• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በግንቦት 20 ያተረፍኩትና የጎደለብኝ

May 28, 2017 01:54 pm by Editor Leave a Comment

ግንቦት 20 ከመደዴ ቀንነት ተመንጥቆ፣ ቅድስና ተቀብቶ መዘከር ከጀመረ ይኽው ሀያ ስድስት አመት ሆነ፡፡ በየካቲት 1983 አ.ም. ጎንደር በኢህአዴግ ሲያዝ፣ እኔና ጓደኞቼ እናስተምርበት ከነበረው ከጎርጎራ መንደር፣ በውጫሌ በኩል በኢህአዴግ ተሸኝተን፣ ደሴ ላይ አንድ ኩንታል ስንዴ ተመጽውተን አዲስ አበባ ገባን፡፡

ውጫሌ ላይ የሸኙን የኢህአዴግ ታጋዮች ቀድመውን አዲስ አበባ እንደሚገቡ ነግረውን ነበር፤ እንዳሉት ቀድመውን ባይገቡም፣ ብዙ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ ከኢህአዴግ የመጨረሻ ግዛት ከውጫሌ የደርግ ግዛት እስከነበረው የሀይቅ ከተማ የነበረውን የፈሪ ምድር ያቋረጥነው በእግር ነበር፡፡

ያንን ረባዳ ለምለም ስፍራ በእግር ስጓዝ አስበው የነበረው (አሁን ምኞት ብለው ይሻላል) ልብን የሚያሞቅ፣ ብርታት የሚሰጥ ነገር እስካሁን ከህሊናዬ አልጠፋም፡፡ ” . . . . ከሁሉም በላይ የደርግ መንግስት ወድቆ፣ ሀገሪቱ ከነበረችበት ማጥ ስትወጣ ይታየኝ ነበር፤ የኢህአዴግ ታጋዮች እየከፈሉት ያለው መስዋእትነት ልቤን ያሞቀው ነበር፤ ድሆች በቀን ሶስት ጊዜ በልተው ሲያድሩ ይታየኝ ነበር፤ የግል ፕሬስ ሲያብብ. . .ሲያፈራ፣ ሰዎች ያለፍርሀት ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ ይታየኝ ነበር፣ ዜጎች በመረጡት መንግስት ሲተዳደሩ ይታየኝ ነበር፡፡ . . . “

ይህ ሁሉ በደርግ የአገዛዝ ዘመን አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በደርግ የአገዛዝ ዘመን ድንበርዋ የታፈረና የተከበረ እትዮጵያ ነበረች፤ ይህች ኢትዮጵያ ጠንካራ የፍትህ ስርአት ነበራት፤ ደርግ ወጣቱን ወደ እስር ቤት ያጋዘውና በየመንገዱ የረሸነው በመደበኛ ፍርድ ቤት ፍትህን መሳሪያው አድርጎ አይደለም – የራሱን የጦር ፍርድ ቤት መስርቶ ነው፡፡

ዛሬ ከ26 አመት በኋላ የደርግ አንባገነናዊ መንግስት የለም፡፡ በኢህአዴግ ያገኘሁት ብቸኛ በረከት እሱ ነው – የደርግ መገርሰስ፡፡ እነዚያ ሁሉ . . ከውጫሌ እስከ ሀይቅ በእግር ስጓዝ አስባቸው የነበሩት፣ በተስፋ አሙቀው ለመንገዴ ብርታት የነበሩት ሀሳቦቼ ሁሉ ሀሳብ ሆነው ቀርተዋል፡፡ ብዙዎች “ልማትን ከኢህአዴግ አግኝተሀል” ይሉኛል፡፡

እኔ ግን፣ “አንድ መንግስት መንገድ መስራትና ባቡር መዘርጋት፣ ውሀና መብራት ማስገባት ስራው – ግዴታው ነው፣ ያለዚያ ስለምን ይነግሳል? አባት ልጁን ማልበስና መመገብ ግዴታው ነው እንጂ እንደ ውለታ ተቆጥሮ ያስመሰግነዋልን?” እላቸዋለሁ፡፡

ይሁን እንጂ ድሆች በቀን ሶስቴ በልተው ሲያድሩ አላየሁም፤ ህዝቦች ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ አላየሁም፣ ዲሞክራሲ ሰፍኖ አላየሁም፡፡ እነዚህ ግን በደርግም ዘመን አልነበሩምና ኢህአዴግ አልነጠቀኝም፤ ኢህአዴግ ያጎደለብኝ በደርግ ጊዜ የነበሩትን ድንበሯ የተከበረ ኢትዮጵያና ፍትህ የማይዛባበት ፍርድ ቤት ነው፡፡

(በድሉ ዋቅጅራ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule