• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠ/ሚ/ሩ በአሜሪካ ከወሳኝ ኢትዮጵያውያን ጋር ሊነጋገሩ ነው

May 25, 2018 03:12 pm by Editor 1 Comment

በኢህአዴግ የተሰየሙት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ በሰኔ ወር መገባደጃ አካባቢ ወደ አሜሪካ ጉዞ እንደሚያደርጉ ታወቀ። በቆይታቸው ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ በተለይ በሰላማዊ መንገድ ትግል ከሚያደርጉ ኢትዮጵያውያን ጋር በግልና በቡድን በመገናኘት ሊነጋገሩ እንደሚችሉ ተነግሯል።

በህወሓት/ኢህአዴግ ስያሜ የጠቅላዩን መንበር የተቆናጠጡት ዓቢይ አህመድ ላለፉት በርካታ ሳምንታት በአገር ውስጥ እና በአጎራባች አገራት ጉብኝቶችን ሲደርጉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቀጣይ የተያዘው መርሃግብር ወደ አውሮጳና አሜሪካ ጉዞ ማድረግ እንደሚሆን መረጃዎች ሲወጡ ነበር። ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ የጠቅላይ ሚ/ሩ የአሜሪካ ጉብኝት መረጃ ቀደም ብሎ የደረሰው ቢሆንም በወቅቱ የተባለው በሰኔ ወር መገባደጃ ወይም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ላይ ንግግር ለማድረግ በመስከረም አካባቢ ሲመጡ ሊሆን ይችላል የሚለው ነበር።

ዛጎል ታማኝ ምንጮቼ ያደረሱኝ መረጃ ነው በሚል በድረገጹ ላይ እንደገለጸው ጠ/ሚ/ሩ “ሰኔ 26 ወይም 27 ወደ አሜሪካ እንደሚያቀኑ” ተናግሯል። ሲቀጥልም የዓቢይ አህመድ ጉብኝት “በአሜሪካ በኩል ሙሉ ድጋፍ ያለውና አስፈላጊው ሁሉ ትብብር የሚደረግለት” መሆኑን አስታውቋል።

“በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ አዙሪት ያሳሰባት አሜሪካ በአገሪቱ የሰከነ የፖለቲካ ለውጥ እንዲኖር፣ ለዚሁም ተግባራዊነት ድጋፍ የምታደርግ፣ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ይህንን ለውጥ የማይቀበል ከሆነ ኮሮጆውን እስከማድረቅ የሚያደርስ እርምጃ እንደምትወስድ እያስጠነቀቀች መቆየቷ ይታወሳል። በሂደት ላይ ያሉ የህግ ጉዳዮችም አሉ። በዚሁ ቅኝት መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የአሜሪካ ጉዞ በዲያስፖራውና በመንግሥት በኩል ያለውን ልዩነት ለማርገብ፣ የወደፊቱን የለውጥ ሂደት የማስረዳትና በዝርዝር የማሳየት እንዲሁም አፋኝ የሚባሉት ህጎችን አስመልክቶ የሚደረገውን ማሻሻል በይፋ የማሳወቅ ነው። ተያይዞም አገራቸው መግባት ለሚፈልጉ በይፋ ዋስትና የሚሰጥ ግብዣ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።”

ጊዜው ሲደርስ የሚታወቅ ቢሆንም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የጉብኝት ወቅት በዳስፖራው ፖለቲካ ላይ በጉልህ የሚታወቁ በተለይም በሰላማዊ (ነውጥ አልባ) መንገድ ትግላቸውን ለዓመታት ሲያካሂዱ ከነበሩ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር ይገናኛሉ ተብሏል። እነዚህም በድርጅት ተደራጅተውም ይሁን በግላቸው በአገራቸው ጉዳይ ላይ የሚወተውቱትን እንደሚካትት ታውቋል።

“በዚሁ መሰረት ውይይቱ ከመዘላለፍ፣ ከሁከትና ውጤት ከማያስገኝ እንከኖች የጸዳ ይሆን ዘንድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንን” ዛጎል የመረጃ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። ሲቀጥልም “(የዜናው አቀባዮች) ስለ አጠቃላዩ ዝግጅት ከመናገራቸው ውጪ ስለሚደረገው ዝግጅት በዝርዝር አላብራሩም፤ የአሜሪካ ሚና ምን እንደሚሆንም አላስታወቁም” ብሏል።

የጠቅላዩን ጉዞ በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ ወገኖች ጉብኝቱን እንደ መልካም ዕድል በመጠቀም ለበጎ ውጤት እንጠቀምበት በማለት ይመክራሉ። ጠቅላይ ሚ/ር ዓቢይ አህመድ የዳያስፖራውን ኃይል በሚገባ የተገነዘቡና ይህንንም በአደባባይ የተናገሩ መሆናቸውን የሚጠቅሱ ክፍሎች ዳያስፖራው ካለው ሙሉ የመናገር መብት አኳያ አገር ቤት ያለው ኢትዮጵያዊ በድፍረት ሊናገር የማይችለውን በማንሳት ለወገኑ ያለውን ተቆርቋሪነት ማሳየት ይገባል ይላሉ። ከዚህ በፊት የህወሓት ኃላፊዎች በድብቅ መጥተው በድብቅ መሄዳቸው አግባብነት የለውም በሚል ትልቅ ተቃውሞ ይደርስባቸው እንደነበር የሚያስታውሱ ወገኖች በገሃድ እንወያይ የሚል መሪ ሲመጣ በጭፍን ከመቃወም ይልቅ “እኛም የምንፈልገው ይህንን ነበር” በሚል በሰከነ መንፈስ የጉብኝቱ አካል መሆን ይገባቸዋል በማለት ሃሳብ ይሰጣሉ።

ጉብኝቱ ዋሽንግቶን ዲሲ በሚገኘው ኤምባሲ የበላይ ኃላፊነት የሚቀናበር ከመሆኑ አኳያ እዚያ ያሉት የህወሓት ሎሌዎች ውይይቱንም ሆነ ስብሰባውን በዳስፖራው ስም በደጋፊዎቻቸውና በአፍቃሪ ህወሓቶች ጠለፋ እንዳያካሂዱበት ካሁኑ ጠንቅቆ በመጠበቅ አስፈላጊውን የቤት ሥራ መሥራት እንደሚገባ ጎልጉል ያነጋገራቸው የዳያስፖራ አካል ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, diaspora, Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    May 26, 2018 10:35 pm at 10:35 pm

    በምን ነጥብ ላይ?? በህገ መንግሥቱ? በመሬት ሥሪት? በክልላዊ ኣስተዳደር?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule