• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከተማርኩት ቁጥር 1

March 12, 2016 05:41 am by Editor 2 Comments

ያሜሪካ ቆይታዬ በጣም አጭር ነው። ሁለት አመት እንኳን አይሞላም። ላገሩ አሁንም ላገሩ ባዳ ለወንዙ እንግዳ ነኝ። ገና ብዙ ያልገባኝ ነገር አለ።

ግን በዚህች አጭር ጊዜም ቢሆን ብዙ ጠቃሚ ነገር ተምሬያለሁ ብል “አይ ገና ምኑ ተይዞ” እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ለምን ቢባል ልማር ላለ ሳር ቅጠሉ እውቀት መሆኑን ታውቁታላችሁ ብዬ ነው። ይልቅስ ለመሆኑ ምን ተማርክ ብትሉኝ ወጌን እጀምራለሁ።

አዎ! ብዙ ነገር። ከእንግዲህ ምናልባት ሰሚ ካገኘሁ ከተማርኩት እያልኩ በተከታታይ አንዳንድ ነገር ለማካፈል አቅጃለሁ። ታዲያ እኔ ትምህርት አገኘሁበት ያልኩት ነገር ከታወቀ የቆየ ወይም የፊደል ቆጣሪ ግንዛቤ ሆኖ ካገኛችሁት የሞተውን አባባ ይለዋል ወይም የልጅ ነገር ሳትሉ ሃሳብ ስጡበት። እኔ አላማዬ መማር ስለሆነ ከስህተቴ እማራለሁ።

ከተማርኩት ቁጥር 1

ወደፍሬ ነገሩ ከመግባቴ በፊት ተማርኩባቸው የምላቸው ጉዳዮችን የማነሳው ሀገሬ ኢትዮጵያን በሆዴ ይዤ መሆኑን ልብ በሉልኝ። ባጭሩ መሰረታዊ ጉዳያችን ታላቋ ኢትዮጵያ (ለኔ ዛሬም ኢትዮጵያ ታላቅ ናት) ከታላቋ አሜሪካ ህይወት ምን ልትማር ትችላለች የሚል ነው።

ስለ ጦርነት

አሜሪካኖች እርስበርእሳቸው ተዋግተዋል። ለአምስት አመት። ከ600 ሽህ ህዝብ በላይ አልቋል። ልባአድርጉ! የተዋጉት እርስበርስ ነው። ከዚህ የታሪክ ክስተት መነሻና መድረሻ ለሀገራችን ጉዳይ የሚጠቅም ቁም ነገር ማግኘት ይቻላል። በመጀመሪያ ኢትዮጵያውያን እርስበእርሳችን ስንዳማ መኖራችን የሚያስመሰግን ባይሆንም ካለም ለይቶ የሚያስረግመን ገጠመኝ አይደለም። በዘመኑ የተሻለ ስልጣኔ የነበራቸው አሜሪካኖች ዴሞክራሲያዊ የሚባል ስርአት ከገነቡ በኋላ እንኳን በዚያን ጊዜ ባስከፊነቱ ወደር አልባ የነበረ እልቂት ያስከተለ ጦርነት አካሂደዋል። ከዚህ አንፃር ሲታሰብ የኢትዮጵያውያን ልምድ ባይወደስም ጉድ ሊባል አይገባም።

ከዚህ ሁሉ የበለጠው ትምህርት ግን ጦርነትን የታሪክ ትምህርት እንጂ የዘወትር የጀግንነት ስራ አድርጎ ያለመቀጠል ነው። አሜሪካኖች ጦርነቱን ታላቅ ሀገርና ጠንካራ የፍትህ ስርአት ገንብተውበታል። ዳግመኛም አላካሄዱትም። ጦርነታቸውን ሌላ ጦርነት የማያስነሳ ስርአት መሰረቱበትና ታሪክ ብቻ ሆኖ እንዲቀር አደረጉት። እኛም ማድረግ ያቃተንና ማድረግ ያለብንም ይህንን ነው። መኮነን ያለብን ያሳለፍነውን ጦርነት ሳይሆን የሚመጣውን አዲስ ጦርነት ነው። አሜሪካኖች አንድ ጊዜ ደም ተፋሰው የጦርነትን በር ዘጉ። እኛ የታሪክ ጦርነቶችን እያብሰለሰልን ላዲስ ጦርነት ጠመንጃ እንወለውላለን። ልዩነታችን እዚህ ላይ ነው። በጦርነት ስልጣን የያዘው አካል ጦርነት በታሪክ ያደረሰብንን ጉዳት በማጤን ዳግም ደም አፋሳሽ ግጭት እንዳይነሳ ለሰላምና ለህዝብ ደህንነት በግንባር ቀደምትነትና በሆደሰፊነት ጠንክሮ ከመስራት ይልቅ ወንድ የሆነ ይምጣ አይነት ፉከራን ያሰማናል። እንዲያውም ራሱ ቀድሞ በራሱ ህዝብ ላይ ጦርነት አውጆ ህዝብ በከፈለው ግብር ጥይት እየገዛ ህዝብ ላይ ይተኩሳል። ሌላው በበኩሉ ለነፃነትና ሰላም መፍትሄው ጠመንጃ ነው በሚል አቀባብሎ ደም ሸቶኛል ይላል።

ዳያስፖራውም ቢሆን ቢያንስ ጦርነት አከል ንግግር አላጣም። እና ሁላችንም ተደምረን ስንሰማ ዜማችን አንድ ነው። ይሄውም፤ ትናንት ስንዋጋ ነበር፤ ዛሬም እንዋጋለን፤ ነገም እንዲሁ፥ የሚል ነው። ክፉ አባዜ!

አሜሪካኖች ከጦርነት ዘላቂ ሰላም፣ ነፃነትና ፍትህን ሲመሰርቱ እኛ ከጦርነት ተነስተን ወደ ጦርነት እንጓዛለን። አሜሪካኖች ከጦርነት ልማትን ተምረው ሰላማዊ ስርአት ሲመሰርቱ እኛ ግን ከጦርነት ለነገ የሚሆነንን አዲስ ጥፋት እንቀስማለን።

እኔ ግን የተማርኩትና ያገሬ ሰውም እንዲማር የምመኘው ከጦርነት ጥፋትን ሳይሆን ደህንነትን፣ ከግጭት ቂምን ሳይሆን ፍቅርን፣ ከስህተት ስህተትን ሳይሆን እርምትን እንማር ዘንድ ነው። እናም እኔ ካሜሪካኖች ታሪክ የተማርኩት የመጀመሪያው ቁምነገር ይህንን ነው። ሌላውን ሌላ ጊዜ ማንሳቴ አይቀርም። ሰላም ሁኑልኝ፡፡

ህሩይ ደምሴ

ከዋሽንግተን ዲሲ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    March 18, 2016 04:03 pm at 4:03 pm

    ወንድሜ ህሩይ

    በወገኔና በአገሬ ላይ ከገጠመኝና አልወለድ ካለ የጽንስ ምጥ የገላገልከኝ መሰለኝ!ለካ እንዲህ እንዳንተ ያሉ ቅን ሃሳብ ያላቸው ወንድሞች በየቦታው አሉ በማለት ከእንቅልፌ ነቃሁ! በርታ ወንድሜ! አብረን እንጬህ በጎ የሆነውንም በተግባር እናሳይ!በለው፣ አሳደው፣ ድፋው፣ አሳየው፣ ፉከራው፣ ጥላቻውና መነቋቆሩ ወዘተ የትም አላደረሰንምና በፍቅር ለሁለንተናዊ የዘመናት ችግራችን በጋራ ምክክር አብረን ለበጎ ሥራ እንነሳ???

    ይህችን አባባልህን ወደድኳት:

    እኔ ግን የተማርኩትና ያገሬ ሰውም እንዲማር የምመኘው ከጦርነት ጥፋትን ሳይሆን ደህንነትን፣ ከግጭት ቂምን ሳይሆን ፍቅርን፣ ከስህተት ስህተትን ሳይሆን እርምትን እንማር ዘንድ ነው። እናም እኔ ካሜሪካኖች ታሪክ የተማርኩት የመጀመሪያው ቁምነገር ይህንን ነው። ሌላውን ሌላ ጊዜ ማንሳቴ አይቀርም። ሰላም ሁኑልኝ፡፡

    መልካም ፈቃድህ ከሆነ በኢሜል ተገናኝተን በመመካከር ለምስኪኑ ወገናችን ሰላም በእግዚአብሔር ስም በጎ ሥራ አብረን እንሥራ: eunethiwot@gmail.com

    የፍቅር አምላክ በመለኮታዊ ፍቅሩ በጽሑፍህ ላይ ከገለጥከው በበለጠ መልኩ:
    ለራሱ ክብር!
    ለምስኪኑ ወገንህ ጥቅምና ሰላም!
    ለክፉው ደግሞ መዋረድ!
    በሃይልና በስልጣን ይግለጥህ!!!

    ይህ ከሆነ ሕልምህ እኔም አብሬህ ነኝ!!!

    በእውነት ወንድምህ

    እውነቱ ነኝ

    Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 09:31 pm at 9:31 pm

    Mikirih melkam new hizibum yaminal. Hulum sew Mihur Mehayimu yemisasatew neger:- Ethiopian yemimeraw akal Satan /LUSIFER MEHONUN / YIZENEGALU. Wendime eski hasabihin le Lusiferu asredaw.KETEKEBELEH WEDE AGANINTINET ZIK BILOWAL MALET NEW 10 % KETEGEBERE JINI HONWAL MALET NEW. 50 %ketekebeleh yih jini tamo yihonal.ANTE YALKEWIN 90% KETEKEBELE YIH JINI MOTOWAL MALET NEW. Lije berta jiniw bimot le Ethiopiachim melkam new.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule