• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ!

February 24, 2023 08:19 am by Editor Leave a Comment

ስሙ የክህደት መጠሪያ ሆነ እንጂ የስሙ ትርጉም ግሩም ነው። ይሁዳ የሚለው ቃል በእብራይስጥም “ይሁዳ” ማለት ነው፤ “ያዳ” ነው ሥርወ ቃሉ ይላሉ የሙያው ባለቤቶች። ይህ ደግሞ ትርጉሙ “ማመስገን” ማለት ነው። በግሪክም ትርጓሜው ተመሳሳይ ነው – “የተመሰገነ”፣ “ምስጉን” ማለት ነው። 

“የአስቆሮቱ” የሚለው ቃል ደግሞ የክፋት መጠሪያ አይደለም። በተለምዶ “የአስቆሮቱ ይሁዳ” በማለት ከሃዲዎችን ስንጠራቸው “አስቆሮቱ” የይሁዳ የክፋት ማዕረግ ይመስለናል። ሊቃውንቱ እንደሚሉን ከሆነ ትርጉሙ “የኬሪዮት ሰው” ወይም “የአራዳ ልጅ” እንደ ማለት ነው ይላሉ። ስለዚህ በከሃዲነቱ ባናውቀው ኖሮ “ተመስገን ያራዳ ልጅ” ብለን እንጠራው ነበር። ስሙ ግን ከግብሩ ፍጹም የራቀ ነው፤ እንዲያውም ተጻራሪ።

ይሁዳ ከሃዲ ብቻ አይደለም፤ ማሳካት የሚፈልገው ዓላማ ያለውና የሚያደርገውን ጠንቅቆ የሚያውቅ ነበር። ከመድኃኒዓለም ጋር አብሮ ለሦስት ዓመት ተኩል ቆይቷል፤ የጌታችንን አስተዳደርና አመራር ውስጠ ምሥጢሩን በደንብ አጥንቷል። “ሐዋርያ” ተብሎ ተጠርቷል። ሁለት፣ ሁለት ተደርገው ሲላኩ እርሱም ሁለት ጊዜ ተልኳል። አጋንንት አውጥቷል፣ ተዓምራት ሠርቷል፤ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንሰሐ ግቡ” እያለ ወንጌልን ሰብኳል!

ይሁዳ ሲነቅፍ በጭፍን አይደለም፤ ረቂቅ ነው። አዛኝና ርኅሩኅ ምስኪን ሆኖ ነው እንጂ በፈጣጣው አይደለም። ማርያም መግደላዊት እጅግ ውድ የሆነ ሽቶ በጌታችን እግር ላይ ስታፈስ “ይህ ተሸጦ ድሆችን መመገብ ይቻል ነበር” ያለው እንጂ በጭፍን አልተቃወመም። መጽሐፍ ግን ይህንን ያለው “ሌባ ስለነበር ነው” ይላል።

መምህሩን የሸጠው ለገንዘብ ብቻ ብሎ አይደለም። ዓላማው ሌላ ሆኖ “ለምን ቢዝነስ አልሠራም” በሚል ገንዘቧ የጎንዮሽ ጥቅም ማስገኛ ነበረች። መድኃኒዓለም አሳልፎ ከተሰጠ አልያዝም በማለት ያምጻል፤ ከዚያም ያንን ሙታንን የሚስነሳውን ኃይል ተጠቅሞ ሮምን ድምጥማጧ ያጠፋል፤ ከዚያም መምህሩ በዳዊት ዙፋን ሲነግሥ “ለዚህ ነጻነት ያበቃኋችሁ እኔ ነኝ” ብሎ ይሁዳ የእልፍኝ አስከልካይ ወይም አፈ ንጉሥ ወይም የንጉሥ አማካሪ ወይም አንድ የሆነ ሥልጣን ላይ እደርሳለሁ ብሎ ነበር። ሁሉም ቀርቶ መጨረሻው ፍጹም የተለየ ሆነ!

