• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች

March 22, 2016 01:24 am by Editor Leave a Comment

ገዢው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት በየዕለቱ በሚያደርገው ፀረ-ኢትዮጵያዊ ተግባር፤ የተለያዩ የፖለቲካ ሕዝባዊ ስብስቦች መግለጫ ያወጣሉ። አዳዲስና ነባር የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አለን በማለት ስማቸውን በአንባቢዎች ያስመዘግባሉ። ለመሆኑ ጋዜጣዊ መገለጫዎች ለምንድን ጉዳይ ነው የሚወጡት? ማነው የሚያወጣቸው? መግለጫዎችን ተከትሎ የሚተገበሩት ምንድን ናቸው? አሉስ ወይ? መግለጫ አውጪዎቹና መግለጫ ያላወጡ የፖለቲካ ሕዝባዊ አካሎች መለያቸው ምንድን ነው? መግለጫዎችና አውጪዎቻቸው፤ ሕዝባዊ ናቸው ወይንስ ጠባብ ወገንተኛ? መልዕክት አላቸው ወይንስ አደረግሁ ለማለት የተወረወሩ? አስፈላጊነታቸውስ ምን ያህል ነው? በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ በተንጎደጎዱ ወቅት የደረሱኝ እጦማሮች ነበሩ። ሁሉም ወቀሳዎች ናቸው። “ለምን መግለጫ አታወጣም?” “ካሁን በፊትም ዝም ብለሃል!” የሚሉና ሌሎችም ከጠላት ጋር ወግነሃል ያሉኝም ነበሩባቸው። ለምንድን ነው መግለጫ ማውጣት ያለብኝ? መግለጫ አላወጣም። ይሄን ግልጽ በሆነ መንገድ ማስቀመጥ አለብኝ።

መንግሥታትና ድርጅቶች መግለጫ ሲያወጡ፤ መሠረታዊ ዓላማው፤ ጉዳዩ ካተኮረባቸው አካላት ጋር ተባባሪ መሆናቸውን አንባቢ ወይንም አዳማጭ እንዲያውቅላቸው አይደለም። መግለጫውን የሚያወጡት፤ ነግ ለኔ ብለው፤ ካሁኑ ቀድሜ እርምጃ እወስዳለሁ ማለታቸው ነው። ከማንኛውም መግለጫ ጋር፤ አብሮ የሚሄድ መልዕክት አለ። “የሚያስፈልገውን ለማድረግ እንጥራለን!” “ከዛሬ ጀምሮ ይሄን ወይንም ያኛውን እናደርጋለን!” “በሚያስፈልገው ነገር ሁሉ ልንረዳችሁ ዝግጁ ነን!” “ሊረዷችሁ የሚችሉ ሰዎችን ልከንላችኋል!” “ለመቋቋሚያ እንዲያግዛችሁ ገንዘብ ልከንላችኋል!” እና የመሳሰሉት ናቸው። እንግዲህ ልብ ብለን ብናጤነው፤ ዋናው የመግለጫው ማሠሪያ፣ ይሄ ከወደኋላ የተከተለው ተግባር ነው። እስኪ ወደኛ፤ በተለይም የገዢውን ቡድን ተግባር የሚያወግዙትን ጋዜጣዊ መግለጫዎችና አውጪዎቻቸውን እንመለስ።

በጠላትን ፈርጀው የሚታጋሉትን ገዢ ቡድን፤ “ይሄን በማድረጉ አውግዘናል!” ማለት ምንድን ነው ትርጉሙ? ካወገዙስ በኋላ ምንድን አንው የተከተለው? “ድርጅታችን የበለጠ ትግሉን ይቀጥላል!” ማለትስ ምንድን ነው ትርጉሙ? “ያንን እስኪያደርግ ድረስ የበለጠ አልተጋልንም!” የሚል ኑዛዜ ነው? “የታሰሩትን እንዲፈታ እንጠይቃለን!” ማለት ለፌዝ ነው? “ከሌሎች ጋር እንተባበራለን!” የሚል ማስፈራሪያ አስቀምጦ ድምፅን ማጥፋትስ ለምን አስፈለገ? በተለይ የመተባበርን ጉዳይ አስመልክቶ፤ “እተባበራለሁ!” ያላለ ድርጅት የለም። ትግሉ “ያለአንድነት የትም አይደርስም!” ያላለ ድርጅት የለም። አስፈላጊነቱን ያላሰመረ፣ የሕዝቡ ጥያቄ መሆኑን ያላስገነዘበና ጥሪውን በተደጋጋሚ ያላወጀ ድርጅት የለም። ታዲያ አሁን የት ላይ ቆመናል? መግለጫዎቹ አደረግሁ ለማለት ነበር የወጡት? ለመተባበር ጥሪ ያደረገ ድርጅት፤ ከወዲሁ አብሮ የመሥራትን አስፈላጊነት ማመን ብቻ ሳይሆን፤ ለማስተባበርም ኃላፊነቱን መውሰዱ ነው። ታዲያ ያንን ኃላፊነት ለመውሰድ የወሰነ ድርጅት፤ ሌሎች ለሚጠሩት ትብብር ለምን መልስ መሥጠት ገደደው? ምን መልስ ሠጠ? እኔ ለጠራሁት ሌሎች መልስ ይሥጡ እንጂ፤ ሌሎች ለጠሩት እኔ መልስ አልሠጥም ማለት ይሆን? አስመሳይነት ማለት ምን ማለት ነው? ዋሾነት በምን ይከሰታል? በዚህ ጉንጉን የተተበተበ ሂደት ምን ያህል ካለበት ፎቀቅ ማለ ይቻላል?

እዚህ ላይ ነው የኔ መግለጫ አለማውጣት ትርጉም የሚሠጠው። የምደግፈው ተግባራዊ ጉልበት በማልሠጥበት ሂደት፤ መግለጫ አላወጣም። በርግጥ አንዳንድ ያደረግኋቸውን ለማመላከት፤ የእስላሞችን እንቅስቃሴ አስመልክቶ በግፍ መሪዎቻቸው ሲታሰሩ እኛም ሰለምን፤ በማለት ከትቤያለሁ። አብረሃ ደስታ ሲታሰር አሻንጉሊቶች ናችሁ በማለት ከትቤያለሁ። ሌሎችንም በዚሁ ማስታወሻ መድረኬ ጠቃቅሻለሁ። ዋናው ቁም ነገር ግን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ብዬ ያሰቀመጥኩትን ቡድን፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ይሄን! ወይንም ያንን! ሠራ ብዬ መግለጫ በማውጣት ውግዘት አላሽጎደጉድም። ጠላት ከዚያ የተለዬ ምን ሊያደርግ ኖሯልና! ጠላቴ ብዬ ፈርጀዋለሁ እኮ! ይልቅስ ይሄንን ጠላት ብለን የፈረጅነውን አካል፤ በተግባር በመተባበር ለመጣል በአንድነት እንሰለፍ።

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

ማክሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን፣ ፳፻፰ ዓመተ ምህረት

eske.meche@yahoo.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule