• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠ/ሚ/ሩ በአሜሪካ ከወሳኝ ኢትዮጵያውያን ጋር ሊነጋገሩ ነው

May 25, 2018 03:12 pm by Editor 1 Comment

በኢህአዴግ የተሰየሙት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ በሰኔ ወር መገባደጃ አካባቢ ወደ አሜሪካ ጉዞ እንደሚያደርጉ ታወቀ። በቆይታቸው ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ በተለይ በሰላማዊ መንገድ ትግል ከሚያደርጉ ኢትዮጵያውያን ጋር በግልና በቡድን በመገናኘት ሊነጋገሩ እንደሚችሉ ተነግሯል።

በህወሓት/ኢህአዴግ ስያሜ የጠቅላዩን መንበር የተቆናጠጡት ዓቢይ አህመድ ላለፉት በርካታ ሳምንታት በአገር ውስጥ እና በአጎራባች አገራት ጉብኝቶችን ሲደርጉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቀጣይ የተያዘው መርሃግብር ወደ አውሮጳና አሜሪካ ጉዞ ማድረግ እንደሚሆን መረጃዎች ሲወጡ ነበር። ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ የጠቅላይ ሚ/ሩ የአሜሪካ ጉብኝት መረጃ ቀደም ብሎ የደረሰው ቢሆንም በወቅቱ የተባለው በሰኔ ወር መገባደጃ ወይም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ላይ ንግግር ለማድረግ በመስከረም አካባቢ ሲመጡ ሊሆን ይችላል የሚለው ነበር።

ዛጎል ታማኝ ምንጮቼ ያደረሱኝ መረጃ ነው በሚል በድረገጹ ላይ እንደገለጸው ጠ/ሚ/ሩ “ሰኔ 26 ወይም 27 ወደ አሜሪካ እንደሚያቀኑ” ተናግሯል። ሲቀጥልም የዓቢይ አህመድ ጉብኝት “በአሜሪካ በኩል ሙሉ ድጋፍ ያለውና አስፈላጊው ሁሉ ትብብር የሚደረግለት” መሆኑን አስታውቋል።

“በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ አዙሪት ያሳሰባት አሜሪካ በአገሪቱ የሰከነ የፖለቲካ ለውጥ እንዲኖር፣ ለዚሁም ተግባራዊነት ድጋፍ የምታደርግ፣ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ይህንን ለውጥ የማይቀበል ከሆነ ኮሮጆውን እስከማድረቅ የሚያደርስ እርምጃ እንደምትወስድ እያስጠነቀቀች መቆየቷ ይታወሳል። በሂደት ላይ ያሉ የህግ ጉዳዮችም አሉ። በዚሁ ቅኝት መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የአሜሪካ ጉዞ በዲያስፖራውና በመንግሥት በኩል ያለውን ልዩነት ለማርገብ፣ የወደፊቱን የለውጥ ሂደት የማስረዳትና በዝርዝር የማሳየት እንዲሁም አፋኝ የሚባሉት ህጎችን አስመልክቶ የሚደረገውን ማሻሻል በይፋ የማሳወቅ ነው። ተያይዞም አገራቸው መግባት ለሚፈልጉ በይፋ ዋስትና የሚሰጥ ግብዣ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።”

ጊዜው ሲደርስ የሚታወቅ ቢሆንም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የጉብኝት ወቅት በዳስፖራው ፖለቲካ ላይ በጉልህ የሚታወቁ በተለይም በሰላማዊ (ነውጥ አልባ) መንገድ ትግላቸውን ለዓመታት ሲያካሂዱ ከነበሩ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር ይገናኛሉ ተብሏል። እነዚህም በድርጅት ተደራጅተውም ይሁን በግላቸው በአገራቸው ጉዳይ ላይ የሚወተውቱትን እንደሚካትት ታውቋል።

“በዚሁ መሰረት ውይይቱ ከመዘላለፍ፣ ከሁከትና ውጤት ከማያስገኝ እንከኖች የጸዳ ይሆን ዘንድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንን” ዛጎል የመረጃ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። ሲቀጥልም “(የዜናው አቀባዮች) ስለ አጠቃላዩ ዝግጅት ከመናገራቸው ውጪ ስለሚደረገው ዝግጅት በዝርዝር አላብራሩም፤ የአሜሪካ ሚና ምን እንደሚሆንም አላስታወቁም” ብሏል።

የጠቅላዩን ጉዞ በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ ወገኖች ጉብኝቱን እንደ መልካም ዕድል በመጠቀም ለበጎ ውጤት እንጠቀምበት በማለት ይመክራሉ። ጠቅላይ ሚ/ር ዓቢይ አህመድ የዳያስፖራውን ኃይል በሚገባ የተገነዘቡና ይህንንም በአደባባይ የተናገሩ መሆናቸውን የሚጠቅሱ ክፍሎች ዳያስፖራው ካለው ሙሉ የመናገር መብት አኳያ አገር ቤት ያለው ኢትዮጵያዊ በድፍረት ሊናገር የማይችለውን በማንሳት ለወገኑ ያለውን ተቆርቋሪነት ማሳየት ይገባል ይላሉ። ከዚህ በፊት የህወሓት ኃላፊዎች በድብቅ መጥተው በድብቅ መሄዳቸው አግባብነት የለውም በሚል ትልቅ ተቃውሞ ይደርስባቸው እንደነበር የሚያስታውሱ ወገኖች በገሃድ እንወያይ የሚል መሪ ሲመጣ በጭፍን ከመቃወም ይልቅ “እኛም የምንፈልገው ይህንን ነበር” በሚል በሰከነ መንፈስ የጉብኝቱ አካል መሆን ይገባቸዋል በማለት ሃሳብ ይሰጣሉ።

ጉብኝቱ ዋሽንግቶን ዲሲ በሚገኘው ኤምባሲ የበላይ ኃላፊነት የሚቀናበር ከመሆኑ አኳያ እዚያ ያሉት የህወሓት ሎሌዎች ውይይቱንም ሆነ ስብሰባውን በዳስፖራው ስም በደጋፊዎቻቸውና በአፍቃሪ ህወሓቶች ጠለፋ እንዳያካሂዱበት ካሁኑ ጠንቅቆ በመጠበቅ አስፈላጊውን የቤት ሥራ መሥራት እንደሚገባ ጎልጉል ያነጋገራቸው የዳያስፖራ አካል ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, diaspora, Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    May 26, 2018 10:35 pm at 10:35 pm

    በምን ነጥብ ላይ?? በህገ መንግሥቱ? በመሬት ሥሪት? በክልላዊ ኣስተዳደር?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule