ባለፉት ፳፭(ሃያ አምሥት) ዓመታት በዐማራው ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ከችግሩ ሥፋት እናጥልቀት አንፃር ተመጣጣኝ የሆነ የሚዲያ ሽፋን አልተሰጠውም። በ«ኢትዮጵያዊነት» ስም በተቋቋሙት ድርጅቶችም ሆነ በተለያዩ አገሮች መንግሥታት ሥር የሬድዮ እና የቴሌቪዥን መርኃ-ግብሮችን በአማርኛ ቋንቋ የሚያሠራጩ ሚዲያዎች በዐማራው ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እና በደል የዓለም ማኅበረሰብ እንዲያውቀው የማድረግ ፈቃደኝነታቸው እጅግ ውስን መሆኑን በተደጋጋሚ ታይቷል። ይህም «ችግሩ ችግራችን ነው» ብሎ የሚይዝ ሚዲያ አለመኖሩን ያረጋግጣል። ስለሆነም እኛ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት አባሎች እና ደጋፊዎችለመላው የዐማራ ሕዝብ ድምጽ የሚሆን የሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም ቆርጠን ተነስተናል። ዐማራው በተገንጣይ እና ጠባብ የጎጠኞች ቡድኖች የተክፈተበትን የሥነ-ልቦና ጦርነት ተመጣጣኝ በሆነ … [Read more...] about ሞረሽ የዐማራ ድምፅ የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋም ለምን አስፈለገ?
Archives for March 2016
ሀላፊነት እወስዳለሁ ማለትና ይቅርታ በተግባር መተርጎም አለበት
ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማርአም ደሳለኝ ከጥቂት ቀናት በፊት ለፓርላማው ባቀረቡት ዘገባ ውስጥ ጨምረው በሀገራችን ባሁኑ ሰአት በተለይም በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ጎልቶ የሚታየውን የህብዝን መነሳሳት ከመልካም አስተዳደር መጥፋትና ከስርአቱ ብልሽት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ለተፈጸመው በደል ተጠያቂ እንደሆኑም አምነው "ይቅርታ" ጠይቀዋል። (የመግለጫው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል)። … [Read more...] about ሀላፊነት እወስዳለሁ ማለትና ይቅርታ በተግባር መተርጎም አለበት
ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ ለኢትዮጵያውያን የቢሊዮኖች ዶላር ካሣ ይጠይቃል
ጋ ዜ ጣ ዊ መ ግ ለ ጫ መጋቢት 7 ቀን 2008 ዓ/ም Garland, Texas: (ጋርላንድ፤ ቴክሳስ)፡ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ - የኢትዮጵያ ጉዳይ፤ መንግሥታዊ ያልሆነ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢኮኖሚና የማሕበራዊ ጉዳዮች አካል ውስጥ የተመዘገበ ተቋም ነው። በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ እየተከናወነ በሚገኘው የኢጣልያ ፕሬዚዳንትና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉብኝት አጋጣሚ ጊዜ የድርጅታችን ዓላማ የኢጣልያ መንግሥት እ.አ.አ. በ1928-33 ዓ/ም በኢትዮጵያ ላይ ለፈጸመው የጦር ወንጀልና የሰው እልቂት ተገቢው ፍትሕ እንዲገኝና ከኢትዮጵያ የተዘረፈውን ኢጣልያ፤ የቫቲካን ቤተ መጻሕፍትና ሌሎችም እንዲመልሱና እንዲክሱ ለማድረግ ነው። በ1928-33 ዓ/ም ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ በፈጸመችው ጦርነት፤ ፋሺሽቶች በአውሮፕላኖች አማካኝነት በነስነሱት የመርዝ ጋዝ ጭምር የብዙ ሰው … [Read more...] about ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ ለኢትዮጵያውያን የቢሊዮኖች ዶላር ካሣ ይጠይቃል
በርሀብ የሚገድል መንግሥት እንዴት በሥልጣን ላይ ይቆይ?
ታላላቅ ረሀቦች ተብለው በዓለም ታሪክ ከሚዘከሩት ውስጥ የቻይናውያን ረሀብ ኣይዘነጋም። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ1958-1961 ድረስ ቻይና ውስጥ ከፍተኛ ረሀብ ተከስቶ ወደ ሰላሳ ሚሊዮን ህዝብ ረግፏል። ብዙ ምሁራን እንደሚሉት ለዚህ አስከፊና ቻይናውያን ሊረሱት ለማይችሉት ረሀብ አንደኛ ተጠያቂ ማዖ ዚዳንግን ነው። የኮሙኒስት ፓርቲ መሪ የነበረው ማዖ ዚዳንግ በሶቪየት ህብረት በነጆሴፍ ስታሊን አብዩት ፍቅር የከነፈ ሲሆን ቻይናን በአምስት ዓመታት ውስጥ ከሁዋላ ቀር ግብርና አውጥቼ ወደ ኢንዱስትሪ እለውጣታለሁ በማለት Great Leap Forward ታላቁ የግስጋሴ ርምጃ የተሰኘ የአምስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን እቅድ ነድፎ አመጣ። እቅዱ የግል የመሬት ባለቤትነትን የሚጻረርና የወል እርሻን የሚያራምድ ነበር። በዚሁ እቅድ መሰረት ቻይናውያን በፍጥነት እየተደራጁ የወል እርሻ ሥራን … [Read more...] about በርሀብ የሚገድል መንግሥት እንዴት በሥልጣን ላይ ይቆይ?
ግፍ በገፍ የሞላበት አገር!
ከደቡብ ኦሞ እስከ መተማ፤ ከጅጅጋ እስከ ጋምቤላ፤ ከመቀሌ እስከ ባሌ፤ ከወልቃይት እስከ ኮንሶ! በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ ቅድመ-አያቶች፣ አያቶች፣ ወላጆችና ልጆች፤ ሦስትና ከዛም በላይ የሆነ ትውልድ ተመሳሳይ በሆኑ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መሃል ተተብትቦ የሚማቅቅ ከሆነ የዛ ማህበረሰብ ጉዞ ጤናማነትና አቅጣጫ ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል፡፡ በእንዲህ አይነት ማህበረሰብ ውስጥ መሰረታዊ የሆኑና የጎሉ ለውጦች ብዙም አይስተዋሉም፡፡ አንዳንዶቹም ለውጦች የቁልቁለት ጉዞ ውጤቶች ይሆኑና በራሱ ብቻ ሳይሆን በአያቶቹም ቁስል የሚማቅቅ፣ መቃብር ቆፋሪና ሸክሙ የከበደው ትውልድ ይፈጠራል፡፡ ይህ አይነቱ ትውልድ የተጫነውን ሸክሙን አራግፎ በነገ ህይወቱና ጥቅሞቹ ዙሪያ ላይ በማተኮር ለፈጠራና ለምርምር ሊያውለው የሚችለውን አቅሙንና ጊዜውን ያልኖረበትን ትላንትን እያመነዠከና የወረሰውን … [Read more...] about ግፍ በገፍ የሞላበት አገር!
በወልቃይት ጠገዴና ቃብቲያ ሁመራ ህዝብ ላይ የታቀደው የህወሃት ድብቅ ሤራ
ከዚህ በታች የምታነቡት በትግረኛ ተጽፎ የህወሓት ባለስልጣናት የተወያዩበትና የተስማሙበት ድብቅ መረጃ ነው። ይህ ረቂቅ ዶኩመንት በወያኔም ባለስልጣናት ተቀባይነት አግኝቶና ጸድቆ በተግባር በአስቸኳይ በወልቃይት ጠገዴና ቃብቲያ ሁመራ ህዝብ ላይ በተግባር ላይ እንዲውል ስምምነት ተደርሶበታል። ይህ በትግረኛ የተዘጋጀውና ወደ አማርኛ የተተረጎመው ሰንድ የተዘጋጀውና በህወሃት ባለስልጣናት እንዲተገበር ያቀረበው በብዕር ስሙ ዘጽኣት አናንያ በሚል ስም የሚታወቅ እውነትኛ ስሙ ግን ጎይቶኦም የማነ ገብረኣናንያ የተባለ ቀንደኛ የህወሃት ስውር ፊታውራሪ ነው። ከትግረኛ ወደ አማርኛ የተተረጎመውን ከዚህ ቀጥሎ ያንብቡ። በትግረኛ የተጻፈው በመጨረሻዎቹ ገጾች ላይ ማንበብ ይቻላል። ባለፉት 15 ኣመታት በትንሽ ግለሰቦች ሲነሳ የቆየ ባሳለፍናቸው ትንሽ ኣመታት ደግሞ የተቃውሞ ቅርፅ እየያዘ … [Read more...] about በወልቃይት ጠገዴና ቃብቲያ ሁመራ ህዝብ ላይ የታቀደው የህወሃት ድብቅ ሤራ
ከተማርኩት ቁጥር 1
ያሜሪካ ቆይታዬ በጣም አጭር ነው። ሁለት አመት እንኳን አይሞላም። ላገሩ አሁንም ላገሩ ባዳ ለወንዙ እንግዳ ነኝ። ገና ብዙ ያልገባኝ ነገር አለ። ግን በዚህች አጭር ጊዜም ቢሆን ብዙ ጠቃሚ ነገር ተምሬያለሁ ብል “አይ ገና ምኑ ተይዞ” እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ለምን ቢባል ልማር ላለ ሳር ቅጠሉ እውቀት መሆኑን ታውቁታላችሁ ብዬ ነው። ይልቅስ ለመሆኑ ምን ተማርክ ብትሉኝ ወጌን እጀምራለሁ። አዎ! ብዙ ነገር። ከእንግዲህ ምናልባት ሰሚ ካገኘሁ ከተማርኩት እያልኩ በተከታታይ አንዳንድ ነገር ለማካፈል አቅጃለሁ። ታዲያ እኔ ትምህርት አገኘሁበት ያልኩት ነገር ከታወቀ የቆየ ወይም የፊደል ቆጣሪ ግንዛቤ ሆኖ ካገኛችሁት የሞተውን አባባ ይለዋል ወይም የልጅ ነገር ሳትሉ ሃሳብ ስጡበት። እኔ አላማዬ መማር ስለሆነ ከስህተቴ እማራለሁ። ከተማርኩት ቁጥር 1 ወደፍሬ ነገሩ ከመግባቴ በፊት … [Read more...] about ከተማርኩት ቁጥር 1
የሃገራችን መድብለ ፓርቲ ሥርዓት ተግዳሮቶች
በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ውይይት ለማንሳት ስነሳ በ1994 ዓ.ም የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በቤተ መንግስት ውስጥ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር ሲወያዩ አንድ ምሁር የተናገረው ነገር ትውስ አለኝ። ትዝ ይላችሁ እንደሆነ የዚህ ምሁር ንግግር ብዙዎችን ኣስደምሞ ነበር። ለማስታወስ ያህል ይህ ምሁር ለራሳቸው ጠቅላይ ሚንስትር ለነበሩት ለአቶ መለስ እንዲህ ነበር ያለው። “እዚህ አገር ሌላ መድብለ ፓርቲ ስርዓት ተመስርቶ፣ ገበሬው ውስጥ ገብቶ ፋይዳ ያለው ለውጥ አይኖርም እርስዎ እያሉ። አይኖርም። ምክንያቱም እርስዎ እንዳይኖር ያደርጉታልና ነው። እስካሁን በዚህ ተሳክቶልዎታል በሚቀጥሉት ሃያ ኣመታትም ይህንኑ ያደርጋሉ።” የሚገርመው ይህ ምሁር ምንም ውስብስብ ነገር አልተናገረም። ብዙ ምጡቅ አሳቦች በዚህ ስብሰባ ላይ ተነስተው ነበር። ይሁን እንጂ በተለይ የዚህ … [Read more...] about የሃገራችን መድብለ ፓርቲ ሥርዓት ተግዳሮቶች
$200 million deal to bring slavery period in the 21st century
The Bank Hapoalim has made a deal to loan 200 million dollar for the purpose of assisting the rapid growth of land grabbing in Ethiopia. In the Omo valley in Ethiopia farmers are being forcibly displaced from their land in the pretext of sugar plantation which is financed and sponsored by the largest Israel’s bank (Bank Hapoalim) with more than $200 million. The Ethiopian government amazingly brought the 18th and 19th century slavery and colonial period back and applied the slavery methods on … [Read more...] about $200 million deal to bring slavery period in the 21st century
ህወሃት – 9 ስደተኞችን ደብዳቤ ጽፎ ከአሜሪካ ወሰዳቸው
ከተለያዩ አገራት አሜሪካ ገብተው የስደት ማመልከቻ ያስገቡ 9 ኢትዮጵያውያንን ህወሃት ተረከቦ ወደ አገር ቤት እንደወሰዳቸው ታወቀ። አንዱ ራሱን ለማጥፋት ሞከሮ ነበር። ወደ ኢትዮጵያ ቢሄድም የጤናው ሁኔታ አልታወቀም። ድርጊቱን አስመልክቶ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ከህወሃት ተግባር በላይ በራሳችን አዝኛለሁ” ሲሉ ወጣቶቹን ለማዳን ያደረጉት ጥረት መረጃው ዘግይቶ ስለደረሳቸው አለመሳካቱን አመለከቱ። “ለቤተሰቦቼ የት እንዳለሁ እንኳን ነግሬያቸው አላውቅም” ሲል የተናገረውን ወጣት ጨምሮ ህወሃት የተረከባቸው ኢትዮጵያዊያን ወግኖች አሜሪካ ለመድረስ እስከ 14 ወራት ፈጅቶባቸዋል። በብራዚል፣ በኮሎምቢያ ጫካ አቋርጠው፣ በፓናማ ወንዝ ተሻግረው፣ በሜክሲኮ አድርገው በአጠቃላይ እስከ 16 የሚደርሱ አገራትን አልፈው በተለያዩ መንገዶቸ አሜሪካ ደርሰው ጥገኝነት የጠየቁት ወገኖች ህጉ ከሚፈቅደው ውጪ … [Read more...] about ህወሃት – 9 ስደተኞችን ደብዳቤ ጽፎ ከአሜሪካ ወሰዳቸው