* የተራዘመው የምህረት አዋጅ * የ90 ቀኑ ምህረት አዋጅ አስተምሮቱ .. * አጭሩን ጊዜ በአግባቡ ለመጠቀም .. * የበረራ ፈቃድ እና የአሻራ አሰጣጡ ተጠያቂ ማነው? * በቂ ድጋፍ ለማድረግ የሰው ሃይልን ስለማደራጀት .. * ስራው በማን ነው የሚሰራው? የዲፕሎማቶች? መኖሪያና የስራ ፈቃድ የሌላቸው ሳውዲን በ90 ቀን ውስጥ ለቀው እንዲወጡ የተሰጠው ቀነ ገደብ ለ30 ቀናት ተራዝሟል ። በሳውዲው ንጉሳዊ ቤተሰቦች አመራሮች ይሁንታ አግኝቶ በሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ ትዕዛዝ ማምሻውን በፖስፖርት የበላይ ዳይሬክተር በሜጀር ጀኔራል ሱሌማን የህያ ይፋ የሆነው መረጃ ይፋ ይፋ ሆኗል። ይፋ የሆነው የምህረት አዋጅ የ90 ቀኑ የምህረት አዋጅ ካለቀበት እአአ ከሰኔ 25 ጀምሮ እስከ ቀጣዩ ሐምሌ 25 ቀን 2017 ድረስ የሚቆይ እንደሆነው ታውቋል። ፖስፖርት የበላይ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል … [Read more...] about የሳውዲ የተራዘመ የምህረት አዋጅ እንዴት እንጠቀምበት?
Archives for June 2017
ይድረስ ለአርበኛው ጸሐፊ ዕዝራ ዘለቀ (ዕዝራ አስቻለው ዘለቀ)
በተከታታይ የጻፍካቸውን ሁለት ግሩም መጣጥፎች በፍቅር አነበብኳቸው፡፡ በነዚህ ጽሑፎች እንደተረዳሁት ጥሩ አንባቢ ነህ፤ የብዕር አጣጣልህም ውብ ነው፡፡ ሀገርህንም እንደምትወድ በጽሑፍህ ብቻ ሣይሆን በረሃ መውረድህ ራሱም በቂ ምሥክር ነው፡፡ ማቄን ጨርቄን ሳትል ለአንዲት እናትህ ኢትዮጵያ ስትል እያሳለፍከው ያለኸውን መከራና ስቃይ መረዳት እችላለሁና የእምዬ አምላክ ይከተልህ፡፡ አንተን ብቻም ሣይሆን ለተመሳሳይ በጎ ዓላማ የተሰለፋችሁትን ጓዶችህንም ሁሉ ፈጣሪ ይጠብቃችሁ፤ ያሰባችሁትንም ያሳካላችሁ፡፡ በረከቱ የሁላችንም ነውና፡፡ እኛም በጸሎት ከጎናችሁ አለን፡፡ ይሁንና በግልጽ መነጋገር ለሁሉም ወገን የሚበጅ እንደመሆኑ ከጽሑፍህ ለመረዳት የሞከርኩትን በግልጽ የተነገሩና ያልተነገሩ አንዳንድ ነጥቦችን ማንሳት ወደድኩ፡፡ ከብረት ዝገት ከሰው ስህተት እንደመገኘቱ ተሳስቼ የተረዳሁብህ ነገር … [Read more...] about ይድረስ ለአርበኛው ጸሐፊ ዕዝራ ዘለቀ (ዕዝራ አስቻለው ዘለቀ)
…ቅምሻ…
በቀረችው ትንፋሽ ... አገሩን አስታሞ ... እሱም እንደ ሌሎች ... ሊያሸልብ ነው ደግሞ! .......................................................... እንደ ሸረሪት ድር ... ነገር ተወሳስቦ... እውነትን ማን ያውጣት ... ከመሃከል ስቦ...? ......................................................... አገር ተሰቃየች...ጣሯ ብቻ በዛ.. ግማሹ እየሸጣት...ግማሹ እየገዛ...! ......................................................... የሰው ዘር መገኛ ... ብለው ሲጎበኙን... በብሄር ተጠምደን ... ተከፋፍለን አዩን:: ......................................................... ማን እንደዘረፈኝ ... ልቤ እያስተዋለ የለመደው … [Read more...] about …ቅምሻ…
“ተዋከበና!”
ለቴዲ አፍሮ ዉበት ያምራል እንዴ? ቁንጅናስ ያምራል? አንዳንድ ጊዜ ሰዎች “I didn’t do nothing” ወይም “I didn’t say nothing” ሲሉ መስማት አዲስ አይደለም። እጅግ በጣም አልፎ አልፎ ቢሆንም፣ እንግሊዝኛ ያፍ መፍቻ ቋንቋቸው የሆኑ ሰዎችም ሲሉት ይሰማሉ። በቋንቋው ህግ መሰረት ይህ አ/ነገር ጎደሎ ነው። “double negative” የሚፈጥረው የ“positive” ትርጉም/ፍቺ ግድፈት ይመስለኛል። ሁለት ነጌቲቭ (“didn’t” እና “nothing”) ቃላት/ሃረጎች፣ አንዳንዴ ፖዚቲቭ ትርጉም የሚያስከትሉ መሆኑ ነው። “I didn’t do nothing” ወይም “I didn’t say nothing” በሚሉት ዓ.ነገሮች ውስጥ ለማለት የተፈለገው “ምንም አላደረግሁም”/“ምንም አልተናገርኩም” ሲሆን፣ ትርጉሙ ግን የተገላቢጦሹ ሊሆን እንኳን ባይችልም፣ በጣም ያደናግራል። እናም … [Read more...] about “ተዋከበና!”
አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ አወጣ
የዚህች ጦማር ዋና ዓላማ፡ “ያዲስ አበባው ሲኖዶስ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ከቀሩት አኀት አብያተ ክርስቲያናት ተነጥላ ከሀያ በላይ ስህተት ሰርታለችና ትመርመር የሚል ክስና ወቀሳ አቀረበ” ብሎ ሀራ ዘተዋህዶ ባቀረበው ዜና፤ ግራ የተጋባችሁ ክርስቲያኖች፤ “በአኀት አብያተ ክርስቲያናት ሐዋርያዊ ትውፊት አንጻር እንዴት ትመለከተዋለህ“ ብላችሁ ላቀረባችሁልኝ ጥያቄ ለመመለስ ነው። ይህ የቀረበው ሀሳብ የሀራ ዘተዋህዶ ድረ ገጽ ፈጠራ ከሆነ፡ ”አባት ሆ ይ!እኔ በአንተ አንተ በእኔ እንዳለህ እነርሱም በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ”(ዮሐ 17፡ 21“)በሚለው ክርስቶሳዊ ቃል፤ አንድነታቸውን አጽንተው በኖሩት በአኀት አብያተ ክርስቲያናት ላይ እየዘመተ ነው ማለት ይቻላል። ምናልባትም ከጥንት ጀምሮ እነዚህን ጥንታውያት አብያተ ክርስቲያናትን ለማጥፋት የሚታገሉት የሰባልዮስ ወይም የአርዮስ ተከታዮች ሊሆን … [Read more...] about አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ አወጣ
አስናቀ እንግዳ ይድረስህ ምስጋና
አስናቀ እንግዳ ገና ከጠዋቱ፡ ጎህ እንደቀደደ፡ ገና በማለዳ ከቆላ ከደጋ ተሸክሞ ዕዳ ከደቡብ ከሰሜን ከምዕራብ ከምሥራቅ ዘልቆ በመደዳ ለሀገሩ ለቀዬው ሰው እንዳይሆን ባዳ አበው ያወረሱት ታሪክ እንዳይጠፋ መላውን ዕድሜውን ያለ ቀና ደፋ ሀሰትን ኮንኖ፡ ሀቅን ይሚያፋፋ ምዝበራን ተጋፍጦ፡ ለሕዝብ የተዋጋ አልገዛም ያለ ላምባገነን መንጋ ሕይወቱን አስተምሮ፡ ሕይወትን የኖረ ንዋይ፡ ሀብት፡ ዝና ከቶ ያላፈቀረ የዕድሜ ባለጸጋው ጀግናው የእንግዳ ልጅ ይድረስህ ምስጋና ከዚህ ካሲምባ ደጅ ከዘመድ ከወዳጅ። ያገር ፍቅር ስሜት ውስጡን እየበላው የወገኑ ብሶት እያብከነከነው የሰንደቁ ክብር እያንገበገበው ኢትዮጵያ ታሪኳ ተከብሮ እንዲኖር አንድነቷ ጸንቶ እንዲሆነን ማገር ሉዓላዊነቷ ጸንቶ እስከዘላለም የሕዝቧ አንድነት እንዲኖር እስካለም ታግሎ ያታገለ፡ መካሪ … [Read more...] about አስናቀ እንግዳ ይድረስህ ምስጋና
የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!
ሰዎች መልካም ሢሠሩና ሲናገሩ ማመስገን፣ መጥፎ ሢሠሩና ሲናገሩ ደግሞ መምከርና መገሰጥ ተገቢ ነው። ምንጊዜም ሁሉም ሰው ሕይዎቱን ሙሉ ስሕተት ብቻ እየሠራ አይኖርም። መልካም ነገሮችም ይሠራል። ልዩነት የሚኖረው የትኛው ሥራው ነው የሚያመዝነው? መልካሙ ወይስ መጥፎ የሚለውን መመዘኑ ላይ ነው። በዚህ ረገድ የሻለቃ ዳዊትን ሥራዎች መዝኖ፤ የማሞገሱም ሆነ የመውቀሱ ተግባር፣ እርሳቸውን የሚያውቁ፣ አብረዋቸው የሠሩ፣ የትaምህርትና የሥራ ባልደረቦቻቸው ተግባር ይሆናል። ሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ለዐማራ ነገድ ድምፅ ለመሆን የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ ያለ ድርጅት ነው። ስለዚህ ሻለቃውን በዚህ ንግግራቸው፣ ላለፉት 5 ዓመታት ሲጮኽባቸው የነበሩ አንኳር ጉዳዮችን እያነሱ፣ ዐማራውን ሲያወግዙ፣ በጠላትነት ፈርጀው የዘር ፍጅት በፈጸሙ ግለሰቦችና ስብስቦች ፊት በኩራት ቆመው በመናገራቸው ከልብ … [Read more...] about የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
መርዛማ ፍሬ 11፡ የታሪክ መቃብር! በስሜት በሚነዳ የዘውግ ፖለቲካ ውስጥ ታሪክ ትልቅ ማገዶ ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ታሪክ አካታችነት ባለው መልኩ በአጎልባች ሚና (ብሔራዊ ተዋፅዖ) መፃፍ እየተገባው ምክንያታዊነትን አስመንኖ የልዩነት ሃረጎችን ብቻ በመምዘዝ በየአቅጣጫው የሚፃፍ መሆኑ ከተካረረ ሙግት ሊፀዳ አልቻለም። መዋቅራዊ ድጋፍ ባለው መልኩ የታሪክ ሙግቱ እየተካረረ በመምጣቱ ብሔራዊ ርዕይ ርቆን የመንደር አጥር እስከመስራት ደርሰናል። ደርግ በየትኛውም ያህል መጠን አምባገነንና ጨፍጫፊ ሆኖ ቢገኝም የኢትዮጵያን ታሪክ ሲንቅና ሲያንቋሽሽ አልተገኘም። ከቶውንም ለብሔራዊ ርዕይ መፍጠሪያነት እንደግብዓት ተጠቅሞበታል። ከመነሻው ጀምሮ ኢትዮጵያዊ ስሜትን (የጋራ ማንነትን) በመካድ ራሱን ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር አድርጎ የሰየመው ህወሓት፣ የአገሪቱን የረዥም ጊዜ ታሪክ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
አንድነት ከማን ጋር? አንድነት ለምን? አንድነት መቼ?
ዐማራው በባህሉ፣ በሥነ-ልቦናውና በፖለቲካ ታሪኩ እንዲሁም በሚጋራቸው የወል ዕሴቶቹ፣ በእሱነቱና በኢትዮጵያዊነቱ መካከል የተሰመረ ልዩነት ባለመኖሩ፣በዘር ጠላትነት ተፈርጆ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ሲፈጸምበት ፣ወንጀሉ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጸም ነው በማለት፣ለምን? እንዴት? ብሎ ለመጠየቅ ከሁለት ዓሥርተ ዓመታት በላይ እንደፈጀበት በግልጽ ይታወቃል። ይህም ዘረኛው የትግሬ ወያኔ ቡድንና አጋሮቹ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ ኢትዮጵያ እንዲጠፉ ሠፊ ዕድልና አጋጣሚ እንዲያገኙ ረድቷቸዋል። ይህን ያህል ቁጥር ያለው ከትግሬ፣ ከሶማሌ፣ ከጉራጌ፣ ከሲዳማ፣ ከወላይታ ቢጠፋ ሁሉም የነገዱ አባሎች ጠፉ ማለት ነበር። ዐማራው ይኸን ያህል ቁጥር የሰው ኃይል ጠፍቶበት፣ ምንም ያልመሰለው ከጣና ሐይቅ በጭልፋ ውኃ የመቀነስ ያህል ሆኖ በመታየቱ፣ የሁሉንም የዐማራውን ነገድ ጆሮ … [Read more...] about አንድነት ከማን ጋር? አንድነት ለምን? አንድነት መቼ?
የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?
አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል። የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው። ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር … [Read more...] about የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?