• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች

March 30, 2016 11:05 pm by Editor Leave a Comment

የኢህአዴግ የቁርጥ ቀን ልጅ ልደቱ አያሌውና ፓርቲው ኢዴፓ ባዲስ ትርፍ የፓርላማ መቀመጫ ፍለጋ ሰሞኑን ከእንቅልፋቸው መንቃታቸውን ሰምቼ ትንሽ ተገረምኩ። በውል ያልተደነቅሁበት ምክንያት ኢዴፓንና ሌሎች በኢህአዴግ-ወለድ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ም/ቤት ውስጥ የታጨቁ የስልጣን ተስፈኞች እንጂ ፖለቲካ የሚያውቁ ቁርጠኛ ተቃዋሚዎች ናቸው ብዬ ስለማላውቅ ነው። ደግነቱ ደግሞ ነገሩ እውነት መሆኑ ነው። እነዚህ ኢህአዴግ በልካቸው በሰራላቸው ጉረኖ ታሽገው በኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ስልጣን ለመቀላወጥ በተስፋ የሚያደቡት ኢዴፓና አጃቢዎቹ ሰሞኑን የኢህአዴግ ዙፋን ሲነቃነቅ በፈጠረው የፖለቲካ ስንጥቅ ለመሰካት በጠቅላይ ሚንስትሩ እግር ስር ወድቀው ትራፊ ወንበር እንዲረጥቧቸው ልመና መጀመራቸውን ሰምቼ አፈርኩባቸው።

የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደ አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም ለአሜሪካ ድምፅ ያማርኛው አገልግሎት በሰጡት ቃለምምልስ ተቃዋሚዎች በፓርላማ የውክልና ወንበር እንዲኖራቸው ለማድረግ ተስፋ እንደተሰጣቸው ያለሀፍረት ሲናገሩ ተደምጠዋል። እስቲ ማን ይሙት በዚህ ወቅት፣ ከአንድ የተቃዋሚ ፓርቲ የሚጠበቅ ይህ ነበር? ፊደል ያልቆጠረው ምስኪኑ የኢትዮጵያ ገበሬ ለዴሞክራሲና ፍትህ የድሃ ደሙን እያፈሰሰ ባለበት በዚህ ወሳን ወቅት የኛ ዶክተር ፖለቲከኞች ሊሞት በሚያጣጥር አምባገነን እግር ስር ወድቀው የፓርላማ ወንበር ይለምናሉ። መጥኔ አቦ! እንዴት ያለ ህሊና ቢኖራቸው ነው ጃል? በህዝብ ደም አሮጌ የስልጣን ወንበር መመኘት።

ክቡር የሆነውን የወገን ደም ማርከስ አይሆንም? እንደወጉ ቁርጠኛ ተቃዋሚ መሆን ባይሳካላቸውና ተፈጥሯቸው ባይፈቅድላቸው እንኳን ገላጋይ ሽማግሌ ለመሆን ቢጥሩ ምን ነበረበት? ህዝብ ለፍትህ ሲጮኽ ብትት እንኳን ሳይሉ የወንበር እርጥባን ሹክሹክታ እንዴት በአንድ ጊዜ አባነናቸው? ጉድ ነውመቼም!

ለነገሩ ይህ ፓርቲና አጋሮቹ ምን ጊዜም ኢህአዴግ ጭንቅ በገጠመው ጊዜ ሁሉ ደራሽና የቁርጥ ቀን አገልጋዮች በመሆናቸው ታሪካቸውን ለሚያውቅ ድርጊታቸው የሚያስገርመው አይሆንም። የቅንጅት ዘመን ሚናቸውን ያስታውሷል። ያኔም ቢሆን ሀገር የከዱት በስልጣን ጥምና ስግብግብ ፍላጎታቸው ነበር። ዛሬም ያው ልማደኛ የስልጣን አራራቸው ተነሳና የህዝብ አስከሬን ላይ ቆመው ስልጣን ይለምኑ ጀመር። አቤት ክፉ ቀን ስንት ክፉ ነገር ያሳያል? ይህን ከመሰሉ አርተፊሻል ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ በስንት ጣዕሙ ጃል!

ዛሬ ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታ ልዩ መፍትሄ የሚሻ ነው። አሁን ስልጣንና ወንበር በስሌት የምንከፋፈልበት ጊዜ አይደለም። አሁን ይህች ውብ ሀገር ከገጠማት የታሪክ ፈተና ለማውጣት ሁላችንም (ምናልባትኢህአዴግን ጨምሮ) ሌት ተቀን የምንጨነቅበት ወቅት ነው። ዛሬ ነባር የግልና የቡድን ጥቅማችንን እያሰላን ሆዳችን የሚጮኽበት ጊዜ ሳይሆን በምጥ ላይ የምተገኘውን ሀገራችንን ካንቺ በፊት ያርገኝ የምንልበት ፈታኝ ወቅት ነው። እናም ኢደዓዊያን፣ እባካችሁ ህሊና ግዙ። ይሉኝታም ያስፈልጋል። ሀገር ሰላም ከሆነ ሌት ተቀን የሚያቃዣችሁ የስልጣን ሱስ የሚረካበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል። ሀገር ከወደቀች ግን ከነቅዠታችሁ ትቀበራላችሁና አስቡበት። ቢቻል የህዝብን ጩኸት ችላ ብላችሁ በጓሮ በር ስልጣን ለመቀላወጥ ያደረጋችሁት ሙከራ አሳፋሪ ነውና በይፋ ይቅርታ ጠይቁ። ይህ ጨዋነት የማይሆንላችሁ ከሆነ ደግሞ ለገዛ እናታችሁ ቀብር መቆፈር የጀመራችሁትን ቁፋሮ አቁሙ። ኢህአዴግም ይታዘባችኋል። ይህ ካልሆነ ዛሬ ለኢትዮጵያ በቆፈራችሁት ጉድጓድ እናንተው ትገቡበታላችሁ። በጭንቅ ቀን ሀገሩን የከዳ ዋጋው ከዚህ ያነሰ ሊሆን አይችልም። ልቦና ይስጣችሁ! አሜን።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule