• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ታከለ ኡማ የዳያስፖራ አኩራፊዎችን ሰብስበው ድርጅት እየመሠረቱ ነው፣ ሚዲያም አቋቁመዋል 

July 11, 2023 01:00 am by Editor 1 Comment

ከኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ወደ ኦህዴድ ከለወጡት የዶክተር መረራ ወጣቶች ክንፍ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ታከለ ኡማ አዲስ የትግል ኅብረት በመፍጠር ላይ መሆናቸው ተሰማ። ለዚህ እንቅስቃሴ የሚሆናቸው የመደበኛ ሚዲያና የማኅበራዊ ሚዲያ ትሥሥር ገጽ ሠራዊት እንዳመቻቹም ታውቋል። መነሻቸው ፖለቲካዊ ኩርፊያ ነው ተብሏል።

ጎልጉልን ያነጋገሩ የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የማዕድን ሚኒስትር መንግሥት ላይ አቂመዋል። የለውጡ የምሥጢር ታጋይ እንደነበሩ የሚናገሩት ታከለ አሜሪካ ከተሻገሩ በኋላ በዳያስፖራ ከሚገኙ ዋነኛ አኩራፊዎች ጋር በማበር ጠበቅ ባለ እንቅስቃሴ ተጠምደዋል።    

ጥያቄው ከቀረበላቸው መካከል አንዱ የሆኑት የኦህዴድ የቀድሞ አመራር እንዳሉት ታከለ ኡማ ከአማራ፣ ከኦሮሞና የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ካኮረፉ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) አካላት ጋር ምክክርና ግንኙነት ጀምረዋል።    

እንዲህ ያለውን ስብስብ ከጀርባ በመምራት የሚታወቁት ሻለቃ ዳዊት መሆናቸውን በተደጋጋሚ በጎልጉል ድረገጽ የዘገብነው ጉዳይ እንደሆነ ይታወቃል። በወቅቱ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሻለቃ ዳዊት በ1977 ዓም ተከሰተ በተባለውድርቅ ከረሃብተኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ 300,000 ሺህ ዶላር በመዝረፍ አሜሪካ ሁለት ቤት መግዛታቸውን ይታወሳል።    

ታከለ ኡማ የአዲስ አበባ ከንቲባ እያሉ በተደጋጋሚ አቶ ጃዋር መሀመድ ቤት ይታዩ እንደ ነበር ድንገት እዚያ ያገኙዋቸው ምስክሮች አሉ። ቀደም ሲል የሆለታ ከንቲባ እያሉ ባልደረቦቻቸው በሙሉ በሌብነት ሲታሰሩ እርሳቸው ብቻ ነጻ መደረጋቸውን ተከትሎ “ሁለት ቦታ መጫወት ይችሉበታል” በሚል በኔትዎርክ አብረዋቸው መሬት ሲያጫውቱ በነበሩ ባልደረቦቻቸው ይታሙ እንደነበር ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑ በኋላ በመሬት ጉቦ ሚዲያ በመያዝ ሰፊ ምዝበራ እንዳካሄዱ የሚነገርባቸው ታከለ ኡማ ወደ ማዕድን ሚኒስትርነት ሲዛወሩም በተመሳሳይ ከወርቅ ማዕድን መሬት እደላ ጋር በተያያዘ ስማቸው ከሚታወቁ “ምስለኔዎች” ጋር ተነስቷል።    

እዚያው ማዕድን ሚኒስትር እያሉ ምዕራብ ሸዋ ቶኬ አካባቢ አባታቸው በኅዳር ወር 2015ዓም በኦነግ ሸኔ ታፍነው 10ሚሊዮን ብር ክፈሉ ተብለዋል የሚል መረጃ በወጣበት ሰሞን ታከለ በትዊተር ገጻቸው ላይ “አባቴ አርሶ አደርነው፤ አሁን ምግብርና ላይ ነው” (Abbaan kiyya qotee bulla dha. Ammas qonnasaarra jira) ከማለት ሌላ ምንም አልተናገሩም ነበር። ታከለ ይህንን ከለጠፉ በኋላ ምንም ክፍያ ሳይጠየቁ አባታቸው መለቀቃቸውን የሚያውቁ የታከለና የሸኔን ግንኙነት በተመለከ ተከፍተኛ ጥርጣሬ እንዳደረባቸው ገልጸው በድርጅትና በመረጃ ደህንነት በኩል ማጣራት እንዲካሄድባቸው ጥያቄ ቀርቦ እንደነበር ዜናውን ያጋሩት አስታውሰዋል።    

የትግራይ ተወላጅ ከሆነች ከቀድሞ ወዳጃቸው አንድ ልጅ ያላቸው ታከለ ኡማ “ሸኔዎችሊገድሉኝሞክረዋል” በሚል መኖሪያ ቤታቸውን ያስቀየሩት ምራሳቸው ከሚታሙበት ጉዳይ ነጻ ለማውጣት ሆነ ብለው የተጠቀሙበት ሥልት እንደሆነ እነዚሁ ወገኖች በርካታ መረጃዎችያቀርባሉ።    

አሜሪካ ከገቡ በኋላ ከልጃቸው እናት ጋር ስላላቸው ግንኙነት ብዙም መረጃ እንደሌላቸው የሚናገሩት  ወገኖች “አቶ ታከለ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሪፖርተርነት ትሠራ የነበረች አንድ ወዳጃቸው የምትመራው ሚዲያ ከፍተዋል። አሁን ወቅቱ ስላልሆነ የሚዲያው እና የሚዲያውን መሪ ስም ለጊዜው መግለጽ አስፈላጊ አይደለም” ሲሉ የሚያውቁትን ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አመልክተዋል።    

አቶ ታከለ በቅርቡ አዲስ አበባ ደርሰው የተመለሱ ሲሆን በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከመንግሥት ሰዎች ጋር ብዙም ግንኙነት እንዳላደረጉ ታውቋል። ከሚኒስትርነት ሥልጣናቸው ሲነሱ ቢያንስ ኦሮሚያ ክልል አለመመደባቸው ክፉኛ ያበሳጫቸው አቶ ታከለ በአቶ ግርማ ብሩ ሽማግሌነት ድርጅታዊ ይቅርታ ተደርጎላቸው ለትምህርት በሚል ወደ አሜሪካ ማምራታቸውን ለጎልጉል መረጃውን ካቀበሉት ለመረዳት ተችሏል።    

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, takele uma, takele umma, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. haileyesus says

    July 12, 2023 12:01 am at 12:01 am

    ማውራት የፈለከው ስለማን እንደሆነ ገብቶኛል።
    ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule