• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሞተውም ይፈራሉ

May 27, 2017 09:04 am by Editor Leave a Comment

ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከ1920ዎቹ ትውልዶች የቀለም ቀንድ፣ የአገርና የሃይማኖት ፍቅር፣ የአንድነትና የነፃነት ቀናዒ ከነበሩት አንዱ እንደሆኑ ይታወቃል። አሥራት ሞትን ታግለው፣ ድል እየነሱ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ሕይዎት ሲታደጉ የኖሩ፣ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሐኪም እንደነበሩ ሕያው ታሪካቸው ያስረዳል።

በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በተገዙት ሽዕቢያና ወያኔ ትብብር፣ የአገራችን ዳር ድንበር ሲቆራረስ፣ ሰንደቅ ዓላማችን ሲራከስ፣ ቀይባሕር የባዕድ እንዲሆን ሲደረግ፣ ሕዝቡ በነገድ ተከፋፍሎ ዓይንና ናጫ እንዲሆን ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ሲሰጥ፣ አሥራት ይህ ሊሆን አይገባውም በማለት ከተሰበሰቡት የነገድ ድርጅቶች መካከል ድምፃቸውን ያሰሙት እርሳቸው ነበሩ። ቀጥሎም ዐማራን ለማጥፋት ዓላማው አድርጎ የተሰለፈው ወያኔና ጓደኞቹ   በሐረርጌ፣ በአርሲ፣ በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ራያና ቆቦ ወዘተ ዐማራ በዘሩ ተመርጦ ሲታረድ፣ ሲሰቃይና ከነሕይዎቱ ገደል ሲጣል፣ ለዚህ ሕዝብ ድምፅ ለመሆን የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅትን (መዐሕድ) አቋቁመው የሕዝቡን በደል ለዓለም ማኅበረሰብ  ከማሰማት አልፈው፣ ዐማራው ተደራጅቶ ለኅልውናውና ለማንነቱ እንዲታገል ፋና ወጊ ሆነው የቆሙ  እንደነበሩ በክብር  ይታወሳሉ።

ይህ ጥረታቸው  ከዐማራው አልፎ የመላውን አገርና አንድነት ወዳድ ኢትዮጵያውያንን ኅሊና በመሳቡ ባጭር ጊዜ ውስጥ ሠፊ ዕውቅና ለማግኘት በመቻላቸው፣ ለወያኔ እንቅስቃሴ ከፍተኛ መሰናልክ ሆነው ታዩ። ይህም ወያኔን እንቅልፍ ስለነሳው፣ በሀሰት ከሶ፣ ከሳሽም፣ ዳኛም፣ መስካሪም ወያኔ ሆኖ፣ በእስር አሰቃይቶና ሕክምና ከልክሎ ለሕልፈተ ሕይዎት እንደዳረጋቸው ዓለም ያውቃል።

አሥራት በሕይዎት ኖረው ባያዩትም፣ የእርሳቸውን ፈለግ የተከተለው ትውልድ «ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!» በሚል ቋሚ መፈክር ዓርማቸውን  አንግቦ፣ የዐማራው ድምፅ ከአጥናፍ አጥናፍ መስተጋባት ብርክ የለቀቀበት  ወያኔ፣ አጽማቸው በሰላም እንዲያርፍ አልፈለገም። ሞተው ተቀብረውም የቆመውን ወያኔ አስፈሩት። ትናንት ሕይዎታቸውን ቀጠፈ። ዛሬ ደግሞ አጽማቸው ያረፈበትን የመቃብር ቦታ፣ ግፍ የማይፈሩት የትግሬ ልጆች  ማፍረሱን የወንድና የጀግና ተግባር አድርገውታል።

ኢትዮጵያውያን ስንባል ለአስከሬን ክቡር እንሰጣለን። ይህን ግን የዐማራ ጠላቶች ለሆኑት የትግራይ ትውልዶች ባዕድ በመሆኑ፣ ጠላትነታቸውን ሕይዎት በመቅጠፍ ብቻ ሳይሆን፣ አጽምንም በማድቀቅ እያሳዩን ነው። ይህ ለዐማራው ልጆች የማይረሳ የበደል በደል ነው። አሥራት የሚችሉትን ሠርተው መልካም የጽናት ምልክት ሆነው አልፈዋል። የእርሳቸውን ዓርማ አንስተን ፍቅር ለማይገባቸው ፍቅርን፣ ትዕግሥት ፍርሃት ለመሰላቸው ጀግንነትን፣ ማስተዋል አለማወቅ ለመሰላቸው፣ ማወቃችን ለማሳየት መዘጋጀት ለነገ የሚባል እንዳልሆነ ሊገባቸው በሚችለው ቋንቋ ልናናግራቸው ይገባል።

የአሥራትም ሆነ የሌሎች ኢትዮጵያውያን አጽም በክብር ካረፈበት ቦታ ሊጠበቅ ይገባዋል። አሁን በተያዘው መልኩ የአሥራትን አጽም  አውጥቶ ለመጣል  ከታሰበ መዘዙ ብዙ ሊሆን እንደሚችል ለትግሬ ትውልድ  ሊያውቅ ይገባል። ይህ አረመኔ አገዛዝ ያልፋል። የማያልፈው ትውልድ ነው። በመሆኑም መጭው የትግሬ ትውልድ በሰላም እንዲኖር ፍላጎት ያላችሁ ትግሬዎች ይህን ግፍ በዝምታ ልትመለከቱት አይገባም። ሲጀመር የአሥራት አስከሬን በክብር ማረፍ የነበረበት  ለኢትዮጵያ አርበኞች በተዘጋጀው በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ  ካቴድራል መካነ መቃብር ቦታ ነበር። ያን ሆን ተብሎና የእርሳቸውን ክብር ያዋረድን መስሎት መለስ ከለከለ። የባንዳው የአስረሱና የዜናዊ ልጅን ጊዜ ሆነና ፣አርበኛው ተገፍተው ዘረ ባንዳው መለስ ተቀበረበት። ይህ በራሱ የፈጠረው ቂም ሳይሽር ሌላ ቂም መግባት ለምን አስፈለገ? ይህ አረመኔያዊ ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ሕሊናን የሚዘገንን ስለሆነ፤ የትግሬ ትውልድ  ለመጭ ሕይዎቱ  ሲል አብሮን ሊጮህ ይገባል።

የዐማራው ልጆችና ድርጅቶች ይህን ጉድ፣ ከማውገዝ ባሻገር ፣ወያኔና አጋሮቹን ሊቆጠቁጥ የሚችል ተግባር ለመፈጸም  እንዘጋጅ!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

አንድ ዐማራ ለሁሉም ዐማራ ፤ ሁሉም ዐማራ ለአንድ ዐማራ!

ቅዳሜ ግንቦት ፲፱ ቀን ፪ሺህ ፱ ዓ.ም.                        

ቅፅ፭፣ ቁጥር  ፲፮


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule