• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአዲስ አበባውና የአሜሪካው ኢህአዴግ ቢሮ አይተዋወቁም

March 21, 2016 07:02 am by Editor 2 Comments

በሳምንቱ አጋማሽ የተሰማውን ዜና ያደመጡ፣ ከቅርብ ሆነው የሚከታተሉና ለጉዳዩ የቀረቡ እንደሚሉት የአዲስ አበባው ኢህአዴግና አሜሪካ ያለው የኢህአዴግ ቢሮ የማይተዋወቁበት ደረጃ ደርሰዋል። ኢህአዴግ በደብዳቤ የተረከባቸውን ስደተኞች በብሔር መትሮ “ኢትዮጵያዊ አይደላችሁም” በሚል ወደ አሜሪካ መመለሱ የእለት ጉርስና የዘመን መሻገሪያ ድርጎ የምትመድበውን አሜሪካንን አስቆጥቶ እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።

ኢህአዴግ እንደ “አሸባሪ” የፊጥኝ አስሮ ከፍሎሪዳ ጠቅላይ ግዛት ማያሚ እስር ቤት ወደ ኢትዮጵያ የወሰዳቸው ወገኖች ከአገራቸው የወጡበትን ጊዜ ሳይቆጥር አሜሪካ ለመድረስ ብቻ እስከ አስራ አራት ወራት ፈጅቶባቸዋል። ስደተኞቹ በብራዚል፣ በኮሎምቢያ ጫካ ፣ በፓናማ ወንዝ አሳብረው፣ በሜክሲኮና በድምሩ 16 የሚደርሱ አገራትን አልፈው ነበር አሜሪካ ጥገኝነት የጠየቁት። እነዚህ ወገኖች ህጉ ከሚፈቅደው ውጪ ከስድስት ወር በላይ በፍሎሪዳ ጠቅላይ ግዛት ማያሚ እስር ቤት መቆየታቸውን ጎልጉል መዘገቡ ይታወቃል። በአስራ አንደኛው ሰዓት ለአቶ ኦባንግ ሜቶ የላኩት “የድረሱልን” ደብዳቤ ነገሩን ሁሉ ይፋ አደረገው።

በዚህ መካከል ነበር አቶ ግርማ ብሩ የሚመሩት የህወሃት የአሜሪካ ቢሮ ስደተኞቹን “ዜጎቼ ናቸው” ብሎ ጠርቶ ሲያበቃ፣ ስም ዘርዝሮ፣ ቢመለሱ ምንም አይሆኑም፣ ምንም አይደርስባቸውም፣ ሰላማዊ ኑሮ መኖር ይችላሉ፣ ወዘተ በማለት ደብዳቤና አዘጋጅቶ በሰጠው የመጓጓዣ ሰነድ አማካይነት ወጣቶቹ ተላልፈው ተሰጥተውታል።

ጎልጉል ከተመላሾች ባገኘው መረጃ መሰረት፣ የአሜሪካ ልዩ የፖሊስ አባላት ማያሚ እስር ቤት ሌሊት መጡ፤ ተነሱ አሏቸው፤ እጃቸውን አሰሩ፤ በመኪና ተጫኑ። አቅራቢያ ባለ አየር ማረፊያ በተዘጋጀ አነስተኛ የግል አውሮፕላን ተጫኑ። ከአስራ አንድ ሰዓት በላይ በረራ ካደረጉ በኋላ ሴኔጋል ዳካር አረፉ። አውሮፕላንዋ ነዳጅ ስትሞላ እነሱም ውሃና የሚቀመስ አግኝተው ባሉበት ቆዩ። ከዚያም ወደ “አገራቸው” ኢትዮጵያ አቀኑ። አዲስ አበባ ሲደርሱ የህወሃት ነፍጥ አንጋቾች ተረከቧቸው። ጉዞው በህወሃት አሸናፊነት ተጠናቀቀ። ለጉዞው አሜሪካኖቹ ከፍተኛ ወጪ አውጥተዋል።

ርክክቡ ከተጠናቀቀ በኋላ ሁሉም በየተራ ቃለመጠይቅ ተደረገላቸው። መከረኛው የብሔር ጥያቄ ቀረበ። ጠያቂዎቹ የህወሃት ሰዎች የብሄር ጥያቄውን ተከትሎ ወጣቶቹን እንደ እህል በዘር መደቧቸው። እናትና አባታቸው የኢትዮጵያ ሶማሌና አማራ፣ ሃረሪና ኦሮሞ የሆኑት ሁለቱ፣ እንዲሁም ሁለት የጅጅጋ ነዋሪዎችና የኢትዮጵያ ሶማሌ ተወላጆች እና ሙሉ በሙሉ የሃረሪ ተወላጅ እንደሆነ የተናገረውን ጨምሮ አምስቱ ተመርጠው “አማርኛ በደንብ ትችላላችሁ ግን ኢትዮጵያዊ አይደላችሁም” ተብለው ወደ አሜሪካ እንደተመለሱ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባው አሜሪካ ኤምባሲ ከከፍተኛ የህወሃት መሪዎች ጋር ዘለግ ያለ ንትርክ አካሂደዋል። ራሱ “ዜጎቼ” ብሎ ደብዳቤ በመጻፍ ተላልፈው እንዲሰጡት ጠይቆ ሲያበቃ፣ ራሱ የጉዞ ሰነድ አዘጋጅቶ፣ ራሱ እስር ቤት ድረስ ሄዶ እጅና እግር አስሮ፣ ራሱ ነፍጥ አንጋች አሰልፎ አቀባበል አድርጎ፣ ከአንድ የትግራይ ልጅ በስተቀር ሁሉንም በአማርኛ አነጋግሮ በስተመጨረሻ አምስቱን “ኢትዮጵያውያን አይደላችሁም” ብሎ ወደ አሜሪካ እንዲመለሱ ማድረጉ “አውራ ፓርቲ” የሚባለውን ኢህአዴግን ቅሌት ውስጥ እንደጣለው ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ አመልክተዋል።

“አሜሪካ ያለው ኢህአዴግና አዲስ አበባ ያለው ኢህአዴግ የማይተዋውቁበት ደርጃ ደርሰዋል” ሲሉ አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል የአሜሪካ ዘጋቢ ገልጸዋል። አክለውም “ይህ የሚያሳየው ድርጅቱ በተግባር መዋቀሩ የተሽመደመደ፣ ማዕከላዊነት የሚባል ነገር መጥፋቱን፣ ሁሉም በየፊናው ሩጫ መጀመሩን፣ እንደ አገር የክስረት ማመላከቻ ነው” ሲሉ በተፈጸመው ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።deportee letter

ከተመለሱት መካከል ያነጋገሯቸው እንዳሉ ያስታወቁት ኦባንግ፤ ካሁን በኋላ ልጆቹ እስር ቤት የሚቆዩበት አንዳችም ምክንያት ባለመኖሩ እንደሚፈቱ ጠቁመዋል።

“ኑሮዬ ሳይስተካከል የት እንዳለሁ እንኳን ለቤተሰቦቼ አልገለጽኩም። እናትና አባቴ ልሙት፣ ልኑር አያውቁም፤ ከተለየኋቸው ጊዜ ጀምሮ ስልክ ሳልደውል አራት አመት ከአስራ አንድ ወራት አልፈውኛል” በሚል የድረሱልኝ ጥያቄ ጨምሮ ዘጠኙን ወገኖች ለማስፈታት አቶ ኦባንግ ባለቀ ሰዓት መረጃው ደርሷቸው የሚቻላቸውን ሁሉ ጥረው ነበር። “የድረሱልን ጥሪውን እንደተቀበልኩ ወዲያውኑ ስደተኞቹን የሚወክል ጠበቃ ያዝኩ። የወጣቶቹ ከስድስት ወር በላይ መታሰር ከህግ አንጻር አግባብ ባለመሆኑና ስደተኞቹ ሊመለሱ እንደማይገባ ለማውቃቸው እንደራሴዎችና ሴናተሮች በማስረዳት የእስር ውሳኔ ላስተላለፉት ዳኛ ደብዳቤ ሊላክ የሰዓታት ዕድሜ ሲቀር ነበር የመላካቸውን ጉዳይ የሰማሁት” በሚል ነበር ሃዘናቸውን የገለጹት።

ቀደም ሲል በአስራ አንደኛው ሰዓት ጉዳዩን የያዘው ጠበቃ የልጆቹን መመለስ ሲሰማ መገረሙን፤ ሌሎችም አካላት በተመሳሳይ በሰሙት ሁኔታ በኢትዮጵያ በመንግሥት ደረጃ ያለው ሥርዓት አልበኝነት ያስደነገጣቸው መሆኑን ያመለከቱት ኦባንግ፣ ጉዳዩ ህጉ በሚያዝው መሰረት እንደሚከናወን አመልክተዋል። በርግጠኛነት ልጆቹ በቅርቡ እንደሚፈቱም አክለዋል። በሌላ መልኩ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በሚገኙ እስር ቤቶች ተመሳሳይ የድረሱልኝ ጥሪ ያሰሙ ወገኖች መኖራቸውንና እነዚህን ወገኖች ለመርዳት በሳቸው በኩል የሚደረገውን ሁሉ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሊቢያ ዜጎች ስልክ ሲደውሉ ጆሮዋቸው ላይ በመዝጋት፣ ስልክ እንዳይደውሉ በመከልከል፣ በተለያዩ አረብ አገራት እህቶቻችን ላይ ሰቃይ ሲደርስና ሲገደሉ፣ በደቡብ አፍሪቃ በዜጎች ላይ ተመሳሳይ አደጋ ሲደርስ ህወሃት ያሳየውን ቸልተኛነት ያስታወሱት ኦባንግ “ብሔርን፣ ዘርን፣ ወገንን፣ … ለይቶ የሚፈጸሙ ጥፋቶች ፈር እየለቀቁ የማንመልሰው ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ለናርቃቸው ይገባል” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። ዜጎች ከዘር ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ በመስጠት እርስ በርስ መደጋገፍ ላይ እንዲያተኩሩም አሳስበዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. moon says

    March 23, 2016 08:18 am at 8:18 am

    What do you really need .
    If accepted , you say they were sent to woyane
    If deported , you say they are denied access to ETHIOPIA . Confused guys !

    Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 10:41 pm at 10:41 pm

    Enem ende h/aram 1 ayin mehone inji ethiopiawi negni.A A YALEW “WEYANE “SIHON U S A YALEW KETARIK ANITSAR TINISH MORAL YELELEW BANDA YE ETHIOPIA EMBASSY NEW. 100% ethiopian yemiwekilu embasiwoch bemulu 666 nachew.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule