የሚማር የለም እንጂ የሚማር ቢኖር የሽብርተኛነትን ትርጉም ሰሞኑን በቤልጂክ እያየንና እየሰማን ነው፤ በኢትዮጵያ ያሉ የእውቀት ምልክቶችን በዶላር እየገዙ ስማቸው ላይ የለጠፉ ጉልበተኞች ተናገርክ(ሽ) ብለው ብቻ ሳይሆን አሰብህ(ሽ) ብለው ሰፋፊ እስር ቤቶች እያሰሩ ወጣቶችን ሲያጉሩበት ምክንያታቸው ሽብርተኛነት ነው፤ ሽብር ማለት ሰሞኑን በቤልጂክ አውሮጵላን ጣቢያና በባቡር ጣቢያ ላይ እንደታየው ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ አልታየም፤ ከታየም በአገዛዙ ኃይሎች የተፈጸመ ነው፤ ለብዙ ዓመታት ሲፈጸም የቆየ ነው፤ የኢትዮጵያ ጉልበተኞች ከቻሉ ሊያስተውሉት የሚገባ አንድ ነገር አለ፡- ሽብርም ነጻነትን ይፈልጋል፤ በቤልጂክ ሽብሩን የፈጸሙት ሁሉ ነጻነትን ፈልገው ከአገራቸው የተሰደዱና በአገራቸው ያላገኙትን ነጻነት በሰው አገር እየተሞላቀቁበት እንደሆነ የሚያመለክት ነው፤ ትርጉሙ፡- ነጻነት በሌለበት … [Read more...] about የሽብርተኛ ትርጉም
Archives for March 2016
የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች
የኢህአዴግ የቁርጥ ቀን ልጅ ልደቱ አያሌውና ፓርቲው ኢዴፓ ባዲስ ትርፍ የፓርላማ መቀመጫ ፍለጋ ሰሞኑን ከእንቅልፋቸው መንቃታቸውን ሰምቼ ትንሽ ተገረምኩ። በውል ያልተደነቅሁበት ምክንያት ኢዴፓንና ሌሎች በኢህአዴግ-ወለድ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ም/ቤት ውስጥ የታጨቁ የስልጣን ተስፈኞች እንጂ ፖለቲካ የሚያውቁ ቁርጠኛ ተቃዋሚዎች ናቸው ብዬ ስለማላውቅ ነው። ደግነቱ ደግሞ ነገሩ እውነት መሆኑ ነው። እነዚህ ኢህአዴግ በልካቸው በሰራላቸው ጉረኖ ታሽገው በኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ስልጣን ለመቀላወጥ በተስፋ የሚያደቡት ኢዴፓና አጃቢዎቹ ሰሞኑን የኢህአዴግ ዙፋን ሲነቃነቅ በፈጠረው የፖለቲካ ስንጥቅ ለመሰካት በጠቅላይ ሚንስትሩ እግር ስር ወድቀው ትራፊ ወንበር እንዲረጥቧቸው ልመና መጀመራቸውን ሰምቼ አፈርኩባቸው። የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደ አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም ለአሜሪካ … [Read more...] about የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች
“የልጄን ነገር አደራ…” እናት ሎሚ
የእናትን መሪር ሐዘን ሰምቸ ሆዴ ተላውሷል፣ የእናትን ጥልቅ ጭንቀቷ፣ ያለ አባት በአሳር በመከራ ያሳደገቻት የእናትን ሎሜ መሪር ሐዘን ተረድቸ ህመም መታመሜ እውነት ሳለ በዝምታ እየቆሰልኩ ማስረጃ መረጃ ፍለጋ መዋተቴ ህመሜን አክብዶታል፡፡ ከጉያዋ ወሽቃ፣ በትንፋሿ አሙቃ፣ ስታገኝ በደስታ፣ ስታጣ ተከፍታ ድሃ አደግ ቤቷን አሟሙቃ ነገን ልጆቿን ለወግ ለማዕረግ የማድረስ ምኞት ተስፋን ሰንቃ ተስፋዋን የተነጠቀች እናት እንባ ውስጤን አድምቶ አቃጥሎታል። እናት ዛሬ ማለዳ በላኩልኝ መልዕክት እንዲህ ይላል “የልጀን ነገር አደራ እባክህ ነፍሴን አሳርፋት" … ሰው ሆዬ ሲጨንቀው እኔ መረጃን ከምንጩ ከማሰራጨት ባለፈ ሁሉን ማድረግ የሚቻለኝ አድርጎ ይስለኛል፤ እኔ ግን አቅሙ የለኝም! መረጃዎችን ለወገናቸው ጥቅም ቅድሚያ ከሚሰጡ የመንግስትና የድርጅት አባላት በሚስጥር፤ ከቀሩት ወገኖች … [Read more...] about “የልጄን ነገር አደራ…” እናት ሎሚ
ህወሃት ራሱን በራሱ ሸንጎ አስገምግሞ የእጁን ደም ሊያጸዳ ነው
ህወሃት በኦሮሚያና በአማራ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸመውን ወንጀልና ርህራሄ አልባ ግፍ ራሱ አጣርቶ፣ ራሱ አጠናክሮ፣ ራሱ በፈጠረው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አማካይነት አቅርቦ፣ በራሱ ሸንጎ በማጸደቅ እጁን ከደም ሊያጸዳ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ይፋ መሆኑንን ተከትሎ ለሪፖርቱ ማዳመቂያ የምስል ቪዲዮዎች መዘጋጀታቸው ታወቀ። በኦሮሞና በአማራ ህዝብ ላይ የተወሰደውንና እየተወሰደ ያለውን የኃይል ርምጃ አስመልከቶ ድራማ እየተሰራ ነው ሲል የጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ሪፖርተር የኢህአዴግ ጽ/ቤት ምንጮቹን ጠቅሶ ነው ስለ ሁኔታው የዘገበው። ህወሃት በአዋጅ ያቋቋመው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መሪ ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር ቀደም ሲል በጉዳዩ ዙሪያ ሪፖርት ያቀረቡትን የመብት ተሟጋች ድርጅቶች እንደማይታመኑ ተናግረዋል። በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር መመሪያ ሰጪነት ህወሃት … [Read more...] about ህወሃት ራሱን በራሱ ሸንጎ አስገምግሞ የእጁን ደም ሊያጸዳ ነው
ለአዲስ አበባ የውሃ ድርቅ “ፈረቃ” መፍትሔ ሆኖ ተበሰረ
ራሱን “ልማታዊ” እያለ የሚጠራው ኢህአዴግ በውሃ ድርቅ ሳቢያ በአዲስ አበባ በዝርዝር ባልተገለጹ ቦታዎች ውሃ በፈረቃ ማቅረብ መፍትሔ ሆኖ ተበሰረ። በአገሪቱ በይፋ ያልተገለጸ የውሃ ችግር አለ። አዲስ አበባን በተመለከተ የከርሰ ምድር ውሃ ችግር እንደሌለ ባለሙያዎች ሃሳብ ሲሰጡ ኖረዋል። ኢህአዴግም ቢሆን ከ1997 ምርጫ በኋላ የአዲስ አበባን የውሃ ችግር ለመፍታት የከርሰ ምድር ውሃን እንደሚያጎለብት በተደጋጋሚ ሲገልጽ ነበር። የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የህዝብ ግንኙነትን ጠቅሶ ቪኦኤ እንደዘገበው የፈረቃው አሠራር የተጀመረው የካቲት 24 ነው። ፈረቃው መፍትሔ ሆኖ የቀረበው የድሬና የለገዳዲ ግድቦች በቂ ውሃ ባለመያዛቸው ሲሆን ፈረቃውም የሚያካትታቸውን ቦታዎች “የተወሰኑ” ከማለት ሌላ ዝርዝር አልቀረበም። በከፊል አዲስ አበባ ተብሎ በደምሳሳው ውሃ በፈረቃ እንደሚታደል ሲገለጽ … [Read more...] about ለአዲስ አበባ የውሃ ድርቅ “ፈረቃ” መፍትሔ ሆኖ ተበሰረ
በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች
ገዢው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት በየዕለቱ በሚያደርገው ፀረ-ኢትዮጵያዊ ተግባር፤ የተለያዩ የፖለቲካ ሕዝባዊ ስብስቦች መግለጫ ያወጣሉ። አዳዲስና ነባር የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አለን በማለት ስማቸውን በአንባቢዎች ያስመዘግባሉ። ለመሆኑ ጋዜጣዊ መገለጫዎች ለምንድን ጉዳይ ነው የሚወጡት? ማነው የሚያወጣቸው? መግለጫዎችን ተከትሎ የሚተገበሩት ምንድን ናቸው? አሉስ ወይ? መግለጫ አውጪዎቹና መግለጫ ያላወጡ የፖለቲካ ሕዝባዊ አካሎች መለያቸው ምንድን ነው? መግለጫዎችና አውጪዎቻቸው፤ ሕዝባዊ ናቸው ወይንስ ጠባብ ወገንተኛ? መልዕክት አላቸው ወይንስ አደረግሁ ለማለት የተወረወሩ? አስፈላጊነታቸውስ ምን ያህል ነው? በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ በተንጎደጎዱ ወቅት የደረሱኝ እጦማሮች ነበሩ። ሁሉም ወቀሳዎች ናቸው። “ለምን መግለጫ አታወጣም?” “ካሁን በፊትም ዝም ብለሃል!” የሚሉና … [Read more...] about በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች
ኃይለማርያም ቋፍ ላይ የደረሱ ይመስላሉ!
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን የሚሰጡት አስተያየትና ንግግር ህወሃት/ኢህአዴግ ያፈጠጠበትን ችግር ብቻ ሳይሆን እርሳቸውም በቋፍ ላይ የደረሱ መሆናቸውን ያመላከተ እየሆነ ሄዷል፡፡ ወደ ሥልጣን ሲመጡ በሙስና ላይ ዘመቻ እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ይናገሩ የነበሩት ኃይለማርያም እስካሁን የሚታይ ለውጥ ሳያመጡ ቀርተዋል፡፡ በቅርቡ ከምሁራን ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይም “የተለያየ አመለካከትን የማይቀበል ሥርዓት የጊዜ ጉዳይ እንጂ መውደቁ አይቀርም” ማለታቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ችግሩን በቀጥታ ከኢህአዴግ ጋር እያያዙ በግልጽ መናገራቸው በሕይወታቸው ላይ አደጋ እስከሚያመጣ የደረሰ መሆኑ ለጎልጉል የደረሱ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም የግል ጠባቂዎቻቸውና አጃቢዎቻቸው ላይ የተደረጉ ለውጦችን ከዚህም ጋር የሚያያይዙ ወገኖች ኃይለማርያም በእርግጥም በችግር ውስጥ እንዳሉ ጠቋሚ መሆናቸውን … [Read more...] about ኃይለማርያም ቋፍ ላይ የደረሱ ይመስላሉ!
የአዲስ አበባውና የአሜሪካው ኢህአዴግ ቢሮ አይተዋወቁም
በሳምንቱ አጋማሽ የተሰማውን ዜና ያደመጡ፣ ከቅርብ ሆነው የሚከታተሉና ለጉዳዩ የቀረቡ እንደሚሉት የአዲስ አበባው ኢህአዴግና አሜሪካ ያለው የኢህአዴግ ቢሮ የማይተዋወቁበት ደረጃ ደርሰዋል። ኢህአዴግ በደብዳቤ የተረከባቸውን ስደተኞች በብሔር መትሮ “ኢትዮጵያዊ አይደላችሁም” በሚል ወደ አሜሪካ መመለሱ የእለት ጉርስና የዘመን መሻገሪያ ድርጎ የምትመድበውን አሜሪካንን አስቆጥቶ እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል። ኢህአዴግ እንደ “አሸባሪ” የፊጥኝ አስሮ ከፍሎሪዳ ጠቅላይ ግዛት ማያሚ እስር ቤት ወደ ኢትዮጵያ የወሰዳቸው ወገኖች ከአገራቸው የወጡበትን ጊዜ ሳይቆጥር አሜሪካ ለመድረስ ብቻ እስከ አስራ አራት ወራት ፈጅቶባቸዋል። ስደተኞቹ በብራዚል፣ በኮሎምቢያ ጫካ ፣ በፓናማ ወንዝ አሳብረው፣ በሜክሲኮና በድምሩ 16 የሚደርሱ አገራትን አልፈው ነበር አሜሪካ ጥገኝነት የጠየቁት። እነዚህ ወገኖች ህጉ … [Read more...] about የአዲስ አበባውና የአሜሪካው ኢህአዴግ ቢሮ አይተዋወቁም
የዕርቅ ሃሳብ ከውስጥም ከውጭም ትኩረት ስቧል
አሁን ኢትዮጵያ ለደረሰችበት አሳሳቢ ደረጃ ዋናውና ብቸኛው መፍትሔ ሰላማዊ ዕርቅ መሆኑ በአገር ውስጥና በውጪ ልዩ ትኩረት እየሳበ መሆኑ ተሰማ። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ኢህአዴግ በራሱ ችግር በየጊዜው ከሕዝብ ጋር ቅራኔ ውስጥ መግባቱን፣ ይህንን ቅራኔ መፍታት ካልቻል መንገዱ የውድቀት እንደሚሆን አስጠነቀቁ። ሕዝብ በአፉና በእጁ እየገፋን ነው አሉ። ለጎልጉል የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በቅርቡ የተጀመረውን “የኢትዮጵያ የዕርቅና ርትዓዊ ፍትሕ ምክርቤት” ተከትሎ የዕርቅ ሃሳብ አሁን ኢትዮጵያ ላለችበት ሁኔታ አማራጭ የሌለው እንደሆነ እየተጠቆመ ነው፡፡ በተለይ በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ጉዳይ ተከታታዮችና ፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ ጉዳዩ ድጋፋቸውን የሚሰጡበት እንደሆነ መረጃው አመልክቷል፡፡ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የተመሠረተው ምክርቤት ድጋፍ እንደሚያስፈልገው በመጠቆም ስለምክር ቤቱ … [Read more...] about የዕርቅ ሃሳብ ከውስጥም ከውጭም ትኩረት ስቧል
Leadership Gap: The main reason why we keep failing to topple dictatorship
In the last couple of decades, people around the world fought and toppled dictators. Courageous Africans removed dictators from Benin, Zambia, and Ghana in the 90’s and early 2000. The Arab Spring that took place in the northern African countries such as in Tunisia, Egypt, and Libya ousted despots.Likewise, successful revolutions in Asia like the one in Philippines (Yellow Revolution)that took place in 1986 overthrew President Ferdinand Marcos. In the beginning of the new century, Rose, Orange, … [Read more...] about Leadership Gap: The main reason why we keep failing to topple dictatorship