የእኛ አገር ፖለቲከኞች፣ አክቲቪስቶች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎች የሚባሉት፣ ዩትዩበሮች፣ ወዘተ ከስማቸው ብንነሳ የብዙዎቹ ቤተሰብ ያወጣላቸው ስም በጣም ደስ የሚልና ጥሩ ትርጉም ያለው ነው። እንዲያውም ከመጽሐፍ ቅዱስ የተወሰደ ነው። አሁን አሁን ግን የአንዳንዶቹ ስም እንደ ይሁዳ ለልጆቻችን የማናወጣው እየሆነ የመጣ ይመስላል። እንደው እንደ ምሳሌ ብንጠቅስ ልጁን “ሕዝቅኤል፣ ኤርምያስ” ብሎ የሚሰይም ሁለት ጊዜ ማሰቡ አይቀሬ ነው። የሌሎቹ ስም እንኳን ከድህነት ለመላቀቅ፣ ከደጋፊ ዘመድ አልባ ብቸኝነት ለማምለጥ በሚል ለምኞት ማስታገሻነት የወጡ የአጥቢያ ስሞች ስለሆኑ ሳልጠቅስ ልለፋቸው።  

እነዚህ የአገራችን ይሁዳዎች እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ዓላማ ያላቸው ናቸው። በየቀኑ የሚያደርጉትን ጠንቅቀው ያውቃሉ፤ መዳረሻ አላቸው። በሥራቸው የሚላላኩላቸው ጉዳይ ፈጻሚዎችም አሏቸው። በየቀኑ እየበላሁ እንዴት ዝም እላለሁ እንደሚል ውሻ እየወጡ የሚጮኹ ናቸው። ብዙዎቹ በቅርብ ሆነው ምሥጢር በመጠኑ ያጠኑና ያወቁ ናቸው። ለውጡን ተከትሎ በየሚዲያው የለውጡን ወንጌል ውስጥ ካሉት ሰዎች በላይ ሲሰብኩ የነበሩ ናቸው። “የለውጥ ዘመን መጥቷልና ከዘመነ ኢህአዴግ አገዛዝ ንሰሐ ግቡ” እያሉ በየቀኑ ስብከተ ለውጥ ሲያሰሙ፣ ውዳሴ ሲያቀርቡ ነበሩ።

በኢህአዴግ ዘመን የፖለቲካ ዓይናቸው የታወረውን ያበሩ፣ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ልክፍት የተያዙን በወንጌለ ለውጥ እያናዘዙ ያስወጡ፤ ከለውጡ ሊቃነ ጳጳሳት በላይ የለውጥ ፋና ወጊዎች የነበሩ ናቸው። ከባሕር ማዶ የተመኙትና በርቀት የተሳለሙት ሹመት፣ አማካሪነት፣ ቪላ ቤት፣ ቪ8፣ … ቀቢጸ ተስፋ ሆኖ እንደ ጉም ሲተንንባቸው ኢትዮጵያን ለመስቀል 30 ብር ተቀብለው እንደ ይሁዳ ሥራቸውን በምሽት እየሠሩ ነው – የጨለማውን ሥራ! ይሁዳ መምህሩን አሳልፎ ለመስጠት በአንድነት ራት ይበሉ ከነበረበት ቤት ሲወጣ መጽሐፍ ሲናገር “ሌሊትም ነበር” ይላል። 

የዘመናችን ይሁዳዎች እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ለድሃ ሐዘነተኛ ሆኖ በመታየት የሚቀድማቸው የለም። ይሁዳ ሽቶው ተሸጦ ለድሆች ሊሰጥ ይችላል አለ እንጂ እኔ ለድሆች ልስጥ አላለም። እነዚህም እንዲሁ ናቸው። ሰው እየሞተ ዳቦ ቤት ለምን ይገነባል? ለዳቦ ቤት መገንቢያ የወጣውን ገንዘብ ለድሆች ብናከፋፍለው ለስንት ደሃ ሊደርስ ይችል ነበር? በማለት ይሁዳዊ አዛኝነታቸውን ያሰማሉ።

ኢትዮጵያ ስሟን ቀያሪ የሆነውን ተግባር ፈጸመች – ስንዴ ወደ ውጭ ላከች! ሲባል የስንዴ ዱቄት ከአገር ውስጥ ገበያ ጠፍቷል ይላሉ። ከዚህ በፊት ስንዴ ለመላክ እየሠራን ነው ሲባል ግን ምንም ትንፍሽ ሳይሉ የቆዩ ናቸው። ምናልባትም ስንዴው ለምርት አይደርስም ብለው ጠብቀው ይሆናል። ምርቱ መሰብሰብ ሲጀምር ግን በጦርነት እየታመሰች ያለችው ዩክሬይን ለኢትዮጵያ ስንዴ ላከች ብለው ነበር። የሚገርመው የእርዳታ እህል ተካለ ሳይሆን የተባለው “ስንዴ” በስም ተጠርቶ ነው ወሬው የተሰራጨው። መርከቧ በሶማሊያ የባሕር አደጋ ጣዮች ተዘረፈች እንዳንል እስካሁን ምንም የተሰማ ነገር የለም፤ መርከቧ ቀርታ “ስንዴው” ቢደርስ እንኳ ጥሩ ነበር።

ኢትዮጵያዊ ይሁዲዎቹ ከስንዴው ፖለቲካ በፊት የሰሜኑን ጦርነት ኢትዮጵያ እንደማታሸንፍ እና የወንበዴው ቡድን ኃይል ታላቅ እንደሆነ በየቀኑ ሲሰብኩ ነበር። የወንበዴው ቡድን ከምዕራባውያን ጋር ነውና ኢትዮጵያ አልቆላታል እያሉ ተስፋ አስቆራጭ ዲስኩር ሲለቅቁ ነበር። አጎዋ ስንሰረዝ ከበር መልስ ተገባበዙ፣ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ለቁጥር የሚታክት ስብሰባ በአገራችን ላይ ሲጠራ አልቆላችኋል ሲሉን ነበር።

የእኛዎቹ ይሁዲዎች የወንበዴው ቡድን አገልጋዮች በነበሩ ጊዜ በዕቅድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን በማፍረስና በማስፈረስ ታጥቀው የሠሩ ይህንን እንደ ሜዳሊያ በጽሑፎቻቸው በግልጽ ሲሰብኩ የነበሩ፤ አሁን ደግሞ የኦርቶዶክስ ቋሚ ጠበቃ ሆነው ብቅ ያሉ፤ ጉዳዩ በሰላም ሲጠናቀቅ ግዝት ፈርተው ከካሜራ ውጪ ሲኖዶሱን ሙልጭ አድርገው የተሳደቡና አባቶችን ከፍ ዝቅ አድርገው ያዋረዱ ናቸው። 

የከሸፈ፣ የተመታ፣ የትም የማያደርስ፣ የምቀኝነት፣ የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ!

የይሁዳ ዓላማ የራስ ጥቅም እና ሲመተ-እኔ ነው! እኔ ልጠቀም፣ እኔ ልሾም፣ እኔ … እኔ … ነው። ይህ የሚፈጸመው ግን በገሃድ ሳይሆን በሕዝብ ዕንባና ደም ወንዝ ላይ ወደ ሥልጣን በመቅዘፍ ነው። እጅግ የረከሰ፣ እጅግ ኢሞራላዊ፣ እጅግ አስጸያፊ የሆነ፣ የመስተካከል እንጥፍጣፊ ተስፋ የሌለው ማንነት!

መጽሐፍ ስለ ይሁዳ መጨረሻ ሲናገር እንዲህ ይላል፤ “(ሠላሳ) ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ”።

ባለማተቡ ነኝ (trinity123@aol.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Ethio 360, ethiopian terrorists, lidetu ayalew, operation dismantle tplf, tamrat layne, tplf terrorist, yared tibebu

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule