• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በግንቦት 20 ያተረፍኩትና የጎደለብኝ

May 28, 2017 01:54 pm by Editor Leave a Comment

ግንቦት 20 ከመደዴ ቀንነት ተመንጥቆ፣ ቅድስና ተቀብቶ መዘከር ከጀመረ ይኽው ሀያ ስድስት አመት ሆነ፡፡ በየካቲት 1983 አ.ም. ጎንደር በኢህአዴግ ሲያዝ፣ እኔና ጓደኞቼ እናስተምርበት ከነበረው ከጎርጎራ መንደር፣ በውጫሌ በኩል በኢህአዴግ ተሸኝተን፣ ደሴ ላይ አንድ ኩንታል ስንዴ ተመጽውተን አዲስ አበባ ገባን፡፡

ውጫሌ ላይ የሸኙን የኢህአዴግ ታጋዮች ቀድመውን አዲስ አበባ እንደሚገቡ ነግረውን ነበር፤ እንዳሉት ቀድመውን ባይገቡም፣ ብዙ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ ከኢህአዴግ የመጨረሻ ግዛት ከውጫሌ የደርግ ግዛት እስከነበረው የሀይቅ ከተማ የነበረውን የፈሪ ምድር ያቋረጥነው በእግር ነበር፡፡

ያንን ረባዳ ለምለም ስፍራ በእግር ስጓዝ አስበው የነበረው (አሁን ምኞት ብለው ይሻላል) ልብን የሚያሞቅ፣ ብርታት የሚሰጥ ነገር እስካሁን ከህሊናዬ አልጠፋም፡፡ ” . . . . ከሁሉም በላይ የደርግ መንግስት ወድቆ፣ ሀገሪቱ ከነበረችበት ማጥ ስትወጣ ይታየኝ ነበር፤ የኢህአዴግ ታጋዮች እየከፈሉት ያለው መስዋእትነት ልቤን ያሞቀው ነበር፤ ድሆች በቀን ሶስት ጊዜ በልተው ሲያድሩ ይታየኝ ነበር፤ የግል ፕሬስ ሲያብብ. . .ሲያፈራ፣ ሰዎች ያለፍርሀት ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ ይታየኝ ነበር፣ ዜጎች በመረጡት መንግስት ሲተዳደሩ ይታየኝ ነበር፡፡ . . . “

ይህ ሁሉ በደርግ የአገዛዝ ዘመን አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በደርግ የአገዛዝ ዘመን ድንበርዋ የታፈረና የተከበረ እትዮጵያ ነበረች፤ ይህች ኢትዮጵያ ጠንካራ የፍትህ ስርአት ነበራት፤ ደርግ ወጣቱን ወደ እስር ቤት ያጋዘውና በየመንገዱ የረሸነው በመደበኛ ፍርድ ቤት ፍትህን መሳሪያው አድርጎ አይደለም – የራሱን የጦር ፍርድ ቤት መስርቶ ነው፡፡

ዛሬ ከ26 አመት በኋላ የደርግ አንባገነናዊ መንግስት የለም፡፡ በኢህአዴግ ያገኘሁት ብቸኛ በረከት እሱ ነው – የደርግ መገርሰስ፡፡ እነዚያ ሁሉ . . ከውጫሌ እስከ ሀይቅ በእግር ስጓዝ አስባቸው የነበሩት፣ በተስፋ አሙቀው ለመንገዴ ብርታት የነበሩት ሀሳቦቼ ሁሉ ሀሳብ ሆነው ቀርተዋል፡፡ ብዙዎች “ልማትን ከኢህአዴግ አግኝተሀል” ይሉኛል፡፡

እኔ ግን፣ “አንድ መንግስት መንገድ መስራትና ባቡር መዘርጋት፣ ውሀና መብራት ማስገባት ስራው – ግዴታው ነው፣ ያለዚያ ስለምን ይነግሳል? አባት ልጁን ማልበስና መመገብ ግዴታው ነው እንጂ እንደ ውለታ ተቆጥሮ ያስመሰግነዋልን?” እላቸዋለሁ፡፡

ይሁን እንጂ ድሆች በቀን ሶስቴ በልተው ሲያድሩ አላየሁም፤ ህዝቦች ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ አላየሁም፣ ዲሞክራሲ ሰፍኖ አላየሁም፡፡ እነዚህ ግን በደርግም ዘመን አልነበሩምና ኢህአዴግ አልነጠቀኝም፤ ኢህአዴግ ያጎደለብኝ በደርግ ጊዜ የነበሩትን ድንበሯ የተከበረ ኢትዮጵያና ፍትህ የማይዛባበት ፍርድ ቤት ነው፡፡

(በድሉ ዋቅጅራ)

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule