• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ

February 21, 2017 10:00 pm by Editor Leave a Comment

የካቲት 13፣ 2009 ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና የጎንደር ከተማ ከንቲባ ተቀባ ተባባል በአንድነት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን ባንጋገሩበት ወቅት ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት የለም” እየተባለ የሚነገረውን የሚያረጋግጥ አስተያየት መስጠቱ ተስማ።

እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ከተሰብሳቢው ለደመቀ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውለታል፡፡ ፋና ይፋ ባያደርገውም በውይይቱ የከረሩ ጉዳዮች መነሳታቸው ከአንዳንድ ምንጮች ለመረዳት ተችሏል፡፡

ደመቀ በገለጻው “ጥልቅ ተሃድሶ፤ መልካም አስተዳደር፤ የህዝብ ተሳትፎ፤ …” በማለት ተሰብሳቢውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርግም የተቻለው እንዳልሆነ ፋና ራሱ ከዘገበው ለመረዳት ቻላል፡፡

“… ተሃድሶው አንዱን አመራር ወደ ሌላ ስፍራ ከመቀየር የዘለለ ለውጥ እያመጣ አይደለም” የሚል አስተያየት ከውይይቱ ተሳታፊዎች መነሳቱን የጠቆመው የፋና ዜና ለዚህ ጥያቄ ደመቀም ሆነ ገዱ ወይም ከንቲባው የመለሱትን አልዘገበም።

ሁለቱ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት መድረኩ ላይ እርስበርሱ የሚጣረስ ሃሳብ ሲሰጡ ተሰምተዋል፡፡ ደመቀ “ባለፉት ወራትም ሀገሪቱ ወደነበረችበት ሰላም መመለስ ችላለች” በማለት ቢናገርም ገዱ አንዳርጋቸው በበኩሉ፥ “ባለፉት ስድስት ወራት በጎንደር የኢንቨስትመንት ጥያቄ ቀንሷል፤ ስለ ጎንደር የሚነሱ አሉባልታዎችን ወደጎን በመተው የከተማዋን ገፅታ መቀየር ይኖርብናል” በማለት የደመቀን “ሰላም ነው” ንግግር ውጤት አልባ አድርጎታል።

ከዚህ በተጨማሪም ገዱ አስተዳድረዋለሁ በሚለው ክልል እርሱ “አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች” በማለት የጠቀሳቸው “የሚጠበቅባቸውን ግብር እየከፈሉ” አይደሉም በማለት መናገሩን የዜና ዘገባው አስረድቷል።

“መንግሥት ባለበት እና የመንግሥት መዋቅር ባለበት ቦታ ሕግ አለ፤ በሕጉ መሠረት ግብር ይሰበሰባል፤ ነገር ግን በሕዝብ አስተሳሰብ ውስጥ መዋቅር ፈርሷል፤ መንግሥት የለም፤ ወዘተ የመሳሰሉ አስተሳሰቦች በሚሰርጹበት ጊዜ ህዝብ እንደዜጋ የሚጠበቅበትን ግብር አልከፍልም ወደማለት ይሄዳል” በማለት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሕግ ባለሙ ለጎልጉል አስያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ይህ የገዱ አንዳርጋቸው ንግግር ጎልጉል (የካቲት 13፤ 2009ዓም፤ February 20, 2017) ከሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ መረጃ በመሰብሰብ ያጠናቀረውን ዘገባ የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ዘገባው ህንን ይል ነበር፤

“… በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል አስቸጋሪ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ያላቸዉን ስፍራዎች በተለይም ታች አርማጭሆ፣ ምዕራብ አርማጭሆ፣ ጠገዴ፣ መተማ፣ ወገራ፣ ምዕራብና ምስራቅ በለሳ ወረዳዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮች በዋናነት  የእምቢተኛነቱ እምብርት እንደሆኑ የሚጠቀሱ ሲሆን፣ በዝርዝር ባይገለጽም ጎጃም አንዳንድ አካባቢዎችና ሰሜን ሸዋ የኅቡዕ ጥቃት እንደሚፈጸም ውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። በሰሜኑ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል በሚገኙ ወረዳዎች ከአርሶ አደሮች መሰብሰብ የነበረበት የ2008 ዓ.ም የመሬት ግብር እና የማዳበሪያ ዕዳ እስካሁን ሊሰበሰብ አለመቻሉ ትልቁ የመዋቅር መሰበር አመላካች ተደርጎ መወሰዱን የጎልጉል የአካባቢው መረጃ አቀባይ አስታውቋል። መረጃ አቀባዩ እንዳለው ራቅ ባሉ የገጠር ቀበሌዎች የማህበራዊ ተቋማት (ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማት፣ የግብርና ጣቢያዎች) ወደ ቀድሞ መደበኛ ሥራቸዉ መመለስ አልተቻላቸውም።”

ከበርካታ ቦታዎች ውጥረት ውስጥ የገባው ህወሃት/ኢህአዴግ መጪውን የማሟያ ምርጫ ለማለፍ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተጋ ይገኛል፡፡ በዳያስፖራ ያለው ኃይል ተባብሮ መሥራት አቅቶት ነው እንጂ ከሕዝባዊ እምቢተኝነቱ በኋላ ይህንንም ያህል አይቆይም የተባለለት ህወሃት/ኢህአዴግ ዕርቅ፣ ሽምግልና፣ ድርድር፣ አብሮ መሥራት፣ ህዝባዊ ተሳትፎ፣ ሕገ መንግሥት ማሻሻል፣ … የመሳሰሉ ዕቅዶችን ወጥኖ ሕዝቡን ለማሳመን እየጣረ ነው፡፡

በአማራና በኦሮሚያ በግፍ ያፈሰሰውን ደም በገንዘብ መተካት የሚችል ይመስል ለወጣቶች ሥራ ዕድል እፈጥራለሁ እያለ ነው፡፡ በዚሁ ጎንደር ላይ በተደረገው ስብሰባ እነ ደመቀ በመላው ኢትዮጵያ 3ሚሊዮን፤ በአማራ ክልል ደግሞ ለ800 ሺህ ወጣቶች የሥራ እድል እንፈጥራለን በማለት ህዝቡን ለመደለል ሲሞክሩ ተሰምተዋል።

የዛሬ ዓመት አካባቢ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ ላፈሰሰው ደም በ2.4 ቢሊዮን ብር ሥራአጥ ወጣቶችን ባለሃብት አደርጋለሁ በማለት በኦህዴድ በኩል ሲያስነግር መቆየቱ የተዘገበ ጉዳይ ነበር፡፡

“መንግሥት የለም” የሚለው አካሄድ በሕዝቡ ዘንድ የፈጠረው የስነልቦና ተጽዕኖ ህወሃት/ኢህአዴግን ክፉኛ ችግር እንደሆነበት ከተለያዩ ቦታዎች የሚሰሙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule