• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ታከለ ኡማ የዳያስፖራ አኩራፊዎችን ሰብስበው ድርጅት እየመሠረቱ ነው፣ ሚዲያም አቋቁመዋል 

July 11, 2023 01:00 am by Editor 1 Comment

ከኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ወደ ኦህዴድ ከለወጡት የዶክተር መረራ ወጣቶች ክንፍ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ታከለ ኡማ አዲስ የትግል ኅብረት በመፍጠር ላይ መሆናቸው ተሰማ። ለዚህ እንቅስቃሴ የሚሆናቸው የመደበኛ ሚዲያና የማኅበራዊ ሚዲያ ትሥሥር ገጽ ሠራዊት እንዳመቻቹም ታውቋል። መነሻቸው ፖለቲካዊ ኩርፊያ ነው ተብሏል።

ጎልጉልን ያነጋገሩ የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የማዕድን ሚኒስትር መንግሥት ላይ አቂመዋል። የለውጡ የምሥጢር ታጋይ እንደነበሩ የሚናገሩት ታከለ አሜሪካ ከተሻገሩ በኋላ በዳያስፖራ ከሚገኙ ዋነኛ አኩራፊዎች ጋር በማበር ጠበቅ ባለ እንቅስቃሴ ተጠምደዋል።    

ጥያቄው ከቀረበላቸው መካከል አንዱ የሆኑት የኦህዴድ የቀድሞ አመራር እንዳሉት ታከለ ኡማ ከአማራ፣ ከኦሮሞና የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ካኮረፉ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) አካላት ጋር ምክክርና ግንኙነት ጀምረዋል።    

እንዲህ ያለውን ስብስብ ከጀርባ በመምራት የሚታወቁት ሻለቃ ዳዊት መሆናቸውን በተደጋጋሚ በጎልጉል ድረገጽ የዘገብነው ጉዳይ እንደሆነ ይታወቃል። በወቅቱ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሻለቃ ዳዊት በ1977 ዓም ተከሰተ በተባለውድርቅ ከረሃብተኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ 300,000 ሺህ ዶላር በመዝረፍ አሜሪካ ሁለት ቤት መግዛታቸውን ይታወሳል።    

ታከለ ኡማ የአዲስ አበባ ከንቲባ እያሉ በተደጋጋሚ አቶ ጃዋር መሀመድ ቤት ይታዩ እንደ ነበር ድንገት እዚያ ያገኙዋቸው ምስክሮች አሉ። ቀደም ሲል የሆለታ ከንቲባ እያሉ ባልደረቦቻቸው በሙሉ በሌብነት ሲታሰሩ እርሳቸው ብቻ ነጻ መደረጋቸውን ተከትሎ “ሁለት ቦታ መጫወት ይችሉበታል” በሚል በኔትዎርክ አብረዋቸው መሬት ሲያጫውቱ በነበሩ ባልደረቦቻቸው ይታሙ እንደነበር ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑ በኋላ በመሬት ጉቦ ሚዲያ በመያዝ ሰፊ ምዝበራ እንዳካሄዱ የሚነገርባቸው ታከለ ኡማ ወደ ማዕድን ሚኒስትርነት ሲዛወሩም በተመሳሳይ ከወርቅ ማዕድን መሬት እደላ ጋር በተያያዘ ስማቸው ከሚታወቁ “ምስለኔዎች” ጋር ተነስቷል።    

እዚያው ማዕድን ሚኒስትር እያሉ ምዕራብ ሸዋ ቶኬ አካባቢ አባታቸው በኅዳር ወር 2015ዓም በኦነግ ሸኔ ታፍነው 10ሚሊዮን ብር ክፈሉ ተብለዋል የሚል መረጃ በወጣበት ሰሞን ታከለ በትዊተር ገጻቸው ላይ “አባቴ አርሶ አደርነው፤ አሁን ምግብርና ላይ ነው” (Abbaan kiyya qotee bulla dha. Ammas qonnasaarra jira) ከማለት ሌላ ምንም አልተናገሩም ነበር። ታከለ ይህንን ከለጠፉ በኋላ ምንም ክፍያ ሳይጠየቁ አባታቸው መለቀቃቸውን የሚያውቁ የታከለና የሸኔን ግንኙነት በተመለከ ተከፍተኛ ጥርጣሬ እንዳደረባቸው ገልጸው በድርጅትና በመረጃ ደህንነት በኩል ማጣራት እንዲካሄድባቸው ጥያቄ ቀርቦ እንደነበር ዜናውን ያጋሩት አስታውሰዋል።    

የትግራይ ተወላጅ ከሆነች ከቀድሞ ወዳጃቸው አንድ ልጅ ያላቸው ታከለ ኡማ “ሸኔዎችሊገድሉኝሞክረዋል” በሚል መኖሪያ ቤታቸውን ያስቀየሩት ምራሳቸው ከሚታሙበት ጉዳይ ነጻ ለማውጣት ሆነ ብለው የተጠቀሙበት ሥልት እንደሆነ እነዚሁ ወገኖች በርካታ መረጃዎችያቀርባሉ።    

አሜሪካ ከገቡ በኋላ ከልጃቸው እናት ጋር ስላላቸው ግንኙነት ብዙም መረጃ እንደሌላቸው የሚናገሩት  ወገኖች “አቶ ታከለ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሪፖርተርነት ትሠራ የነበረች አንድ ወዳጃቸው የምትመራው ሚዲያ ከፍተዋል። አሁን ወቅቱ ስላልሆነ የሚዲያው እና የሚዲያውን መሪ ስም ለጊዜው መግለጽ አስፈላጊ አይደለም” ሲሉ የሚያውቁትን ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አመልክተዋል።    

አቶ ታከለ በቅርቡ አዲስ አበባ ደርሰው የተመለሱ ሲሆን በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከመንግሥት ሰዎች ጋር ብዙም ግንኙነት እንዳላደረጉ ታውቋል። ከሚኒስትርነት ሥልጣናቸው ሲነሱ ቢያንስ ኦሮሚያ ክልል አለመመደባቸው ክፉኛ ያበሳጫቸው አቶ ታከለ በአቶ ግርማ ብሩ ሽማግሌነት ድርጅታዊ ይቅርታ ተደርጎላቸው ለትምህርት በሚል ወደ አሜሪካ ማምራታቸውን ለጎልጉል መረጃውን ካቀበሉት ለመረዳት ተችሏል።    

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, takele uma, takele umma, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. haileyesus says

    July 12, 2023 12:01 am at 12:01 am

    ማውራት የፈለከው ስለማን እንደሆነ ገብቶኛል።
    ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule