• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ታከለ ኡማ የዳያስፖራ አኩራፊዎችን ሰብስበው ድርጅት እየመሠረቱ ነው፣ ሚዲያም አቋቁመዋል 

July 11, 2023 01:00 am by Editor 1 Comment

ከኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ወደ ኦህዴድ ከለወጡት የዶክተር መረራ ወጣቶች ክንፍ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ታከለ ኡማ አዲስ የትግል ኅብረት በመፍጠር ላይ መሆናቸው ተሰማ። ለዚህ እንቅስቃሴ የሚሆናቸው የመደበኛ ሚዲያና የማኅበራዊ ሚዲያ ትሥሥር ገጽ ሠራዊት እንዳመቻቹም ታውቋል። መነሻቸው ፖለቲካዊ ኩርፊያ ነው ተብሏል።

ጎልጉልን ያነጋገሩ የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የማዕድን ሚኒስትር መንግሥት ላይ አቂመዋል። የለውጡ የምሥጢር ታጋይ እንደነበሩ የሚናገሩት ታከለ አሜሪካ ከተሻገሩ በኋላ በዳያስፖራ ከሚገኙ ዋነኛ አኩራፊዎች ጋር በማበር ጠበቅ ባለ እንቅስቃሴ ተጠምደዋል።    

ጥያቄው ከቀረበላቸው መካከል አንዱ የሆኑት የኦህዴድ የቀድሞ አመራር እንዳሉት ታከለ ኡማ ከአማራ፣ ከኦሮሞና የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ካኮረፉ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) አካላት ጋር ምክክርና ግንኙነት ጀምረዋል።    

እንዲህ ያለውን ስብስብ ከጀርባ በመምራት የሚታወቁት ሻለቃ ዳዊት መሆናቸውን በተደጋጋሚ በጎልጉል ድረገጽ የዘገብነው ጉዳይ እንደሆነ ይታወቃል። በወቅቱ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሻለቃ ዳዊት በ1977 ዓም ተከሰተ በተባለውድርቅ ከረሃብተኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ 300,000 ሺህ ዶላር በመዝረፍ አሜሪካ ሁለት ቤት መግዛታቸውን ይታወሳል።    

ታከለ ኡማ የአዲስ አበባ ከንቲባ እያሉ በተደጋጋሚ አቶ ጃዋር መሀመድ ቤት ይታዩ እንደ ነበር ድንገት እዚያ ያገኙዋቸው ምስክሮች አሉ። ቀደም ሲል የሆለታ ከንቲባ እያሉ ባልደረቦቻቸው በሙሉ በሌብነት ሲታሰሩ እርሳቸው ብቻ ነጻ መደረጋቸውን ተከትሎ “ሁለት ቦታ መጫወት ይችሉበታል” በሚል በኔትዎርክ አብረዋቸው መሬት ሲያጫውቱ በነበሩ ባልደረቦቻቸው ይታሙ እንደነበር ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑ በኋላ በመሬት ጉቦ ሚዲያ በመያዝ ሰፊ ምዝበራ እንዳካሄዱ የሚነገርባቸው ታከለ ኡማ ወደ ማዕድን ሚኒስትርነት ሲዛወሩም በተመሳሳይ ከወርቅ ማዕድን መሬት እደላ ጋር በተያያዘ ስማቸው ከሚታወቁ “ምስለኔዎች” ጋር ተነስቷል።    

እዚያው ማዕድን ሚኒስትር እያሉ ምዕራብ ሸዋ ቶኬ አካባቢ አባታቸው በኅዳር ወር 2015ዓም በኦነግ ሸኔ ታፍነው 10ሚሊዮን ብር ክፈሉ ተብለዋል የሚል መረጃ በወጣበት ሰሞን ታከለ በትዊተር ገጻቸው ላይ “አባቴ አርሶ አደርነው፤ አሁን ምግብርና ላይ ነው” (Abbaan kiyya qotee bulla dha. Ammas qonnasaarra jira) ከማለት ሌላ ምንም አልተናገሩም ነበር። ታከለ ይህንን ከለጠፉ በኋላ ምንም ክፍያ ሳይጠየቁ አባታቸው መለቀቃቸውን የሚያውቁ የታከለና የሸኔን ግንኙነት በተመለከ ተከፍተኛ ጥርጣሬ እንዳደረባቸው ገልጸው በድርጅትና በመረጃ ደህንነት በኩል ማጣራት እንዲካሄድባቸው ጥያቄ ቀርቦ እንደነበር ዜናውን ያጋሩት አስታውሰዋል።    

የትግራይ ተወላጅ ከሆነች ከቀድሞ ወዳጃቸው አንድ ልጅ ያላቸው ታከለ ኡማ “ሸኔዎችሊገድሉኝሞክረዋል” በሚል መኖሪያ ቤታቸውን ያስቀየሩት ምራሳቸው ከሚታሙበት ጉዳይ ነጻ ለማውጣት ሆነ ብለው የተጠቀሙበት ሥልት እንደሆነ እነዚሁ ወገኖች በርካታ መረጃዎችያቀርባሉ።    

አሜሪካ ከገቡ በኋላ ከልጃቸው እናት ጋር ስላላቸው ግንኙነት ብዙም መረጃ እንደሌላቸው የሚናገሩት  ወገኖች “አቶ ታከለ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሪፖርተርነት ትሠራ የነበረች አንድ ወዳጃቸው የምትመራው ሚዲያ ከፍተዋል። አሁን ወቅቱ ስላልሆነ የሚዲያው እና የሚዲያውን መሪ ስም ለጊዜው መግለጽ አስፈላጊ አይደለም” ሲሉ የሚያውቁትን ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አመልክተዋል።    

አቶ ታከለ በቅርቡ አዲስ አበባ ደርሰው የተመለሱ ሲሆን በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከመንግሥት ሰዎች ጋር ብዙም ግንኙነት እንዳላደረጉ ታውቋል። ከሚኒስትርነት ሥልጣናቸው ሲነሱ ቢያንስ ኦሮሚያ ክልል አለመመደባቸው ክፉኛ ያበሳጫቸው አቶ ታከለ በአቶ ግርማ ብሩ ሽማግሌነት ድርጅታዊ ይቅርታ ተደርጎላቸው ለትምህርት በሚል ወደ አሜሪካ ማምራታቸውን ለጎልጉል መረጃውን ካቀበሉት ለመረዳት ተችሏል።    

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, takele uma, takele umma, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. haileyesus says

    July 12, 2023 12:01 am at 12:01 am

    ማውራት የፈለከው ስለማን እንደሆነ ገብቶኛል።
    ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule