• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ

February 21, 2017 10:00 pm by Editor Leave a Comment

የካቲት 13፣ 2009 ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና የጎንደር ከተማ ከንቲባ ተቀባ ተባባል በአንድነት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን ባንጋገሩበት ወቅት ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት የለም” እየተባለ የሚነገረውን የሚያረጋግጥ አስተያየት መስጠቱ ተስማ።

እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ከተሰብሳቢው ለደመቀ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውለታል፡፡ ፋና ይፋ ባያደርገውም በውይይቱ የከረሩ ጉዳዮች መነሳታቸው ከአንዳንድ ምንጮች ለመረዳት ተችሏል፡፡

ደመቀ በገለጻው “ጥልቅ ተሃድሶ፤ መልካም አስተዳደር፤ የህዝብ ተሳትፎ፤ …” በማለት ተሰብሳቢውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርግም የተቻለው እንዳልሆነ ፋና ራሱ ከዘገበው ለመረዳት ቻላል፡፡

“… ተሃድሶው አንዱን አመራር ወደ ሌላ ስፍራ ከመቀየር የዘለለ ለውጥ እያመጣ አይደለም” የሚል አስተያየት ከውይይቱ ተሳታፊዎች መነሳቱን የጠቆመው የፋና ዜና ለዚህ ጥያቄ ደመቀም ሆነ ገዱ ወይም ከንቲባው የመለሱትን አልዘገበም።

ሁለቱ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት መድረኩ ላይ እርስበርሱ የሚጣረስ ሃሳብ ሲሰጡ ተሰምተዋል፡፡ ደመቀ “ባለፉት ወራትም ሀገሪቱ ወደነበረችበት ሰላም መመለስ ችላለች” በማለት ቢናገርም ገዱ አንዳርጋቸው በበኩሉ፥ “ባለፉት ስድስት ወራት በጎንደር የኢንቨስትመንት ጥያቄ ቀንሷል፤ ስለ ጎንደር የሚነሱ አሉባልታዎችን ወደጎን በመተው የከተማዋን ገፅታ መቀየር ይኖርብናል” በማለት የደመቀን “ሰላም ነው” ንግግር ውጤት አልባ አድርጎታል።

ከዚህ በተጨማሪም ገዱ አስተዳድረዋለሁ በሚለው ክልል እርሱ “አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች” በማለት የጠቀሳቸው “የሚጠበቅባቸውን ግብር እየከፈሉ” አይደሉም በማለት መናገሩን የዜና ዘገባው አስረድቷል።

“መንግሥት ባለበት እና የመንግሥት መዋቅር ባለበት ቦታ ሕግ አለ፤ በሕጉ መሠረት ግብር ይሰበሰባል፤ ነገር ግን በሕዝብ አስተሳሰብ ውስጥ መዋቅር ፈርሷል፤ መንግሥት የለም፤ ወዘተ የመሳሰሉ አስተሳሰቦች በሚሰርጹበት ጊዜ ህዝብ እንደዜጋ የሚጠበቅበትን ግብር አልከፍልም ወደማለት ይሄዳል” በማለት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሕግ ባለሙ ለጎልጉል አስያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ይህ የገዱ አንዳርጋቸው ንግግር ጎልጉል (የካቲት 13፤ 2009ዓም፤ February 20, 2017) ከሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ መረጃ በመሰብሰብ ያጠናቀረውን ዘገባ የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ዘገባው ህንን ይል ነበር፤

“… በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል አስቸጋሪ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ያላቸዉን ስፍራዎች በተለይም ታች አርማጭሆ፣ ምዕራብ አርማጭሆ፣ ጠገዴ፣ መተማ፣ ወገራ፣ ምዕራብና ምስራቅ በለሳ ወረዳዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮች በዋናነት  የእምቢተኛነቱ እምብርት እንደሆኑ የሚጠቀሱ ሲሆን፣ በዝርዝር ባይገለጽም ጎጃም አንዳንድ አካባቢዎችና ሰሜን ሸዋ የኅቡዕ ጥቃት እንደሚፈጸም ውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። በሰሜኑ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል በሚገኙ ወረዳዎች ከአርሶ አደሮች መሰብሰብ የነበረበት የ2008 ዓ.ም የመሬት ግብር እና የማዳበሪያ ዕዳ እስካሁን ሊሰበሰብ አለመቻሉ ትልቁ የመዋቅር መሰበር አመላካች ተደርጎ መወሰዱን የጎልጉል የአካባቢው መረጃ አቀባይ አስታውቋል። መረጃ አቀባዩ እንዳለው ራቅ ባሉ የገጠር ቀበሌዎች የማህበራዊ ተቋማት (ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማት፣ የግብርና ጣቢያዎች) ወደ ቀድሞ መደበኛ ሥራቸዉ መመለስ አልተቻላቸውም።”

ከበርካታ ቦታዎች ውጥረት ውስጥ የገባው ህወሃት/ኢህአዴግ መጪውን የማሟያ ምርጫ ለማለፍ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተጋ ይገኛል፡፡ በዳያስፖራ ያለው ኃይል ተባብሮ መሥራት አቅቶት ነው እንጂ ከሕዝባዊ እምቢተኝነቱ በኋላ ይህንንም ያህል አይቆይም የተባለለት ህወሃት/ኢህአዴግ ዕርቅ፣ ሽምግልና፣ ድርድር፣ አብሮ መሥራት፣ ህዝባዊ ተሳትፎ፣ ሕገ መንግሥት ማሻሻል፣ … የመሳሰሉ ዕቅዶችን ወጥኖ ሕዝቡን ለማሳመን እየጣረ ነው፡፡

በአማራና በኦሮሚያ በግፍ ያፈሰሰውን ደም በገንዘብ መተካት የሚችል ይመስል ለወጣቶች ሥራ ዕድል እፈጥራለሁ እያለ ነው፡፡ በዚሁ ጎንደር ላይ በተደረገው ስብሰባ እነ ደመቀ በመላው ኢትዮጵያ 3ሚሊዮን፤ በአማራ ክልል ደግሞ ለ800 ሺህ ወጣቶች የሥራ እድል እንፈጥራለን በማለት ህዝቡን ለመደለል ሲሞክሩ ተሰምተዋል።

የዛሬ ዓመት አካባቢ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ ላፈሰሰው ደም በ2.4 ቢሊዮን ብር ሥራአጥ ወጣቶችን ባለሃብት አደርጋለሁ በማለት በኦህዴድ በኩል ሲያስነግር መቆየቱ የተዘገበ ጉዳይ ነበር፡፡

“መንግሥት የለም” የሚለው አካሄድ በሕዝቡ ዘንድ የፈጠረው የስነልቦና ተጽዕኖ ህወሃት/ኢህአዴግን ክፉኛ ችግር እንደሆነበት ከተለያዩ ቦታዎች የሚሰሙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule