• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ!

February 24, 2023 08:19 am by Editor 1 Comment

ስሙ የክህደት መጠሪያ ሆነ እንጂ የስሙ ትርጉም ግሩም ነው። ይሁዳ የሚለው ቃል በእብራይስጥም “ይሁዳ” ማለት ነው፤ “ያዳ” ነው ሥርወ ቃሉ ይላሉ የሙያው ባለቤቶች። ይህ ደግሞ ትርጉሙ “ማመስገን” ማለት ነው። በግሪክም ትርጓሜው ተመሳሳይ ነው – “የተመሰገነ”፣ “ምስጉን” ማለት ነው። 

“የአስቆሮቱ” የሚለው ቃል ደግሞ የክፋት መጠሪያ አይደለም። በተለምዶ “የአስቆሮቱ ይሁዳ” በማለት ከሃዲዎችን ስንጠራቸው “አስቆሮቱ” የይሁዳ የክፋት ማዕረግ ይመስለናል። ሊቃውንቱ እንደሚሉን ከሆነ ትርጉሙ “የኬሪዮት ሰው” ወይም “የአራዳ ልጅ” እንደ ማለት ነው ይላሉ። ስለዚህ በከሃዲነቱ ባናውቀው ኖሮ “ተመስገን ያራዳ ልጅ” ብለን እንጠራው ነበር። ስሙ ግን ከግብሩ ፍጹም የራቀ ነው፤ እንዲያውም ተጻራሪ።

ይሁዳ ከሃዲ ብቻ አይደለም፤ ማሳካት የሚፈልገው ዓላማ ያለውና የሚያደርገውን ጠንቅቆ የሚያውቅ ነበር። ከመድኃኒዓለም ጋር አብሮ ለሦስት ዓመት ተኩል ቆይቷል፤ የጌታችንን አስተዳደርና አመራር ውስጠ ምሥጢሩን በደንብ አጥንቷል። “ሐዋርያ” ተብሎ ተጠርቷል። ሁለት፣ ሁለት ተደርገው ሲላኩ እርሱም ሁለት ጊዜ ተልኳል። አጋንንት አውጥቷል፣ ተዓምራት ሠርቷል፤ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንሰሐ ግቡ” እያለ ወንጌልን ሰብኳል!

ይሁዳ ሲነቅፍ በጭፍን አይደለም፤ ረቂቅ ነው። አዛኝና ርኅሩኅ ምስኪን ሆኖ ነው እንጂ በፈጣጣው አይደለም። ማርያም መግደላዊት እጅግ ውድ የሆነ ሽቶ በጌታችን እግር ላይ ስታፈስ “ይህ ተሸጦ ድሆችን መመገብ ይቻል ነበር” ያለው እንጂ በጭፍን አልተቃወመም። መጽሐፍ ግን ይህንን ያለው “ሌባ ስለነበር ነው” ይላል።

መምህሩን የሸጠው ለገንዘብ ብቻ ብሎ አይደለም። ዓላማው ሌላ ሆኖ “ለምን ቢዝነስ አልሠራም” በሚል ገንዘቧ የጎንዮሽ ጥቅም ማስገኛ ነበረች። መድኃኒዓለም አሳልፎ ከተሰጠ አልያዝም በማለት ያምጻል፤ ከዚያም ያንን ሙታንን የሚስነሳውን ኃይል ተጠቅሞ ሮምን ድምጥማጧ ያጠፋል፤ ከዚያም መምህሩ በዳዊት ዙፋን ሲነግሥ “ለዚህ ነጻነት ያበቃኋችሁ እኔ ነኝ” ብሎ ይሁዳ የእልፍኝ አስከልካይ ወይም አፈ ንጉሥ ወይም የንጉሥ አማካሪ ወይም አንድ የሆነ ሥልጣን ላይ እደርሳለሁ ብሎ ነበር። ሁሉም ቀርቶ መጨረሻው ፍጹም የተለየ ሆነ!

የእኛ አገር ፖለቲከኞች፣ አክቲቪስቶች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎች የሚባሉት፣ ዩትዩበሮች፣ ወዘተ ከስማቸው ብንነሳ የብዙዎቹ ቤተሰብ ያወጣላቸው ስም በጣም ደስ የሚልና ጥሩ ትርጉም ያለው ነው። እንዲያውም ከመጽሐፍ ቅዱስ የተወሰደ ነው። አሁን አሁን ግን የአንዳንዶቹ ስም እንደ ይሁዳ ለልጆቻችን የማናወጣው እየሆነ የመጣ ይመስላል። እንደው እንደ ምሳሌ ብንጠቅስ ልጁን “ሕዝቅኤል፣ ኤርምያስ” ብሎ የሚሰይም ሁለት ጊዜ ማሰቡ አይቀሬ ነው። የሌሎቹ ስም እንኳን ከድህነት ለመላቀቅ፣ ከደጋፊ ዘመድ አልባ ብቸኝነት ለማምለጥ በሚል ለምኞት ማስታገሻነት የወጡ የአጥቢያ ስሞች ስለሆኑ ሳልጠቅስ ልለፋቸው።  

እነዚህ የአገራችን ይሁዳዎች እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ዓላማ ያላቸው ናቸው። በየቀኑ የሚያደርጉትን ጠንቅቀው ያውቃሉ፤ መዳረሻ አላቸው። በሥራቸው የሚላላኩላቸው ጉዳይ ፈጻሚዎችም አሏቸው። በየቀኑ እየበላሁ እንዴት ዝም እላለሁ እንደሚል ውሻ እየወጡ የሚጮኹ ናቸው። ብዙዎቹ በቅርብ ሆነው ምሥጢር በመጠኑ ያጠኑና ያወቁ ናቸው። ለውጡን ተከትሎ በየሚዲያው የለውጡን ወንጌል ውስጥ ካሉት ሰዎች በላይ ሲሰብኩ የነበሩ ናቸው። “የለውጥ ዘመን መጥቷልና ከዘመነ ኢህአዴግ አገዛዝ ንሰሐ ግቡ” እያሉ በየቀኑ ስብከተ ለውጥ ሲያሰሙ፣ ውዳሴ ሲያቀርቡ ነበሩ።

በኢህአዴግ ዘመን የፖለቲካ ዓይናቸው የታወረውን ያበሩ፣ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ልክፍት የተያዙን በወንጌለ ለውጥ እያናዘዙ ያስወጡ፤ ከለውጡ ሊቃነ ጳጳሳት በላይ የለውጥ ፋና ወጊዎች የነበሩ ናቸው። ከባሕር ማዶ የተመኙትና በርቀት የተሳለሙት ሹመት፣ አማካሪነት፣ ቪላ ቤት፣ ቪ8፣ … ቀቢጸ ተስፋ ሆኖ እንደ ጉም ሲተንንባቸው ኢትዮጵያን ለመስቀል 30 ብር ተቀብለው እንደ ይሁዳ ሥራቸውን በምሽት እየሠሩ ነው – የጨለማውን ሥራ! ይሁዳ መምህሩን አሳልፎ ለመስጠት በአንድነት ራት ይበሉ ከነበረበት ቤት ሲወጣ መጽሐፍ ሲናገር “ሌሊትም ነበር” ይላል። 

የዘመናችን ይሁዳዎች እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ለድሃ ሐዘነተኛ ሆኖ በመታየት የሚቀድማቸው የለም። ይሁዳ ሽቶው ተሸጦ ለድሆች ሊሰጥ ይችላል አለ እንጂ እኔ ለድሆች ልስጥ አላለም። እነዚህም እንዲሁ ናቸው። ሰው እየሞተ ዳቦ ቤት ለምን ይገነባል? ለዳቦ ቤት መገንቢያ የወጣውን ገንዘብ ለድሆች ብናከፋፍለው ለስንት ደሃ ሊደርስ ይችል ነበር? በማለት ይሁዳዊ አዛኝነታቸውን ያሰማሉ።

ኢትዮጵያ ስሟን ቀያሪ የሆነውን ተግባር ፈጸመች – ስንዴ ወደ ውጭ ላከች! ሲባል የስንዴ ዱቄት ከአገር ውስጥ ገበያ ጠፍቷል ይላሉ። ከዚህ በፊት ስንዴ ለመላክ እየሠራን ነው ሲባል ግን ምንም ትንፍሽ ሳይሉ የቆዩ ናቸው። ምናልባትም ስንዴው ለምርት አይደርስም ብለው ጠብቀው ይሆናል። ምርቱ መሰብሰብ ሲጀምር ግን በጦርነት እየታመሰች ያለችው ዩክሬይን ለኢትዮጵያ ስንዴ ላከች ብለው ነበር። የሚገርመው የእርዳታ እህል ተካለ ሳይሆን የተባለው “ስንዴ” በስም ተጠርቶ ነው ወሬው የተሰራጨው። መርከቧ በሶማሊያ የባሕር አደጋ ጣዮች ተዘረፈች እንዳንል እስካሁን ምንም የተሰማ ነገር የለም፤ መርከቧ ቀርታ “ስንዴው” ቢደርስ እንኳ ጥሩ ነበር።

ኢትዮጵያዊ ይሁዲዎቹ ከስንዴው ፖለቲካ በፊት የሰሜኑን ጦርነት ኢትዮጵያ እንደማታሸንፍ እና የወንበዴው ቡድን ኃይል ታላቅ እንደሆነ በየቀኑ ሲሰብኩ ነበር። የወንበዴው ቡድን ከምዕራባውያን ጋር ነውና ኢትዮጵያ አልቆላታል እያሉ ተስፋ አስቆራጭ ዲስኩር ሲለቅቁ ነበር። አጎዋ ስንሰረዝ ከበር መልስ ተገባበዙ፣ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ለቁጥር የሚታክት ስብሰባ በአገራችን ላይ ሲጠራ አልቆላችኋል ሲሉን ነበር።

የእኛዎቹ ይሁዲዎች የወንበዴው ቡድን አገልጋዮች በነበሩ ጊዜ በዕቅድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን በማፍረስና በማስፈረስ ታጥቀው የሠሩ ይህንን እንደ ሜዳሊያ በጽሑፎቻቸው በግልጽ ሲሰብኩ የነበሩ፤ አሁን ደግሞ የኦርቶዶክስ ቋሚ ጠበቃ ሆነው ብቅ ያሉ፤ ጉዳዩ በሰላም ሲጠናቀቅ ግዝት ፈርተው ከካሜራ ውጪ ሲኖዶሱን ሙልጭ አድርገው የተሳደቡና አባቶችን ከፍ ዝቅ አድርገው ያዋረዱ ናቸው። 

የከሸፈ፣ የተመታ፣ የትም የማያደርስ፣ የምቀኝነት፣ የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ!

የይሁዳ ዓላማ የራስ ጥቅም እና ሲመተ-እኔ ነው! እኔ ልጠቀም፣ እኔ ልሾም፣ እኔ … እኔ … ነው። ይህ የሚፈጸመው ግን በገሃድ ሳይሆን በሕዝብ ዕንባና ደም ወንዝ ላይ ወደ ሥልጣን በመቅዘፍ ነው። እጅግ የረከሰ፣ እጅግ ኢሞራላዊ፣ እጅግ አስጸያፊ የሆነ፣ የመስተካከል እንጥፍጣፊ ተስፋ የሌለው ማንነት!

መጽሐፍ ስለ ይሁዳ መጨረሻ ሲናገር እንዲህ ይላል፤ “(ሠላሳ) ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ”።

ባለማተቡ ነኝ (trinity123@aol.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Ethio 360, ethiopian terrorists, lidetu ayalew, operation dismantle tplf, tamrat layne, tplf terrorist, yared tibebu

Reader Interactions

Comments

  1. ይስሃቅ አበበ says

    March 21, 2023 01:18 pm at 1:18 pm

    በተጨባጭ የነ ቁስ ከርስ ጉርስ ፈላጊና ህልመኛ ይሁዳ አክቲቪስቶችን ማንነት በትክክል የገመገክበት እውነታ ነው !! የሚያሳዝነው ግን የዋሁ ህዝባችን እነዚህን ክፉ የሴራ ተንኮል አሉባልተኞች አለመረዳቱ አለማወቁ ነው ። ዘውትር መንግስትን ማብጠልጠል ማሳነስ ለሀገር አንዳች አይጠቅምም ። በጎውንም በሚዛን የሚገልፁ አሉ እነዚህ ለኔ ለትውልድም ለሀገርም የሚያስቡ የህሊና ንፅህና ያላቸው በጎ ስዎች ናቸው ። ማድመጥም መስማትም ያለብን እነዚህን ነው ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule