የትግራይ ሕዝብ “ነጻ አውጡኝ” ብሎ ሳይሰይማቸው፣ ሳይመርጣቸው፣ ሳይጠይቃቸው፣ ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብለው የሰየሙ ወንበዴዎችና ሽፍቶች የምኒልክ ቤተመንግሥት ከገቡ 26 ዓመታት ተቆጥረዋል። በቂም፣ በበቀል፣ በክፋትና በኢሞራላዊ ተግባራት የተሞሉ፤ ኢትዮጵያዊ መሆናቸው ፈጽሞ የሚያጠራጥር፤ ማንነታቸው ይህ ነው ተብሎ የማይታወቅ፤ በሐሰት ስም ከበረሃ እስከ ቤተመንግሥትና ዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የታዩ፤ በሐሰት ፕሮፓጋንዳ የትግራይን ሕዝብ ያስጨፈጨፉ (ሐውዜንን ይጠቅሷል)፤ ሲነሱ አንዳች ገንዘብ ያልነበራቸው መናጢዎች በበረሃ የድሃ ረሃብተኛ እህል ዘርፈው በመሸጥ፤ ሥልጣን ከያዙ በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያን ሐብት ሙልጭ አድርገው ዘርፈው ሲያበቁ “የራሳችን ንብረት ነው” በማለት ኤፈርት የሚባል የወንበዴዎች ሃብት ማከማቻ ቋት የፈጠሩ፤ ከበረሃ እስከ መንግሥታዊ ሥልጣን … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመንግሥት ውሸት፣ የሃይማኖት ተቋማት ውድቀት፣ … (ክፍል ሦስት)
Archives for May 2017
“ዕድሜ ለግንቦት ሃያ…”
በግንቦት 20 ዋዜማ ዋልታ ቴሌቪዥንን እያየሁ ነው። ጋዜጠኛው ዝግጅቱን ከአመት አመት በማይቀየሩት መፈክሮች (ለምሳሌ "ግንቦት 20 የህዝቦች ሁሉ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ቀን ነው) ጀመረና፣ ዛሬም በጭንቅላቴ ውስጥ የሚፈነጩትን ጥያቄዎች ዘርዝሬ ለማሰብ እንኳን እድል ሳይሰጠኝ፣ "ከግንቦት 20 ወዲህ የተወለዱ ልጆች ስለዚህ ቀን ምን ያውቃሉ?" ብሎ ለመጠየቅ በየትምህርት ቤቱ መዞር ጀመረ። የ17 አመቷ ቆንጅዬ ልጅ በፍፁም የራስ መተማመን፣ " እኛ ባንደርስበትም በአባቶቻችንና በእናቶቻችን ላይ ላይ የነበረው ጭቆና የቀረበት ቀን ነው" አለች። ከልጅቱ በኋላ አንድም ሳያነቅፋቸው ቀኑን በኢቲቪኛ፣ በፋናኛ እና በዋልታኛ የሚተነትኑ ወጣቶችን ሳይ ቆይቼ፤ ሌላ የ18 አመት ልጅ ብቅ ብሎ " ግንቦት ሃያ ባይኖር እኔም እዚህ አልገኝም ነበር" ሲል ውሃዬን ተጎንጭቼ ዋልታን … [Read more...] about “ዕድሜ ለግንቦት ሃያ…”
“ሲሾም ያልበላ… ድሮ ቀረ” — [የግንቦት 20 ወግ]
አንጀት አርስና አንገት አስደፊ አስተያየት አንጀታቸው ካረረ ሽማግሌ። በመስሪያ ቤታችን የግንቦት 20 በዓልን እያከበርን ነው። ክቡር ሰብሳቢው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ብዙ የበዙና የተባዙ የለውጥ ማሳያዎችን ሲናገሩ ቆይተው በመጨረሻ እንዲህ አሉ፡- "...ባጭሩ ከግንቦት 20 ድል በኋላ ተቆጥሮ የማያልቅ ብዙ ለውጥ አምጥተናል። በተለይም ኪራይ ሰብሳቢነትን በመታገል ረገድ ሙስና በማኅበረሰቡ ዘንድ ነውር ሆኖ እንዲታይ አድርገናል። ሁላችሁም እንደምታውቁት ድሮ ድሮ... "ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል"... እየተባለ በድፍረት ይነገር ነበር። ይህ ማለት ሲሾሙ መብላት ሲሻሩ ላላመቆጨት ወሳኝ መሆኑን ኅብረተሰቡ አምኖበት ነበር። አሁን ግን ይህ አባባል እየቀረና እየተረሳ ነው። ይህም የትግል ውጤት ነው።" ሰብሳቢው ይህንን በክብር እየተናገሩ እያለ ጋሽ ደፋሩ እጃቸው ላጥ! አድርገው አወጡ። … [Read more...] about “ሲሾም ያልበላ… ድሮ ቀረ” — [የግንቦት 20 ወግ]
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመሬት ነጠቃና ስደት (ክፍል ሁለት)
የዛሬ 26 ዓመት ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ብሎ የሰየመ የወንበዴዎችና የሽፍታዎች ስብስብ በምዕራባውያን አንጋሾቹ ታግዞ የምኒልክን ቤተመንግሥት ከተቆጣጠረ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ ሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቃላት እንደ እሣት እየተፉ ታሪክ ፈጽሞ ሊረሳው የማይችለውን ንግግር ያደረጉት ድንቅ ኢትዮጵያዊ ነበሩ – ኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ!! ስለ ኤርትራ መገንጠል እና ስለ ህወሃት የአስፈጻሚነት ተግባር የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ የትንቢት ያህል፤ ሳግ እየተናነቃቸው ይህንን ነበር የተናገሩት፤ “… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመሬት ነጠቃና ስደት (ክፍል ሁለት)
በግንቦት 20 ያተረፍኩትና የጎደለብኝ
ግንቦት 20 ከመደዴ ቀንነት ተመንጥቆ፣ ቅድስና ተቀብቶ መዘከር ከጀመረ ይኽው ሀያ ስድስት አመት ሆነ፡፡ በየካቲት 1983 አ.ም. ጎንደር በኢህአዴግ ሲያዝ፣ እኔና ጓደኞቼ እናስተምርበት ከነበረው ከጎርጎራ መንደር፣ በውጫሌ በኩል በኢህአዴግ ተሸኝተን፣ ደሴ ላይ አንድ ኩንታል ስንዴ ተመጽውተን አዲስ አበባ ገባን፡፡ ውጫሌ ላይ የሸኙን የኢህአዴግ ታጋዮች ቀድመውን አዲስ አበባ እንደሚገቡ ነግረውን ነበር፤ እንዳሉት ቀድመውን ባይገቡም፣ ብዙ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ ከኢህአዴግ የመጨረሻ ግዛት ከውጫሌ የደርግ ግዛት እስከነበረው የሀይቅ ከተማ የነበረውን የፈሪ ምድር ያቋረጥነው በእግር ነበር፡፡ ያንን ረባዳ ለምለም ስፍራ በእግር ስጓዝ አስበው የነበረው (አሁን ምኞት ብለው ይሻላል) ልብን የሚያሞቅ፣ ብርታት የሚሰጥ ነገር እስካሁን ከህሊናዬ አልጠፋም፡፡ " . . . . ከሁሉም በላይ የደርግ … [Read more...] about በግንቦት 20 ያተረፍኩትና የጎደለብኝ
የሚንተከተከው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢና አንድምታዎቹ!
ጋምቤላ እና ብዙ ዋጋ የተከፈለበት ኦጋዴን አደጋ ላይ ናቸው! ኦጋዴን ተገንጥሎ ወደ ሞቃዲሾ እንዲጠቃለል መለስ ዜናዊ ፈርሟል። የሰነዱ ግልባጭ እንግሊዞች እጅ አለ። ወያኔ በሶስት አቅጣጫ እንደ ቆዳ የተወጠረ ቡድን ነው ሲባል ፩ ለዘመናት ሲተዳደርበት የኖረው ኢህአዴግ በሚለው ማእቀፍ ውስጥ የነበረው የአሽከርና የሎሌ ግንኙነት ማብቃቱና በራሱ በህወሃት መካከል ያለው የሃይል ክፍፍል ያመጣው አጠቃላይ የስርአቱ አደጋ መሆኑ፣ ፪ ለረጅም ግዜ ሞቅ ቀዝቀዝ ሲል የነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ መልኩን ቀሮ ወደ ማይመለስ ህዝባዊ ተጋድሎ ማደጉና ከህዝባዊ ተጋድሎው ጀርባ ያሉት ነፍጥ ያነሱትን ድርጅቶች የመገዳደር ወይንም ችግሩን በፖለቲካዊ ውይይት ለመፍታት አቅም የማጣቱ ምክንያት ሲሆን ፫ኛው ክንፍ ደግሞ በምስራቅ አፍሪካ ላይ የተፈጠረው አለም አቀፍ የሃይል አሰላለፍ ላይ "በዚህ ሰፈር … [Read more...] about የሚንተከተከው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢና አንድምታዎቹ!
ኢትዮጵያዊ ነኝ!!
አርነት ! _ የጥቁር ምድር አርማ ፤ ልዕልና ! _ የጥቁር ክብር ማማ፤ የጥቁር ደም - የጥቁር ዘር፤ የጥቁር ብቃይ - ከጥቁር አፈር፤ አንደበት !_ የፍሰሃ ቃል፤ ፋና ወጊ !_ የጥቁር ቀንዲል፤ አብሳሪ !_ የጥቁርን ልዕልና - የጥቁርን ድል ፤ ምንጭ ! _ የሰው ልጅ ዘር ግኝት፤ ማህተም ! _ የጥቁር ሕዝብ ዕሴት፤ ማተብ ! _ የሰው ልጆች ዕምነት፤ የክርስቲያን፤ የእስላሙ፤ _ የይሁዲው ቤት፤ ኢትዮጵያዊ ነኝ ! _ ነፃነተ ዖሪት :: ቀሪውን የአሥራደው ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ … [Read more...] about ኢትዮጵያዊ ነኝ!!
በትዕቢት አይሆንም….
ባልና ሚስት ሆነን መስርተን ትዳር ልጆችም አፍርተን አንዳችም ሳይቀር ተመሥገን ፈጣሪ ምኞቴ ተሟላ አልቀይርም ሕይወት ይሄንን በሌላ ተሥፋ ለወደፊት ምሥጋና ሣሰማ ነገሩ ሌላ ነው ለካሥ ያንቺ ዓላማ የወለድናቸውን ልጆች በየተራ መንፈሥ እየቀየርሽ በተንኮል በሤራ እየመከርሻቸው የመለየት ሥራ ቤታችን ነገሠ ኩርፊያ አተካራ የገነባነውን ሐብትና ትዳር መጠበቅ ሲገባን በጋራ በምክር አንቺ ትብሽ እኔ በለን እንደአዋቂ ቀጣይ ትዳር ሆኖ ወደፊት ዘላቂ እንዲሠፍን ሰላም እንዲከተል ተድላ ሁሌም እንደመትጋት በጋራ በመላ አንቺ ግን ጥላቻ ልጆቹን አስተምረሽ በጎሪጥ ተመልካች ከሁሉም አናክሰሽ አጥሩ እንዲላላ ከውስጥ እንደመዥገር እየቦረቦርሽው እንዳይኖረው ማገር ይጠቅሰው የነበር ሁሉም በምሣሌ ቤታችን አመራ ወደ አልባሌ ለልጆቼ ባዳ ባይተዋር ላገሩ የሌለ … [Read more...] about በትዕቢት አይሆንም….
ሞተውም ይፈራሉ
ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከ1920ዎቹ ትውልዶች የቀለም ቀንድ፣ የአገርና የሃይማኖት ፍቅር፣ የአንድነትና የነፃነት ቀናዒ ከነበሩት አንዱ እንደሆኑ ይታወቃል። አሥራት ሞትን ታግለው፣ ድል እየነሱ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ሕይዎት ሲታደጉ የኖሩ፣ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሐኪም እንደነበሩ ሕያው ታሪካቸው ያስረዳል። በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በተገዙት ሽዕቢያና ወያኔ ትብብር፣ የአገራችን ዳር ድንበር ሲቆራረስ፣ ሰንደቅ ዓላማችን ሲራከስ፣ ቀይባሕር የባዕድ እንዲሆን ሲደረግ፣ ሕዝቡ በነገድ ተከፋፍሎ ዓይንና ናጫ እንዲሆን ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ሲሰጥ፣ አሥራት ይህ ሊሆን አይገባውም በማለት ከተሰበሰቡት የነገድ ድርጅቶች መካከል ድምፃቸውን ያሰሙት እርሳቸው ነበሩ። ቀጥሎም ዐማራን ለማጥፋት ዓላማው አድርጎ የተሰለፈው ወያኔና ጓደኞቹ በሐረርጌ፣ በአርሲ፣ በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ … [Read more...] about ሞተውም ይፈራሉ
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! (ክፍል 1)
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) የተባለ የወንበዴዎች ስብስብ በምዕራባውያን አንጋሾቹ ታግዞ የምኒልክን ቤተመንግሥት ከተቆጣጠረ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ ሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቃላት እንደ እሣት እየተፉ ታሪክ ፈጽሞ ሊረሳው የማይችለውን ንግግር ያደረጉት ድንቅ ኢትዮጵያዊ ነበሩ – ኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ!! ስለ ኤርትራ መገንጠል እና ስለ ህወሃት የአስፈጻሚነት ተግባር የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ የትንቢት ያህል፤ ሳግ እየተናነቃቸው ይህንን ነበር የተናገሩት፤ “… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! (ክፍል 1)