• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሞተውም ይፈራሉ

May 27, 2017 09:04 am by Editor Leave a Comment

ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከ1920ዎቹ ትውልዶች የቀለም ቀንድ፣ የአገርና የሃይማኖት ፍቅር፣ የአንድነትና የነፃነት ቀናዒ ከነበሩት አንዱ እንደሆኑ ይታወቃል። አሥራት ሞትን ታግለው፣ ድል እየነሱ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ሕይዎት ሲታደጉ የኖሩ፣ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሐኪም እንደነበሩ ሕያው ታሪካቸው ያስረዳል።

በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በተገዙት ሽዕቢያና ወያኔ ትብብር፣ የአገራችን ዳር ድንበር ሲቆራረስ፣ ሰንደቅ ዓላማችን ሲራከስ፣ ቀይባሕር የባዕድ እንዲሆን ሲደረግ፣ ሕዝቡ በነገድ ተከፋፍሎ ዓይንና ናጫ እንዲሆን ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ሲሰጥ፣ አሥራት ይህ ሊሆን አይገባውም በማለት ከተሰበሰቡት የነገድ ድርጅቶች መካከል ድምፃቸውን ያሰሙት እርሳቸው ነበሩ። ቀጥሎም ዐማራን ለማጥፋት ዓላማው አድርጎ የተሰለፈው ወያኔና ጓደኞቹ   በሐረርጌ፣ በአርሲ፣ በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ራያና ቆቦ ወዘተ ዐማራ በዘሩ ተመርጦ ሲታረድ፣ ሲሰቃይና ከነሕይዎቱ ገደል ሲጣል፣ ለዚህ ሕዝብ ድምፅ ለመሆን የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅትን (መዐሕድ) አቋቁመው የሕዝቡን በደል ለዓለም ማኅበረሰብ  ከማሰማት አልፈው፣ ዐማራው ተደራጅቶ ለኅልውናውና ለማንነቱ እንዲታገል ፋና ወጊ ሆነው የቆሙ  እንደነበሩ በክብር  ይታወሳሉ።

ይህ ጥረታቸው  ከዐማራው አልፎ የመላውን አገርና አንድነት ወዳድ ኢትዮጵያውያንን ኅሊና በመሳቡ ባጭር ጊዜ ውስጥ ሠፊ ዕውቅና ለማግኘት በመቻላቸው፣ ለወያኔ እንቅስቃሴ ከፍተኛ መሰናልክ ሆነው ታዩ። ይህም ወያኔን እንቅልፍ ስለነሳው፣ በሀሰት ከሶ፣ ከሳሽም፣ ዳኛም፣ መስካሪም ወያኔ ሆኖ፣ በእስር አሰቃይቶና ሕክምና ከልክሎ ለሕልፈተ ሕይዎት እንደዳረጋቸው ዓለም ያውቃል።

አሥራት በሕይዎት ኖረው ባያዩትም፣ የእርሳቸውን ፈለግ የተከተለው ትውልድ «ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!» በሚል ቋሚ መፈክር ዓርማቸውን  አንግቦ፣ የዐማራው ድምፅ ከአጥናፍ አጥናፍ መስተጋባት ብርክ የለቀቀበት  ወያኔ፣ አጽማቸው በሰላም እንዲያርፍ አልፈለገም። ሞተው ተቀብረውም የቆመውን ወያኔ አስፈሩት። ትናንት ሕይዎታቸውን ቀጠፈ። ዛሬ ደግሞ አጽማቸው ያረፈበትን የመቃብር ቦታ፣ ግፍ የማይፈሩት የትግሬ ልጆች  ማፍረሱን የወንድና የጀግና ተግባር አድርገውታል።

ኢትዮጵያውያን ስንባል ለአስከሬን ክቡር እንሰጣለን። ይህን ግን የዐማራ ጠላቶች ለሆኑት የትግራይ ትውልዶች ባዕድ በመሆኑ፣ ጠላትነታቸውን ሕይዎት በመቅጠፍ ብቻ ሳይሆን፣ አጽምንም በማድቀቅ እያሳዩን ነው። ይህ ለዐማራው ልጆች የማይረሳ የበደል በደል ነው። አሥራት የሚችሉትን ሠርተው መልካም የጽናት ምልክት ሆነው አልፈዋል። የእርሳቸውን ዓርማ አንስተን ፍቅር ለማይገባቸው ፍቅርን፣ ትዕግሥት ፍርሃት ለመሰላቸው ጀግንነትን፣ ማስተዋል አለማወቅ ለመሰላቸው፣ ማወቃችን ለማሳየት መዘጋጀት ለነገ የሚባል እንዳልሆነ ሊገባቸው በሚችለው ቋንቋ ልናናግራቸው ይገባል።

የአሥራትም ሆነ የሌሎች ኢትዮጵያውያን አጽም በክብር ካረፈበት ቦታ ሊጠበቅ ይገባዋል። አሁን በተያዘው መልኩ የአሥራትን አጽም  አውጥቶ ለመጣል  ከታሰበ መዘዙ ብዙ ሊሆን እንደሚችል ለትግሬ ትውልድ  ሊያውቅ ይገባል። ይህ አረመኔ አገዛዝ ያልፋል። የማያልፈው ትውልድ ነው። በመሆኑም መጭው የትግሬ ትውልድ በሰላም እንዲኖር ፍላጎት ያላችሁ ትግሬዎች ይህን ግፍ በዝምታ ልትመለከቱት አይገባም። ሲጀመር የአሥራት አስከሬን በክብር ማረፍ የነበረበት  ለኢትዮጵያ አርበኞች በተዘጋጀው በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ  ካቴድራል መካነ መቃብር ቦታ ነበር። ያን ሆን ተብሎና የእርሳቸውን ክብር ያዋረድን መስሎት መለስ ከለከለ። የባንዳው የአስረሱና የዜናዊ ልጅን ጊዜ ሆነና ፣አርበኛው ተገፍተው ዘረ ባንዳው መለስ ተቀበረበት። ይህ በራሱ የፈጠረው ቂም ሳይሽር ሌላ ቂም መግባት ለምን አስፈለገ? ይህ አረመኔያዊ ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ሕሊናን የሚዘገንን ስለሆነ፤ የትግሬ ትውልድ  ለመጭ ሕይዎቱ  ሲል አብሮን ሊጮህ ይገባል።

የዐማራው ልጆችና ድርጅቶች ይህን ጉድ፣ ከማውገዝ ባሻገር ፣ወያኔና አጋሮቹን ሊቆጠቁጥ የሚችል ተግባር ለመፈጸም  እንዘጋጅ!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

አንድ ዐማራ ለሁሉም ዐማራ ፤ ሁሉም ዐማራ ለአንድ ዐማራ!

ቅዳሜ ግንቦት ፲፱ ቀን ፪ሺህ ፱ ዓ.ም.                        

ቅፅ፭፣ ቁጥር  ፲፮


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

 

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule