• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ

February 21, 2017 10:00 pm by Editor Leave a Comment

የካቲት 13፣ 2009 ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና የጎንደር ከተማ ከንቲባ ተቀባ ተባባል በአንድነት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን ባንጋገሩበት ወቅት ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት የለም” እየተባለ የሚነገረውን የሚያረጋግጥ አስተያየት መስጠቱ ተስማ።

እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ከተሰብሳቢው ለደመቀ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውለታል፡፡ ፋና ይፋ ባያደርገውም በውይይቱ የከረሩ ጉዳዮች መነሳታቸው ከአንዳንድ ምንጮች ለመረዳት ተችሏል፡፡

ደመቀ በገለጻው “ጥልቅ ተሃድሶ፤ መልካም አስተዳደር፤ የህዝብ ተሳትፎ፤ …” በማለት ተሰብሳቢውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርግም የተቻለው እንዳልሆነ ፋና ራሱ ከዘገበው ለመረዳት ቻላል፡፡

“… ተሃድሶው አንዱን አመራር ወደ ሌላ ስፍራ ከመቀየር የዘለለ ለውጥ እያመጣ አይደለም” የሚል አስተያየት ከውይይቱ ተሳታፊዎች መነሳቱን የጠቆመው የፋና ዜና ለዚህ ጥያቄ ደመቀም ሆነ ገዱ ወይም ከንቲባው የመለሱትን አልዘገበም።

ሁለቱ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት መድረኩ ላይ እርስበርሱ የሚጣረስ ሃሳብ ሲሰጡ ተሰምተዋል፡፡ ደመቀ “ባለፉት ወራትም ሀገሪቱ ወደነበረችበት ሰላም መመለስ ችላለች” በማለት ቢናገርም ገዱ አንዳርጋቸው በበኩሉ፥ “ባለፉት ስድስት ወራት በጎንደር የኢንቨስትመንት ጥያቄ ቀንሷል፤ ስለ ጎንደር የሚነሱ አሉባልታዎችን ወደጎን በመተው የከተማዋን ገፅታ መቀየር ይኖርብናል” በማለት የደመቀን “ሰላም ነው” ንግግር ውጤት አልባ አድርጎታል።

ከዚህ በተጨማሪም ገዱ አስተዳድረዋለሁ በሚለው ክልል እርሱ “አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች” በማለት የጠቀሳቸው “የሚጠበቅባቸውን ግብር እየከፈሉ” አይደሉም በማለት መናገሩን የዜና ዘገባው አስረድቷል።

“መንግሥት ባለበት እና የመንግሥት መዋቅር ባለበት ቦታ ሕግ አለ፤ በሕጉ መሠረት ግብር ይሰበሰባል፤ ነገር ግን በሕዝብ አስተሳሰብ ውስጥ መዋቅር ፈርሷል፤ መንግሥት የለም፤ ወዘተ የመሳሰሉ አስተሳሰቦች በሚሰርጹበት ጊዜ ህዝብ እንደዜጋ የሚጠበቅበትን ግብር አልከፍልም ወደማለት ይሄዳል” በማለት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሕግ ባለሙ ለጎልጉል አስያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ይህ የገዱ አንዳርጋቸው ንግግር ጎልጉል (የካቲት 13፤ 2009ዓም፤ February 20, 2017) ከሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ መረጃ በመሰብሰብ ያጠናቀረውን ዘገባ የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ዘገባው ህንን ይል ነበር፤

“… በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል አስቸጋሪ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ያላቸዉን ስፍራዎች በተለይም ታች አርማጭሆ፣ ምዕራብ አርማጭሆ፣ ጠገዴ፣ መተማ፣ ወገራ፣ ምዕራብና ምስራቅ በለሳ ወረዳዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮች በዋናነት  የእምቢተኛነቱ እምብርት እንደሆኑ የሚጠቀሱ ሲሆን፣ በዝርዝር ባይገለጽም ጎጃም አንዳንድ አካባቢዎችና ሰሜን ሸዋ የኅቡዕ ጥቃት እንደሚፈጸም ውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። በሰሜኑ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል በሚገኙ ወረዳዎች ከአርሶ አደሮች መሰብሰብ የነበረበት የ2008 ዓ.ም የመሬት ግብር እና የማዳበሪያ ዕዳ እስካሁን ሊሰበሰብ አለመቻሉ ትልቁ የመዋቅር መሰበር አመላካች ተደርጎ መወሰዱን የጎልጉል የአካባቢው መረጃ አቀባይ አስታውቋል። መረጃ አቀባዩ እንዳለው ራቅ ባሉ የገጠር ቀበሌዎች የማህበራዊ ተቋማት (ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማት፣ የግብርና ጣቢያዎች) ወደ ቀድሞ መደበኛ ሥራቸዉ መመለስ አልተቻላቸውም።”

ከበርካታ ቦታዎች ውጥረት ውስጥ የገባው ህወሃት/ኢህአዴግ መጪውን የማሟያ ምርጫ ለማለፍ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተጋ ይገኛል፡፡ በዳያስፖራ ያለው ኃይል ተባብሮ መሥራት አቅቶት ነው እንጂ ከሕዝባዊ እምቢተኝነቱ በኋላ ይህንንም ያህል አይቆይም የተባለለት ህወሃት/ኢህአዴግ ዕርቅ፣ ሽምግልና፣ ድርድር፣ አብሮ መሥራት፣ ህዝባዊ ተሳትፎ፣ ሕገ መንግሥት ማሻሻል፣ … የመሳሰሉ ዕቅዶችን ወጥኖ ሕዝቡን ለማሳመን እየጣረ ነው፡፡

በአማራና በኦሮሚያ በግፍ ያፈሰሰውን ደም በገንዘብ መተካት የሚችል ይመስል ለወጣቶች ሥራ ዕድል እፈጥራለሁ እያለ ነው፡፡ በዚሁ ጎንደር ላይ በተደረገው ስብሰባ እነ ደመቀ በመላው ኢትዮጵያ 3ሚሊዮን፤ በአማራ ክልል ደግሞ ለ800 ሺህ ወጣቶች የሥራ እድል እንፈጥራለን በማለት ህዝቡን ለመደለል ሲሞክሩ ተሰምተዋል።

የዛሬ ዓመት አካባቢ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ ላፈሰሰው ደም በ2.4 ቢሊዮን ብር ሥራአጥ ወጣቶችን ባለሃብት አደርጋለሁ በማለት በኦህዴድ በኩል ሲያስነግር መቆየቱ የተዘገበ ጉዳይ ነበር፡፡

“መንግሥት የለም” የሚለው አካሄድ በሕዝቡ ዘንድ የፈጠረው የስነልቦና ተጽዕኖ ህወሃት/ኢህአዴግን ክፉኛ ችግር እንደሆነበት ከተለያዩ ቦታዎች የሚሰሙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule