• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሞረሽ የዐማራ ድምፅ የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋም ለምን አስፈለገ?

March 17, 2016 01:58 am by Editor Leave a Comment

ባለፉት ፳፭(ሃያ አምሥት) ዓመታት በዐማራው ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ከችግሩ ሥፋት እናጥልቀት አንፃር ተመጣጣኝ የሆነ የሚዲያ ሽፋን አልተሰጠውም። በ«ኢትዮጵያዊነት» ስም በተቋቋሙት ድርጅቶችም ሆነ በተለያዩ አገሮች መንግሥታት ሥር የሬድዮ እና የቴሌቪዥን መርኃ-ግብሮችን በአማርኛ ቋንቋ የሚያሠራጩ ሚዲያዎች በዐማራው ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እና በደል የዓለም ማኅበረሰብ እንዲያውቀው የማድረግ ፈቃደኝነታቸው እጅግ ውስን መሆኑን በተደጋጋሚ ታይቷል። ይህም «ችግሩ ችግራችን ነው» ብሎ የሚይዝ ሚዲያ አለመኖሩን ያረጋግጣል። ስለሆነም እኛ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት አባሎች እና ደጋፊዎችለመላው የዐማራ ሕዝብ ድምጽ የሚሆን የሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም ቆርጠን ተነስተናል። ዐማራው በተገንጣይ እና ጠባብ የጎጠኞች ቡድኖች የተክፈተበትን የሥነ-ልቦና ጦርነት ተመጣጣኝ በሆነ ኃይል በመመከት እውነተኛውን ገፅታ ለማሣየት፣ የሚያስችል የአጸፋ ፕሮፓጋንዳ እና ቅስቀሣለመሥራት፣«ሞረሽ የዐማራ ድምፅ ሬድዮ» በአየር ላይ መዋል ለነገዳችን ህልውና በጣም አስፈልጓል።

ለሩብ ምዕተ-ዓመት በዘለቀው የትግሬ ወያኔ ዘረኛ አገዛዝ፣ ክ፭(አምሥት) ሚሊዮን በላይ ዐማሮችን በልዩ ልዩ መንገዶች ከምድረ ገፅ እንዲጠፉ ተደርጓል። ይህን ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦችን እና ቡድኖችን ለፍትኅ ለማቅረብ የተቀነባበረ የመረጃ ልውውጥ አስፈላጊነቱ አጠያያቂ አይደለም። የዐማራውን ነገድ ለመታደግ የሚቻለው ዐማራው ተደራጅቶ በኅብረት ጥቃቱን ሲመክት ነው። ሰለሆነምዐማራው የሚፈጸምበትን የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ወንጀል ለመቋቋም የሚችለው፣በጠንካራ መሠረት ላይ ተደራጅቶ የሚደርስበትን ጥቃት ለመቋቋም ሲዘጋጅ መሆኑን መቀመበል ያስፈልጋል። ለዚህም ተጣጣኝ የሥነ-ልቦና ትጥቅ ለመታጠቅ የሬድዮ ድምጽ አስፈላጊ ነው። በዚህ ረገድ የዐማራው ልጆች «የወገናችን ችግር ችግራችን ነው፤ ብሦቱም ብሦታችን ነው፤ ከሁሉም በላይ ዘራችን መጥፋት የለበትም» ብለን ከተነሣን፣ እንኳንስ እንዲት የአጭር ሞገድ የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋም ቀርቶ፣ ሁሉን-አቀፍ የሆነ የዐማራ ሚዲያ ማዕከል ለመመሥረት መቻላችን ጥርጥር የለውም።

በመሠረቱ የዐማራው ሕዝብ ጠላቶች በቅድሚያ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላቶች ናቸው። ዐማራው እንዲጠፋ የተወሰነበት አብይ ምክንያት በታሪኩ የሚተማመን፤ አትንኩኝ ባይ፤ለነፃነቱ ቀናዒ፤ለህልውናው እና ለአገር ዳር ደንበር ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ሟች ፍፁም ኢትዮጵያዊ በመሆኑ ነው። በዐማራው ነገድ ላይ ጥቃት የተጀመረው ዛሬ ሣይሆን ከ፭፻(አምሥት መቶ) ዓመታት በፊት በቱርኮች እና በአረቦች ድጋፍ ግራኝ አሕመድ ካካሄደብን የጅምላ ጭፍጨፋ ጀምሮ እንደሆነ ይታወቃል። ከግራኝ ጭፍጨፋ ተከትሎ የኦሮሞዎች ወረራ ተከተለ፤ ከዚያም በዘመነ-መሣፍንት ከፍተኛ የሆነ ዕልቂት የደረሰው በዐማራው ላይ ነበር። ፋሽስት ኢጣሊያም ከአንዴም ሁለቴ ከፍተኛ ጥፋት ያደረሰችው በዐማራው ላይ ነበር። ደርግ ገና ሥልጣን ከመያዙ አስቀድሞ የዘመተው በዐማራው ላይ መሆኑ የቅርብ ዘመን ትውስታችን ነው። የትግሬ-ወያኔ ዘረኞች ገና ከጠዋቱ በርሃ ሲገቡ ጀምረው በፕሮግራማቸው ያሰፈሩት ዋና ጠላታቸው ዐማራ እንደሆነ እና ከተቻለም ከኢትዮጵያ ምድረ ገጽ እንዲጠፋ፣ካልሆነ ደግሞ አቅመቢስ ባርያቸው አድርገው ለመግዛት መሆኑ ግልፅ ነው። ይህንን ጽኑ ፍላጎታቸውን እውን ለማድረግ ከበረሃ ጀምረው በዐማራ ሕዝብ ላይበፍርሃት ተጨምድደው በመሠረቱት ጥላቻ፣ በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስሙን ጥላሸት ቀብተውታል፤ መሬቱን ቀምተውታል፤ በአገሩ ላይ ሁለተኛ ዜጋ በማድረግ ከኖረበት ቀዬው እንዲፈናቀል አድርገውት እናያለን። ለዚህም ማረጋገጫው ላለፉት ፶(ሃምሣ)ዓመታት በሻቢያ፣ በትግሬ-ወያኔ እና  በኦነግ አማካይነት በዐማራው ሕዝብ የተፈጸመው የሥነ-ልቦና ጥቃት ሕዝባችንን ከነበረበት በራስ የመተማመን ደረጃ አወርዶት ይገኛል። ዐማራው ይህን በረቀቀ እና በግልፅ በተቀነባበረ ሥልት የሚፈፀምበትን አደገኛ የሥነ-ልቦና ምት፣ ሁለገብ የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሊቋቋም የሚችለው በአንድ ዐላማ ሥር አንድ ሆኖ ሲቆም ብቻ ነው።ሰለሆነም «ሞረሽ የዐማራ ሬድዮ ድምፅ» የተጎዳውን የወገኖቻችን ሥነ-ልቦና ለማደስም ሆነ የወንድማማችነት  መንፈስ ለማጎልበት ያገለግለናል።

ለአንድ ዓላማ ግብ መምታት በሥርዐት ላይ የተመሠረተ ዝግጅት እና መሠናዶ እጅግ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ነው። ይህ አካሄድ በግል ሕይዎታችንም ስኬት ለማግኘት ያስችላል። ለመዘጋጀት እና ለመስናዳት ደግሞ ቅንብር እና ድርጅት ያስፈልጋሉ። መደራጀት ጠላትን ለይቶ ለመመከት እና አሸንፎ ለመውጣት ያግዛል።

መደራጀት ተመጣጣኝ ኃይል ፈጥሮ በማናቸውም ጊዜ እና ቦታ  ለድርድር ያበቃል። ስለሆነም የሬድዮው ድምጽ በትግሬ-ወያኔ የተመዘዘበትን የጥፋት ሰይፍ ወደ አፎቱ ለማስገባት ዐማራው ለአንድ ዓላማ፣ በአንድ ልብ፣ በፍጹም የወንድማማችነት መንፈስ መነሣት እንዲችል፣በእውነት እና በእውቀት ላይ የቆመ የፕሮፓጋንዳ እና የቅስቀሣ ስራዎችን ለማክናወን የሚያስችል ፍቱን መሳሪያ ነው። ሞረሽ የዐማራ ድምጽ ሬድዮ«ዐማራው ከገባበት አጣብቂኝ ወጥመድ ሰብሮ ለማምለጥ ምን ማድረ አለበት? እንዴትስ በይፋ በአገር አቀፍ ከታወጀበት የዘር ማጽዳት ሤራ እርምጃ ሊተርፍ ይችላል?» የሚሉትን እና የመሳሰሉትን ጉዳዮች በመዳሰስ በኢትዮጵያ ምድር እንደስፌድ ቆሎ ተብትኖ ለሚገኙት ዐማራ ወገኖቻችን ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን እንዲደርስ ያደርጋል።

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የካቲት1 ቀን 2008 ዓ.ም. በቁጥር ሞወዐድ 000100-08 «ሞረሽ የዐማራ ድምፅ ሬድዮ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የእርዳታ ማሰባሰቢያ ጥሪ» በዓለም ለሚገኙ ዐማራ ወገኖች እና ወዳጆች ማቅረቡን በዚህ አጋጣሚ ለማስታወስ እንወዳለን። «ለወገን ችግር ፈጥኖ ደራሹ ወገን ነውና» በሜልበርን (አውስትራሊያ) እና በካልገሪ (ካናዳ) የሚገኙ የሞረሽ-ወገኔ  መሠረታዊ ማኅበራት አባሎች እና ደጋፊዎች የጉዳዩን አጣዳፊነት እና አስፈላጊነት ጠንቅቀው በመገንዘባቸው፣እሑድ የካቲት27 ቀን 2008ዓ.ም. የመጀመሪያ ዙር የገንዘብ እርዳታ ማሰብሰብ ዝግጅት አከናውነዋል። ይህ ጥረት በሚገባ ተጠናክሮ በሁሉም የዓለማችን ክፍሎች ሊቀጥል ይገባዋል።ዐማራው ከገባበት የሚያባራ ጥቃት እና ሰለባ ሊያመልጥ የሚችለው፣ በንጹህ የመላው ዐማራ የወንድማማችነት/እህትማማችነት መንፈስ በአንድነት ቆሞ በምድር ውስጥ የቁም ስቃይ እና መከራ ለሚበላውወገናችን ድምፅ ሲሆን ብቻ ነው። በመሆኑም «ሞረሽ የዐማራ ድምጽ ሬድዮን» ተረባርበን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለአየር እንድናበቃው በዐማራነታችን የሚጠበቅብንን ግዴታ እንድንወጣ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ጥሪውን ለመላው የዐማራ ሕዝብ ያስተጋባል።

የዐማራው ኅልውና ጉዳይ ለዐማራው ብቻ ሊተው አይገባም። የእንቁጣጣሽ በግ ሲታረድ የመስቀሉ በግ ይስቃል እንዳይሆን፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከአገራችን ምድረ ገጽ እንዲጠፋ ከተበየነበት የዐማራ ሕዝብ ጎን በመቆም የዜግነት እና የንፁህ ኢትዮጵያዊ ወንድማማችነት/እህትማማችነት ድርሻ ሊወጣ ይገባዋልና ሞረሽ የዐማራ ሬድዮ ድምጽ እንድትረዱ በዚህ አጋጣሚ ጥሪ እናቀርባለን።

በግፈኛ ዘረኞች ድምፁ ለታፈነው ዐማራ ድምፅ እንሁነው!
ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!
ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ በጀግኖች እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule