• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሞተውም ይፈራሉ

May 27, 2017 09:04 am by Editor Leave a Comment

ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከ1920ዎቹ ትውልዶች የቀለም ቀንድ፣ የአገርና የሃይማኖት ፍቅር፣ የአንድነትና የነፃነት ቀናዒ ከነበሩት አንዱ እንደሆኑ ይታወቃል። አሥራት ሞትን ታግለው፣ ድል እየነሱ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ሕይዎት ሲታደጉ የኖሩ፣ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሐኪም እንደነበሩ ሕያው ታሪካቸው ያስረዳል።

በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በተገዙት ሽዕቢያና ወያኔ ትብብር፣ የአገራችን ዳር ድንበር ሲቆራረስ፣ ሰንደቅ ዓላማችን ሲራከስ፣ ቀይባሕር የባዕድ እንዲሆን ሲደረግ፣ ሕዝቡ በነገድ ተከፋፍሎ ዓይንና ናጫ እንዲሆን ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ሲሰጥ፣ አሥራት ይህ ሊሆን አይገባውም በማለት ከተሰበሰቡት የነገድ ድርጅቶች መካከል ድምፃቸውን ያሰሙት እርሳቸው ነበሩ። ቀጥሎም ዐማራን ለማጥፋት ዓላማው አድርጎ የተሰለፈው ወያኔና ጓደኞቹ   በሐረርጌ፣ በአርሲ፣ በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ራያና ቆቦ ወዘተ ዐማራ በዘሩ ተመርጦ ሲታረድ፣ ሲሰቃይና ከነሕይዎቱ ገደል ሲጣል፣ ለዚህ ሕዝብ ድምፅ ለመሆን የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅትን (መዐሕድ) አቋቁመው የሕዝቡን በደል ለዓለም ማኅበረሰብ  ከማሰማት አልፈው፣ ዐማራው ተደራጅቶ ለኅልውናውና ለማንነቱ እንዲታገል ፋና ወጊ ሆነው የቆሙ  እንደነበሩ በክብር  ይታወሳሉ።

ይህ ጥረታቸው  ከዐማራው አልፎ የመላውን አገርና አንድነት ወዳድ ኢትዮጵያውያንን ኅሊና በመሳቡ ባጭር ጊዜ ውስጥ ሠፊ ዕውቅና ለማግኘት በመቻላቸው፣ ለወያኔ እንቅስቃሴ ከፍተኛ መሰናልክ ሆነው ታዩ። ይህም ወያኔን እንቅልፍ ስለነሳው፣ በሀሰት ከሶ፣ ከሳሽም፣ ዳኛም፣ መስካሪም ወያኔ ሆኖ፣ በእስር አሰቃይቶና ሕክምና ከልክሎ ለሕልፈተ ሕይዎት እንደዳረጋቸው ዓለም ያውቃል።

አሥራት በሕይዎት ኖረው ባያዩትም፣ የእርሳቸውን ፈለግ የተከተለው ትውልድ «ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!» በሚል ቋሚ መፈክር ዓርማቸውን  አንግቦ፣ የዐማራው ድምፅ ከአጥናፍ አጥናፍ መስተጋባት ብርክ የለቀቀበት  ወያኔ፣ አጽማቸው በሰላም እንዲያርፍ አልፈለገም። ሞተው ተቀብረውም የቆመውን ወያኔ አስፈሩት። ትናንት ሕይዎታቸውን ቀጠፈ። ዛሬ ደግሞ አጽማቸው ያረፈበትን የመቃብር ቦታ፣ ግፍ የማይፈሩት የትግሬ ልጆች  ማፍረሱን የወንድና የጀግና ተግባር አድርገውታል።

ኢትዮጵያውያን ስንባል ለአስከሬን ክቡር እንሰጣለን። ይህን ግን የዐማራ ጠላቶች ለሆኑት የትግራይ ትውልዶች ባዕድ በመሆኑ፣ ጠላትነታቸውን ሕይዎት በመቅጠፍ ብቻ ሳይሆን፣ አጽምንም በማድቀቅ እያሳዩን ነው። ይህ ለዐማራው ልጆች የማይረሳ የበደል በደል ነው። አሥራት የሚችሉትን ሠርተው መልካም የጽናት ምልክት ሆነው አልፈዋል። የእርሳቸውን ዓርማ አንስተን ፍቅር ለማይገባቸው ፍቅርን፣ ትዕግሥት ፍርሃት ለመሰላቸው ጀግንነትን፣ ማስተዋል አለማወቅ ለመሰላቸው፣ ማወቃችን ለማሳየት መዘጋጀት ለነገ የሚባል እንዳልሆነ ሊገባቸው በሚችለው ቋንቋ ልናናግራቸው ይገባል።

የአሥራትም ሆነ የሌሎች ኢትዮጵያውያን አጽም በክብር ካረፈበት ቦታ ሊጠበቅ ይገባዋል። አሁን በተያዘው መልኩ የአሥራትን አጽም  አውጥቶ ለመጣል  ከታሰበ መዘዙ ብዙ ሊሆን እንደሚችል ለትግሬ ትውልድ  ሊያውቅ ይገባል። ይህ አረመኔ አገዛዝ ያልፋል። የማያልፈው ትውልድ ነው። በመሆኑም መጭው የትግሬ ትውልድ በሰላም እንዲኖር ፍላጎት ያላችሁ ትግሬዎች ይህን ግፍ በዝምታ ልትመለከቱት አይገባም። ሲጀመር የአሥራት አስከሬን በክብር ማረፍ የነበረበት  ለኢትዮጵያ አርበኞች በተዘጋጀው በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ  ካቴድራል መካነ መቃብር ቦታ ነበር። ያን ሆን ተብሎና የእርሳቸውን ክብር ያዋረድን መስሎት መለስ ከለከለ። የባንዳው የአስረሱና የዜናዊ ልጅን ጊዜ ሆነና ፣አርበኛው ተገፍተው ዘረ ባንዳው መለስ ተቀበረበት። ይህ በራሱ የፈጠረው ቂም ሳይሽር ሌላ ቂም መግባት ለምን አስፈለገ? ይህ አረመኔያዊ ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ሕሊናን የሚዘገንን ስለሆነ፤ የትግሬ ትውልድ  ለመጭ ሕይዎቱ  ሲል አብሮን ሊጮህ ይገባል።

የዐማራው ልጆችና ድርጅቶች ይህን ጉድ፣ ከማውገዝ ባሻገር ፣ወያኔና አጋሮቹን ሊቆጠቁጥ የሚችል ተግባር ለመፈጸም  እንዘጋጅ!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

አንድ ዐማራ ለሁሉም ዐማራ ፤ ሁሉም ዐማራ ለአንድ ዐማራ!

ቅዳሜ ግንቦት ፲፱ ቀን ፪ሺህ ፱ ዓ.ም.                        

ቅፅ፭፣ ቁጥር  ፲፮


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule