝና፣ አልወጣንም ማለት ተገደድሁ። ስለሆነም ዝርዝር ውስጥ ገብቼ እንዲህ ቢሆን እንዲህ … [Read more...] about ለ “የጣመ ውይይት” ምላሽ
እግርኳሳችን የራሷን ሙሴ ትፈልጋለች
ስሜት ጎርፍ ነው፤ ያውም ደራሽ ጎርፍ፤ ብሄራዊ ቡድናችንን ስንደግፍም ሆነ ስናወድስ እንዲሁም ስንወቅስ በዚሁ ደራሽ ጎርፍ መወሰዳችን ይታያል። ይሄ ችግር ግን እንደ ሃገርም ችግራችን እየሆነ የመጣ ነገር ነው በስሜት መደገፍ በስሜት መቃወም፤ ዛሬ ያወደሱትን ነገ መርግም ሁሉንም ነገር በዘላቂ ጥቅም፤ በዘላቂ ስራ እና በዕውቀት መመዘን እያቃተን ነው። ከዚያም ዐልፎ ስሜታችን ጫፍ ላይ በሚደርስበት ጊዜ ሰከን ብሎ የሚያስብ ሰው ሲያጋጥመን እንደጭራቅ እንመለከተዋለን። ከእኛ በሓሳብ የተለየ አስተያየት የሰጠ እንደሆነማ በቃ ቤተክርስቲያን ውስጥ የገባ ውሻ እናደርገዋለን።… የሰሞኑ የብሄራዊ ቡድናችን ውጤትም የዚህ ጎርፍ ሰለባዎች መሆናችን አንዱ ማሳያ ነው። መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲስ አበባ ከቤኒን ብሄራዊ ቡድን ጋር ሲጫወት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የአሰላለፍ ስህተት … [Read more...] about እግርኳሳችን የራሷን ሙሴ ትፈልጋለች
የጣመው ውይይት ፍሬያማ እንዲሆን ምን ይደረግ?
በእኔና በአቶ አንዱ አለም ተፈራ መካከል እየተደረገ ያለው ውይይት እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል:: እየተወያየን ያለንው የጋራ ስለሆነችው አገራችን የወደፊት የፖለቲካ ዕድገትና ሁለንተናዊ ለውጥ መምጣት ስለምንችልበትና አሁን ላሉብን ፖለቲካዊ ችግሮች ሊፈቱበት ስለሚገባቸው አግባብ ዙሪያ ነው:: ይህም፣ የተለያዩ ሃሳቦች መንሸራሸርንና ጠንካራ የሃሳብ ፍጭትን የሚጠይቅ ነው:: ለዚህም፣ የሌሎች ተሳትፎ ወሳኝ ነው:: ይሄኛው ምላሼ ትንሽ ዘግየት ብሏል:: አንድም የተወሰኑ ቀናትን ከቤቴ ውጭ ለስራ ጉዳይ በማሳለፌ፤ ሁለተኛም እስኬ ሌሎች እንዲሳተፉ ጊዜ ለመስጥ፤ ሶስተኛም በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ የማቀረበውን ጥናታዊ ጹሁፍ ለማጠናቀርና ለመጨረስ ስሯሯጥ ስለነበር ነው:: መቼም አቶ አንዱ አለም ይረዱኛል ብዬ ተስፋ አረጋለው:: በምናረገው ውይይት ውስጥ “ያልተግባባንበት ጉዳይ ሁለታችንም አንድ … [Read more...] about የጣመው ውይይት ፍሬያማ እንዲሆን ምን ይደረግ?
Hello Arsne Wenger, are you watching me?
Meet the young man who with less than 30 minutes on the field of play set the prestigious AFCON 2013 soccer extravaganza alight. As his name continue to resonate in South Africa, and surely ... (read more) … [Read more...] about Hello Arsne Wenger, are you watching me?
Beautiful soccer by the most beautiful Ethiopians!
“Who said Africa cannot play like Barcelona? This Ethiopian team is Africa’s Barcelona.” Sunday Olisey, Nigerian foot ball legend. “Today Ethiopians have showed the world that African foot ball is on the rise” Mark Fish, South African foot ball legend. (Read more) … [Read more...] about Beautiful soccer by the most beautiful Ethiopians!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ግጥሚያና ሁኔታዬ
የእግር ኳስ ጨዋታ ለኢትዮጵያዊያን ከረጅም ርቀት ሩጫ ውድደር ጋር ከፍተኛ ቦታ የያዘ ነው። በእድሜያችን ገፋ ላልነው፤ የነመንግሥቱ ወርቁ የኳስ ጥበብ፤ የኢታሎና ሊቻኖ . . . ኧረ ስንቱን በትዝታ ዓለም መጎብኘት ይቻላል። ብቻ ለሁሉም ያንን እንዳስታውስ ያደረገኝ፤ በዛሬው ዕለት ከቤቴ ተቀምጨ ያየሁት የኢትዮጵያ ቡድንና የዛምቢያ ቡድን ጨዋታ ነው። ቡድናችንን በሀገራችን ካለው ዘረኛ አገዛዝ ነፃ አውጥቶ ለብቻው ማየት መቻል ከባድ ነው። ነገር ግን አደረግነው። ስንደቅ ዓላማችንን እንኳ በመሐከሉ ላይ ያስቀመጠውን ጉድፍ ረሳነው። የዘረኛውን የስንደቅ ዓላማ ጉድፍ ለዚች ቀን ከሰንደቅ ዓላማችን ላይ ተሰቅሎ ሲውለበለብ ዝም ብለን ዓየን፤ ትኩረታችን በተጫዋቾቻችን ላይ ነበርና። ከጎኔ ሆነው የባራክ ኦባማን የፕሬዘዳንትነት ምርጫ ስነ ሥርዓት እያዩ ሲጯጯሁብኝ፤ ኮምፒውተሬን ይዤ ክፍሉን … [Read more...] about የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ግጥሚያና ሁኔታዬ