• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች

March 30, 2016 11:05 pm by Editor Leave a Comment

የኢህአዴግ የቁርጥ ቀን ልጅ ልደቱ አያሌውና ፓርቲው ኢዴፓ ባዲስ ትርፍ የፓርላማ መቀመጫ ፍለጋ ሰሞኑን ከእንቅልፋቸው መንቃታቸውን ሰምቼ ትንሽ ተገረምኩ። በውል ያልተደነቅሁበት ምክንያት ኢዴፓንና ሌሎች በኢህአዴግ-ወለድ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ም/ቤት ውስጥ የታጨቁ የስልጣን ተስፈኞች እንጂ ፖለቲካ የሚያውቁ ቁርጠኛ ተቃዋሚዎች ናቸው ብዬ ስለማላውቅ ነው። ደግነቱ ደግሞ ነገሩ እውነት መሆኑ ነው። እነዚህ ኢህአዴግ በልካቸው በሰራላቸው ጉረኖ ታሽገው በኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ስልጣን ለመቀላወጥ በተስፋ የሚያደቡት ኢዴፓና አጃቢዎቹ ሰሞኑን የኢህአዴግ ዙፋን ሲነቃነቅ በፈጠረው የፖለቲካ ስንጥቅ ለመሰካት በጠቅላይ ሚንስትሩ እግር ስር ወድቀው ትራፊ ወንበር እንዲረጥቧቸው ልመና መጀመራቸውን ሰምቼ አፈርኩባቸው።

የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደ አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም ለአሜሪካ ድምፅ ያማርኛው አገልግሎት በሰጡት ቃለምምልስ ተቃዋሚዎች በፓርላማ የውክልና ወንበር እንዲኖራቸው ለማድረግ ተስፋ እንደተሰጣቸው ያለሀፍረት ሲናገሩ ተደምጠዋል። እስቲ ማን ይሙት በዚህ ወቅት፣ ከአንድ የተቃዋሚ ፓርቲ የሚጠበቅ ይህ ነበር? ፊደል ያልቆጠረው ምስኪኑ የኢትዮጵያ ገበሬ ለዴሞክራሲና ፍትህ የድሃ ደሙን እያፈሰሰ ባለበት በዚህ ወሳን ወቅት የኛ ዶክተር ፖለቲከኞች ሊሞት በሚያጣጥር አምባገነን እግር ስር ወድቀው የፓርላማ ወንበር ይለምናሉ። መጥኔ አቦ! እንዴት ያለ ህሊና ቢኖራቸው ነው ጃል? በህዝብ ደም አሮጌ የስልጣን ወንበር መመኘት።

ክቡር የሆነውን የወገን ደም ማርከስ አይሆንም? እንደወጉ ቁርጠኛ ተቃዋሚ መሆን ባይሳካላቸውና ተፈጥሯቸው ባይፈቅድላቸው እንኳን ገላጋይ ሽማግሌ ለመሆን ቢጥሩ ምን ነበረበት? ህዝብ ለፍትህ ሲጮኽ ብትት እንኳን ሳይሉ የወንበር እርጥባን ሹክሹክታ እንዴት በአንድ ጊዜ አባነናቸው? ጉድ ነውመቼም!

ለነገሩ ይህ ፓርቲና አጋሮቹ ምን ጊዜም ኢህአዴግ ጭንቅ በገጠመው ጊዜ ሁሉ ደራሽና የቁርጥ ቀን አገልጋዮች በመሆናቸው ታሪካቸውን ለሚያውቅ ድርጊታቸው የሚያስገርመው አይሆንም። የቅንጅት ዘመን ሚናቸውን ያስታውሷል። ያኔም ቢሆን ሀገር የከዱት በስልጣን ጥምና ስግብግብ ፍላጎታቸው ነበር። ዛሬም ያው ልማደኛ የስልጣን አራራቸው ተነሳና የህዝብ አስከሬን ላይ ቆመው ስልጣን ይለምኑ ጀመር። አቤት ክፉ ቀን ስንት ክፉ ነገር ያሳያል? ይህን ከመሰሉ አርተፊሻል ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ በስንት ጣዕሙ ጃል!

ዛሬ ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታ ልዩ መፍትሄ የሚሻ ነው። አሁን ስልጣንና ወንበር በስሌት የምንከፋፈልበት ጊዜ አይደለም። አሁን ይህች ውብ ሀገር ከገጠማት የታሪክ ፈተና ለማውጣት ሁላችንም (ምናልባትኢህአዴግን ጨምሮ) ሌት ተቀን የምንጨነቅበት ወቅት ነው። ዛሬ ነባር የግልና የቡድን ጥቅማችንን እያሰላን ሆዳችን የሚጮኽበት ጊዜ ሳይሆን በምጥ ላይ የምተገኘውን ሀገራችንን ካንቺ በፊት ያርገኝ የምንልበት ፈታኝ ወቅት ነው። እናም ኢደዓዊያን፣ እባካችሁ ህሊና ግዙ። ይሉኝታም ያስፈልጋል። ሀገር ሰላም ከሆነ ሌት ተቀን የሚያቃዣችሁ የስልጣን ሱስ የሚረካበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል። ሀገር ከወደቀች ግን ከነቅዠታችሁ ትቀበራላችሁና አስቡበት። ቢቻል የህዝብን ጩኸት ችላ ብላችሁ በጓሮ በር ስልጣን ለመቀላወጥ ያደረጋችሁት ሙከራ አሳፋሪ ነውና በይፋ ይቅርታ ጠይቁ። ይህ ጨዋነት የማይሆንላችሁ ከሆነ ደግሞ ለገዛ እናታችሁ ቀብር መቆፈር የጀመራችሁትን ቁፋሮ አቁሙ። ኢህአዴግም ይታዘባችኋል። ይህ ካልሆነ ዛሬ ለኢትዮጵያ በቆፈራችሁት ጉድጓድ እናንተው ትገቡበታላችሁ። በጭንቅ ቀን ሀገሩን የከዳ ዋጋው ከዚህ ያነሰ ሊሆን አይችልም። ልቦና ይስጣችሁ! አሜን።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule