• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች

March 22, 2016 01:24 am by Editor Leave a Comment

ገዢው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት በየዕለቱ በሚያደርገው ፀረ-ኢትዮጵያዊ ተግባር፤ የተለያዩ የፖለቲካ ሕዝባዊ ስብስቦች መግለጫ ያወጣሉ። አዳዲስና ነባር የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አለን በማለት ስማቸውን በአንባቢዎች ያስመዘግባሉ። ለመሆኑ ጋዜጣዊ መገለጫዎች ለምንድን ጉዳይ ነው የሚወጡት? ማነው የሚያወጣቸው? መግለጫዎችን ተከትሎ የሚተገበሩት ምንድን ናቸው? አሉስ ወይ? መግለጫ አውጪዎቹና መግለጫ ያላወጡ የፖለቲካ ሕዝባዊ አካሎች መለያቸው ምንድን ነው? መግለጫዎችና አውጪዎቻቸው፤ ሕዝባዊ ናቸው ወይንስ ጠባብ ወገንተኛ? መልዕክት አላቸው ወይንስ አደረግሁ ለማለት የተወረወሩ? አስፈላጊነታቸውስ ምን ያህል ነው? በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ በተንጎደጎዱ ወቅት የደረሱኝ እጦማሮች ነበሩ። ሁሉም ወቀሳዎች ናቸው። “ለምን መግለጫ አታወጣም?” “ካሁን በፊትም ዝም ብለሃል!” የሚሉና ሌሎችም ከጠላት ጋር ወግነሃል ያሉኝም ነበሩባቸው። ለምንድን ነው መግለጫ ማውጣት ያለብኝ? መግለጫ አላወጣም። ይሄን ግልጽ በሆነ መንገድ ማስቀመጥ አለብኝ።

መንግሥታትና ድርጅቶች መግለጫ ሲያወጡ፤ መሠረታዊ ዓላማው፤ ጉዳዩ ካተኮረባቸው አካላት ጋር ተባባሪ መሆናቸውን አንባቢ ወይንም አዳማጭ እንዲያውቅላቸው አይደለም። መግለጫውን የሚያወጡት፤ ነግ ለኔ ብለው፤ ካሁኑ ቀድሜ እርምጃ እወስዳለሁ ማለታቸው ነው። ከማንኛውም መግለጫ ጋር፤ አብሮ የሚሄድ መልዕክት አለ። “የሚያስፈልገውን ለማድረግ እንጥራለን!” “ከዛሬ ጀምሮ ይሄን ወይንም ያኛውን እናደርጋለን!” “በሚያስፈልገው ነገር ሁሉ ልንረዳችሁ ዝግጁ ነን!” “ሊረዷችሁ የሚችሉ ሰዎችን ልከንላችኋል!” “ለመቋቋሚያ እንዲያግዛችሁ ገንዘብ ልከንላችኋል!” እና የመሳሰሉት ናቸው። እንግዲህ ልብ ብለን ብናጤነው፤ ዋናው የመግለጫው ማሠሪያ፣ ይሄ ከወደኋላ የተከተለው ተግባር ነው። እስኪ ወደኛ፤ በተለይም የገዢውን ቡድን ተግባር የሚያወግዙትን ጋዜጣዊ መግለጫዎችና አውጪዎቻቸውን እንመለስ።

በጠላትን ፈርጀው የሚታጋሉትን ገዢ ቡድን፤ “ይሄን በማድረጉ አውግዘናል!” ማለት ምንድን ነው ትርጉሙ? ካወገዙስ በኋላ ምንድን አንው የተከተለው? “ድርጅታችን የበለጠ ትግሉን ይቀጥላል!” ማለትስ ምንድን ነው ትርጉሙ? “ያንን እስኪያደርግ ድረስ የበለጠ አልተጋልንም!” የሚል ኑዛዜ ነው? “የታሰሩትን እንዲፈታ እንጠይቃለን!” ማለት ለፌዝ ነው? “ከሌሎች ጋር እንተባበራለን!” የሚል ማስፈራሪያ አስቀምጦ ድምፅን ማጥፋትስ ለምን አስፈለገ? በተለይ የመተባበርን ጉዳይ አስመልክቶ፤ “እተባበራለሁ!” ያላለ ድርጅት የለም። ትግሉ “ያለአንድነት የትም አይደርስም!” ያላለ ድርጅት የለም። አስፈላጊነቱን ያላሰመረ፣ የሕዝቡ ጥያቄ መሆኑን ያላስገነዘበና ጥሪውን በተደጋጋሚ ያላወጀ ድርጅት የለም። ታዲያ አሁን የት ላይ ቆመናል? መግለጫዎቹ አደረግሁ ለማለት ነበር የወጡት? ለመተባበር ጥሪ ያደረገ ድርጅት፤ ከወዲሁ አብሮ የመሥራትን አስፈላጊነት ማመን ብቻ ሳይሆን፤ ለማስተባበርም ኃላፊነቱን መውሰዱ ነው። ታዲያ ያንን ኃላፊነት ለመውሰድ የወሰነ ድርጅት፤ ሌሎች ለሚጠሩት ትብብር ለምን መልስ መሥጠት ገደደው? ምን መልስ ሠጠ? እኔ ለጠራሁት ሌሎች መልስ ይሥጡ እንጂ፤ ሌሎች ለጠሩት እኔ መልስ አልሠጥም ማለት ይሆን? አስመሳይነት ማለት ምን ማለት ነው? ዋሾነት በምን ይከሰታል? በዚህ ጉንጉን የተተበተበ ሂደት ምን ያህል ካለበት ፎቀቅ ማለ ይቻላል?

እዚህ ላይ ነው የኔ መግለጫ አለማውጣት ትርጉም የሚሠጠው። የምደግፈው ተግባራዊ ጉልበት በማልሠጥበት ሂደት፤ መግለጫ አላወጣም። በርግጥ አንዳንድ ያደረግኋቸውን ለማመላከት፤ የእስላሞችን እንቅስቃሴ አስመልክቶ በግፍ መሪዎቻቸው ሲታሰሩ እኛም ሰለምን፤ በማለት ከትቤያለሁ። አብረሃ ደስታ ሲታሰር አሻንጉሊቶች ናችሁ በማለት ከትቤያለሁ። ሌሎችንም በዚሁ ማስታወሻ መድረኬ ጠቃቅሻለሁ። ዋናው ቁም ነገር ግን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ብዬ ያሰቀመጥኩትን ቡድን፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ይሄን! ወይንም ያንን! ሠራ ብዬ መግለጫ በማውጣት ውግዘት አላሽጎደጉድም። ጠላት ከዚያ የተለዬ ምን ሊያደርግ ኖሯልና! ጠላቴ ብዬ ፈርጀዋለሁ እኮ! ይልቅስ ይሄንን ጠላት ብለን የፈረጅነውን አካል፤ በተግባር በመተባበር ለመጣል በአንድነት እንሰለፍ።

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

ማክሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን፣ ፳፻፰ ዓመተ ምህረት

eske.meche@yahoo.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule