• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በግንቦት 20 ያተረፍኩትና የጎደለብኝ

May 28, 2017 01:54 pm by Editor Leave a Comment

ግንቦት 20 ከመደዴ ቀንነት ተመንጥቆ፣ ቅድስና ተቀብቶ መዘከር ከጀመረ ይኽው ሀያ ስድስት አመት ሆነ፡፡ በየካቲት 1983 አ.ም. ጎንደር በኢህአዴግ ሲያዝ፣ እኔና ጓደኞቼ እናስተምርበት ከነበረው ከጎርጎራ መንደር፣ በውጫሌ በኩል በኢህአዴግ ተሸኝተን፣ ደሴ ላይ አንድ ኩንታል ስንዴ ተመጽውተን አዲስ አበባ ገባን፡፡

ውጫሌ ላይ የሸኙን የኢህአዴግ ታጋዮች ቀድመውን አዲስ አበባ እንደሚገቡ ነግረውን ነበር፤ እንዳሉት ቀድመውን ባይገቡም፣ ብዙ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ ከኢህአዴግ የመጨረሻ ግዛት ከውጫሌ የደርግ ግዛት እስከነበረው የሀይቅ ከተማ የነበረውን የፈሪ ምድር ያቋረጥነው በእግር ነበር፡፡

ያንን ረባዳ ለምለም ስፍራ በእግር ስጓዝ አስበው የነበረው (አሁን ምኞት ብለው ይሻላል) ልብን የሚያሞቅ፣ ብርታት የሚሰጥ ነገር እስካሁን ከህሊናዬ አልጠፋም፡፡ ” . . . . ከሁሉም በላይ የደርግ መንግስት ወድቆ፣ ሀገሪቱ ከነበረችበት ማጥ ስትወጣ ይታየኝ ነበር፤ የኢህአዴግ ታጋዮች እየከፈሉት ያለው መስዋእትነት ልቤን ያሞቀው ነበር፤ ድሆች በቀን ሶስት ጊዜ በልተው ሲያድሩ ይታየኝ ነበር፤ የግል ፕሬስ ሲያብብ. . .ሲያፈራ፣ ሰዎች ያለፍርሀት ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ ይታየኝ ነበር፣ ዜጎች በመረጡት መንግስት ሲተዳደሩ ይታየኝ ነበር፡፡ . . . “

ይህ ሁሉ በደርግ የአገዛዝ ዘመን አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በደርግ የአገዛዝ ዘመን ድንበርዋ የታፈረና የተከበረ እትዮጵያ ነበረች፤ ይህች ኢትዮጵያ ጠንካራ የፍትህ ስርአት ነበራት፤ ደርግ ወጣቱን ወደ እስር ቤት ያጋዘውና በየመንገዱ የረሸነው በመደበኛ ፍርድ ቤት ፍትህን መሳሪያው አድርጎ አይደለም – የራሱን የጦር ፍርድ ቤት መስርቶ ነው፡፡

ዛሬ ከ26 አመት በኋላ የደርግ አንባገነናዊ መንግስት የለም፡፡ በኢህአዴግ ያገኘሁት ብቸኛ በረከት እሱ ነው – የደርግ መገርሰስ፡፡ እነዚያ ሁሉ . . ከውጫሌ እስከ ሀይቅ በእግር ስጓዝ አስባቸው የነበሩት፣ በተስፋ አሙቀው ለመንገዴ ብርታት የነበሩት ሀሳቦቼ ሁሉ ሀሳብ ሆነው ቀርተዋል፡፡ ብዙዎች “ልማትን ከኢህአዴግ አግኝተሀል” ይሉኛል፡፡

እኔ ግን፣ “አንድ መንግስት መንገድ መስራትና ባቡር መዘርጋት፣ ውሀና መብራት ማስገባት ስራው – ግዴታው ነው፣ ያለዚያ ስለምን ይነግሳል? አባት ልጁን ማልበስና መመገብ ግዴታው ነው እንጂ እንደ ውለታ ተቆጥሮ ያስመሰግነዋልን?” እላቸዋለሁ፡፡

ይሁን እንጂ ድሆች በቀን ሶስቴ በልተው ሲያድሩ አላየሁም፤ ህዝቦች ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ አላየሁም፣ ዲሞክራሲ ሰፍኖ አላየሁም፡፡ እነዚህ ግን በደርግም ዘመን አልነበሩምና ኢህአዴግ አልነጠቀኝም፤ ኢህአዴግ ያጎደለብኝ በደርግ ጊዜ የነበሩትን ድንበሯ የተከበረ ኢትዮጵያና ፍትህ የማይዛባበት ፍርድ ቤት ነው፡፡

(በድሉ ዋቅጅራ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule