• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዕርቅ ሃሳብ ከውስጥም ከውጭም ትኩረት ስቧል

March 17, 2016 07:54 am by Editor 2 Comments

አሁን ኢትዮጵያ ለደረሰችበት አሳሳቢ ደረጃ ዋናውና ብቸኛው መፍትሔ ሰላማዊ ዕርቅ መሆኑ በአገር ውስጥና በውጪ ልዩ ትኩረት እየሳበ መሆኑ ተሰማ። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ኢህአዴግ በራሱ ችግር በየጊዜው ከሕዝብ ጋር ቅራኔ ውስጥ መግባቱን፣ ይህንን ቅራኔ መፍታት ካልቻል መንገዱ የውድቀት እንደሚሆን አስጠነቀቁ። ሕዝብ በአፉና በእጁ እየገፋን ነው አሉ።

ለጎልጉል የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በቅርቡ የተጀመረውን “የኢትዮጵያ የዕርቅና ርትዓዊ ፍትሕ ምክርቤት” ተከትሎ የዕርቅ ሃሳብ አሁን ኢትዮጵያ ላለችበት ሁኔታ አማራጭ የሌለው እንደሆነ እየተጠቆመ ነው፡፡ በተለይ በውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ጉዳይ ተከታታዮችና ፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ ጉዳዩ ድጋፋቸውን የሚሰጡበት እንደሆነ መረጃው አመልክቷል፡፡ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የተመሠረተው ምክርቤት ድጋፍ እንደሚያስፈልገው በመጠቆም ስለምክር ቤቱ ዓላማ ከተረዱ በኋላ “አሁን አገሪቱ ለገባችበት ስጋት ብቸኛው መፍትሔ እርቅ እንደሆነ” እንደሚያምኑና ወቅቱን ጠብቀው ድጋፋቸውን በግልጽ እንደሚሰጡ መረጃው አመልክቷል።

“የኢትዮጵያ የዕርቅና ርትዓዊ ፍትሕ ምክርቤት” ምሥረታን አስመልክቶ መግለጫ ያሰራጨውን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ስለ ጉዳዩ የሚያውቀው ካለ ማብራሪያ እንዲሰጠን ጠይቀን፤ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

ይኽው “የኢትዮጵያ የዕርቅና ርትዓዊ ፍትሕ ምክርቤት” መመሥረቱን ጠቁሞ አኢጋን ሰሞኑንን ባሰራጨው መግለጫው ላይ “… በግድያ እና በብቀላ ዑደት ውስጥ ባለችው አገራችን ዘላቂ ሰላምና ፍትሕ ሊያመጣ የሚችል ብቸኛው ተስፋ ከዚህ የብቀላ አዙሪት በመውጣት ይቅርታን፣ ዕርቅንና ርትዓዊ ፍትሕን መፈለግ ሊኬድበት የሚገባ አዲሱ መንገድ መሆኑ በየጊዜው ግልጽ እየሆነ መምጣቱ ከዚህ ምክርቤት ምሥረታ ጋር አብሮ የሚጠቀስ እውነታ ነው” ሲል ምክር ቤቱ የተወለደበትን ጊዜና ወቅት ትክክለኛነት አውጇል።

መግለጫው አያይዞም “… በዘር በተከፋፈለች አገራችን ተግባብቶ ለመኖር የሚችል ኅብረተሰብ ለመመሥረት የሚቻለው እያንዳንዳችን ከታገትንበት የዘር፣ የጎሣ፣ የነገድ፣ … ሣጥን በመውጣት ሌሎችን እንደራሳችን በመመልከትና ከዘር ወይም ከማንኛውም ልዩነታችን በፊት ለሰብዓዊነት ቅድሚያ መስጠት የሚያግባባ ሃሳብ የሆነበት ደረጃ ላይ” መደረሱንም አመልክቷል።

“… በአገራችን ዕርቅ፣ የጉዳት ፈውስ፣ ርትዓዊ ፍትሕ በሕዝብ መካከል እስካልተደረገ ድረስ የወደፊቱ ኅልውናችን አሁን ካለንበት እጅግ የከፋ ሊሆን እንደሚችል” የጠቆመው የአኢጋን መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ “ለመተማመን እንነጋገር” በሚል መሪ መፈክር ያካሄደው ተከታታይ ስብሰባ ለዚህ የምክርቤት ምሥረታ በዋንኛነት የሚጠቀስ ግብዓት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ መግለጫው ይህንን ሲያስረዳም “መነጋገር ወደ መደማመጥ፣ መደማመጥ ወደ መተማመን፣ መተማመን ደግሞ ወደ ዕርቅ ይመራናል” በማለት እጅግ ለተወሳሰበው የኢትዮጵያ ችግር መፍትሔ ሁሉም ሊያስተውለው በሚችል መንግድ አስረድቷል፡፡ “ከዚህ አንጻር በዚህ ምክርቤት ውስጥ መካተት የማይችል አይኖርም” ያለው መግለጫ “እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወደ መተማመን የሚያደርስ ንግግር እንዲጀምር” ምክርቤቱ ለሁሉም ጥሪውን አቅርቧል፡፡

ሰሞኑን ለኢህአዴግ ጉባኤ የስድስት ወር ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ሃይለማርያም እርስ በእርሱ በሚጋጨው ዲስኩራቸው ስለመታረቅ ተናግረዋል። እንደሳቸው አባባል በፈተና ውስጥ የማለፍ ልዩ ብቃት ያለው ኢህአዴግ፣ አሁን ያጋጠመውን ፈተና እንደሚሻገረው ሲያስገነዝቡ “ሌላ አካል ላይ ጣታችንን ከመቀሰር ችግሩ የራሳችን መሆኑን አስምረን ማለፍ አለብን” በማለት ነበር። ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ፈጥኖ ምላሽ ስለማይሰጥ ኢህአዴግ ከህዝብ ጋር ቅራኔ ውስጥ መግባቱን አቶ ሃይለማርያም ሳይሸሽጉ በይፋ ተናግረዋል።

አቶ ሃይለማርያም ለተፈጠሩት ችግሮችና ለተነሳው ተቃውሞ ሌላ ሃላፊነት አለመውሰድ ዋጋ እንደሚያስከፍል ጠቁመዋል። “… ሌላ ምክንያት መፍጠር ቀዳሚው የውድቀት መንገድ ነው” በማለት የህዝብን ጥያቄ መልሶ ከሕዝብ ጋር መታረቅ የድርጅታቸው ብቸኛው አማራጭ እንደሆነ አስረድተው፣ ህዝብ ስርዓቱን በአፉና በእጁ እየገፋ መሆኑንን አምነዋል። ከትግራይ እስከ ደቡብ ክልል ጫፍ ተመሳሳይ ችግር እንዳለ አውስተው ችግር ባለበት ችግሩን በመፍታት፣ ችግር ባልተከሰተበት አስቀድሞ ለህዝብ ጥያቄ መልስ በመስጠት ከህዝብ ጋር እርቅ መፍጠር አንገብጋቢ መሆኑንን አመላክተዋል። አቶ ሃይለማርያም ንግግራቸውን ተከተሎ በርካታ ወቀሳ ቢሰነዘርባቸውም፣ “ካሁን በኋላ አርሶ አደሩም ሆነ የከተማው ነዋሪ የነቃ ስለሆነ በትከሻው ላይ ተጣብቆ መኖር አይቻልም” ማለታቸው እንደ እውነት ተወስዷል።

“አቶ ሃይለማርያም ራሳቸውን ሆነው ችግሩን በተረዱበት መጠን አይናገሩም” ሲሉ የሚተቹ አንደበታቸው ነጻ መሪ አለመሆናቸውን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ይናገራሉ። ንግግራቸውንም ጉልበት አልባ ይሉታል። ከሕዝብ ጋር መታረቅ ሲሉ ስለ ምን ዓይነት ዕርቅ እንደሚናገሩ ይጠይቃሉ። “ባግባቡ ጥያቄ አቀርቦ አልተመለሰለትም” የሚሉት ሕዝብ ተገድሎና እየተገደለ፣ ታሰሮና እየታሰረ፣ ተደብድቦና አሁንም እየተደበደበ፣ ተስድዶና እየተሰደደ ባለበት ሁኔታ፣ አገሪቱ በወታደራዊ አስተዳደር ሥር ወድቃ፣ እንኳን ተራው ህዝብ እሳቸው ጠ/ሚኒስትር ሆነው በነጻነት ስራቸውን መስራት በማይችሉበት አገር ምን አይነት እርቅ ነው ከህዝብ ጋር የሚደረገው? ሲሉ ኢህአዴግን የሚመራው ህወሃት ስለ እርቅ በቅጡ ሊያስብበት እንደሚገባ ያሳስባሉ።

ስለ መታረቅ ከየአቅጣጫው እየተሰማ ነው። ሹመታቸውና አሿሿማቸው የራሱ ጣጣ ቢኖረውም የኦርቶዶክስ እምነት የበላይ የሆነው ሲኖዶስ “የአገሪቱ ችግር አሳሰበኝ” ሲል ድምጹን አሰምቷል። ከራሱ ከኢህአዴግ ወገኖች የዕርቅ ፍላጎት ያላቸው እንዳሉ ጎልጉል መረጃ አለው። ህወሃት አካሄዱ ያልጣማቸውና በስማቸው ወንጀል የሚፈጸምባቸው የህብረተሰብ ክፍሎችም በተመሳሳይ ዕርቅ እንዲወርድ ይወዳሉ። ትልቁ ችግር ያለው በዝርፊያ የከበሩት አካላት ዘንድ ነው። ለነሱ ይመስላል “ይድረስ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጉልበት ላላችሁ ሁሉ” በሚል ርዕስ ፕሮፌሰር መስፍን ሰሞኑንን “እግዚር በቀዳዳ ያያል” ሲሉ የልጅነት ወግ አዘል ከባድ መልክት አስተላለፈዋል።

“…የኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዓላማችሁ ምንድን ነው? እስከዛሬ ድረስ በየትም አገር በሰማይ ጠቀስ መቃብር ውስጥ የተጋደመ ባለሥልጣን የለም፤ ደግሞስ ሰማይ ጠቀስ መቃብር ካስፈለገ ለአንድ ባለሥልጣን ከነቤተሰቡ ስንት ሰማይ ጠቀስ ፎቆች፣ ስንት ሺህ ካሬ ሜትር መሬት ያስፈልጉታል … እስር ቤቶችን ሁሉ ዝጉ፤ የዘጋችሁትን አንደበት ሁሉ ልቀቁ፤ ያፈናችሁትን አእምሮ ሁሉ ለነጻነት አብቁት፤ ጭካኔን በርኅራኄ፣ ጉልበትን በእውቀት፣ ዱላን በክርክር፣ ቁጣን በፍትሐዊነት እየለወጣችሁና እያበረዳችሁ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ታረቁ፤ በተለይ ከኢትዮጵያ ወጣት ጋር ልብ ለልብ ተገናኙ፤ ነገ የወጣቱ ነው”፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. geresu says

    March 17, 2016 10:56 am at 10:56 am

    አገራችን ታማ ተኝታ ባልጋላይ ትተናት መጣን ሞት ሽረቷን ሳናይ!! አረ ጎራዉ አረ ጎራዉ ወልቃይትን አረሱት ዘቅዝቀዉ እንደቦይ አያሌዉ ቢሄድ ገዱ የለሞይ!! ገዱስ ቢለቅ /ቢታሰር/ቢገመገም አማራ የለሞይ! ጎንደር የለሞይ!! ጎንደር የለሞይ! ሰሜንሸዋ የለሞይ! ኦረሞ የለሞይ! :: ጎራዉ ተንዶ ጎራዉ ሲደለደል ይከን ጊዜ ነዉ ወያኔን መፈንገል!!!

    Reply
  2. gud says

    March 20, 2016 11:44 am at 11:44 am

    Yilik come invest in Ethiopia before it is too late .
    Every cry is a temporary hiccup before full liberalization .

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule