• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትዕቢት አይሆንም….

May 28, 2017 12:19 am by Editor Leave a Comment

ባልና ሚስት ሆነን መስርተን ትዳር
ልጆችም አፍርተን አንዳችም ሳይቀር
ተመሥገን ፈጣሪ ምኞቴ ተሟላ
አልቀይርም ሕይወት ይሄንን በሌላ
ተሥፋ ለወደፊት ምሥጋና ሣሰማ
ነገሩ ሌላ ነው ለካሥ ያንቺ ዓላማ
የወለድናቸውን ልጆች በየተራ
መንፈሥ እየቀየርሽ በተንኮል በሤራ
እየመከርሻቸው የመለየት ሥራ
ቤታችን ነገሠ ኩርፊያ አተካራ

የገነባነውን ሐብትና ትዳር
መጠበቅ ሲገባን በጋራ በምክር
አንቺ ትብሽ እኔ በለን እንደአዋቂ
ቀጣይ ትዳር ሆኖ ወደፊት ዘላቂ
እንዲሠፍን ሰላም እንዲከተል ተድላ
ሁሌም እንደመትጋት በጋራ በመላ

አንቺ ግን ጥላቻ ልጆቹን አስተምረሽ
በጎሪጥ ተመልካች  ከሁሉም አናክሰሽ
አጥሩ እንዲላላ ከውስጥ እንደመዥገር
እየቦረቦርሽው እንዳይኖረው ማገር
ይጠቅሰው የነበር ሁሉም በምሣሌ
ቤታችን አመራ ወደ አልባሌ

ለልጆቼ ባዳ ባይተዋር ላገሩ
የሌለ በዓለም በጎጥ በመንደሩ
እንድንሆን ከንቱ የሌላቸው ተስፋ
ለማድርግ አስበሽ  ትዳሩን የከፋ
ለካሥ ነበር ያንቺ ዓላማ ውጥኑ
እኔ መቼ ገባኝ ተንኮል የዘመኑ

ሃያ ስድስት ዓመት እስቲ ይሁን ብሎ
ቤተስቡ ሁሉ ያንቺን ዕብደት ችሎ
በጊዜ ይገባታል ሁሉንም ተረድታ
ትመለስ ይሆናል ጥጋቧንም ገታ
ብሎ ቢታገስሽ ፈጥሪውን ፈርቶ
አንቺ ግን አይገባሽ ካልሆነ ተዋግቶ
ሥትኖሪ በትዳር በወግ በማዕረግ
ተጠልፌ ነበር ትዳሬን ሣላደርግ
የሚል ጉድ አመጥሽ እንደ ሠበር ዜና
ከማስቆጨት አልፎ ትንሽ የሚዝናና

እረ አደብ ግዢ ታሪክ አትፈብርኪ
ምን ቢደረግ ይሆን ባለሽ የምትርኪ
እግዜር ይሰጥንን በጋራ ተካፍሎ
እንደመብላት ዕና መጓዝ ተቻችሎ
አንቺ ግን አመጣሽ ሁሉም ይሁን ለኔ
ጥጋብ ልብ ደፍኖ ይበደል ወገኔ

ሠላምና ፍቅር አንድነት ባይገባሽ
የጊዜ ጉዳይ ነው ልምከርሽ ከሰማሽ

አይሳካልሽም በተንኮል በሴራ
ቤት ማፍረስ በቀላል የቆመ በጋራ

ልጆቼ መስሏቸው በትቢት ቢመሩ
በማሥተዋል ታሪክ ባንድላይ ሲማሩ
ያጠፋሁት ካለ እኔም በበኩሌ
ላንቺ የማይጥምሽ ሥሕተት ካመሌ
ሲሆን ተነጋግረን ሽማግሌ ጠርቶ
በይቅርታ መንፈሥ ችግሩን አብላልቶ
ፍታዊ የሆነ ዳኝነት ተሰርቶ
ይሥተካከልና ሁሉም እንደቀድሞ
ቤታችን እንግባ ትዳሩም ታክሞ

ይሕንን ቁምነገር አንቺስ መች አጣሺው
አልፈታ ቢልሽ በቂም የቋጠርሺው

ጊዜው ያንቺ ቢሆን በተንኮል መበተን
መለያየት ፍጡር  ወገንነ ከወገን
እንዲሁም ይመጣል ጊዜ ለሰብሳቢ
በፈሪሃ እግዚአብሄር ሁሉንም ዓሳቢ

ይሄ እንደሚሆን ባልጠራጠርም
እስከዛ አደብ ግዢ በትቢት አይሆንም
መኖር አይቻልም ሁል ጊዜ በትቢት
ቀን እንዳጎልብሽ ወይዘሮ ደደቢት

ቦምቡ ፍቅርሽ 2017

(ጌትሽ ማሞ ባወጣው እንከባበር ዜማ ወትዋችነት የተገጠመ – ፎቶ አርአያ ጌታቸው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule