• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአዲስ አበባውና የአሜሪካው ኢህአዴግ ቢሮ አይተዋወቁም

March 21, 2016 07:02 am by Editor 2 Comments

በሳምንቱ አጋማሽ የተሰማውን ዜና ያደመጡ፣ ከቅርብ ሆነው የሚከታተሉና ለጉዳዩ የቀረቡ እንደሚሉት የአዲስ አበባው ኢህአዴግና አሜሪካ ያለው የኢህአዴግ ቢሮ የማይተዋወቁበት ደረጃ ደርሰዋል። ኢህአዴግ በደብዳቤ የተረከባቸውን ስደተኞች በብሔር መትሮ “ኢትዮጵያዊ አይደላችሁም” በሚል ወደ አሜሪካ መመለሱ የእለት ጉርስና የዘመን መሻገሪያ ድርጎ የምትመድበውን አሜሪካንን አስቆጥቶ እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።

ኢህአዴግ እንደ “አሸባሪ” የፊጥኝ አስሮ ከፍሎሪዳ ጠቅላይ ግዛት ማያሚ እስር ቤት ወደ ኢትዮጵያ የወሰዳቸው ወገኖች ከአገራቸው የወጡበትን ጊዜ ሳይቆጥር አሜሪካ ለመድረስ ብቻ እስከ አስራ አራት ወራት ፈጅቶባቸዋል። ስደተኞቹ በብራዚል፣ በኮሎምቢያ ጫካ ፣ በፓናማ ወንዝ አሳብረው፣ በሜክሲኮና በድምሩ 16 የሚደርሱ አገራትን አልፈው ነበር አሜሪካ ጥገኝነት የጠየቁት። እነዚህ ወገኖች ህጉ ከሚፈቅደው ውጪ ከስድስት ወር በላይ በፍሎሪዳ ጠቅላይ ግዛት ማያሚ እስር ቤት መቆየታቸውን ጎልጉል መዘገቡ ይታወቃል። በአስራ አንደኛው ሰዓት ለአቶ ኦባንግ ሜቶ የላኩት “የድረሱልን” ደብዳቤ ነገሩን ሁሉ ይፋ አደረገው።

በዚህ መካከል ነበር አቶ ግርማ ብሩ የሚመሩት የህወሃት የአሜሪካ ቢሮ ስደተኞቹን “ዜጎቼ ናቸው” ብሎ ጠርቶ ሲያበቃ፣ ስም ዘርዝሮ፣ ቢመለሱ ምንም አይሆኑም፣ ምንም አይደርስባቸውም፣ ሰላማዊ ኑሮ መኖር ይችላሉ፣ ወዘተ በማለት ደብዳቤና አዘጋጅቶ በሰጠው የመጓጓዣ ሰነድ አማካይነት ወጣቶቹ ተላልፈው ተሰጥተውታል።

ጎልጉል ከተመላሾች ባገኘው መረጃ መሰረት፣ የአሜሪካ ልዩ የፖሊስ አባላት ማያሚ እስር ቤት ሌሊት መጡ፤ ተነሱ አሏቸው፤ እጃቸውን አሰሩ፤ በመኪና ተጫኑ። አቅራቢያ ባለ አየር ማረፊያ በተዘጋጀ አነስተኛ የግል አውሮፕላን ተጫኑ። ከአስራ አንድ ሰዓት በላይ በረራ ካደረጉ በኋላ ሴኔጋል ዳካር አረፉ። አውሮፕላንዋ ነዳጅ ስትሞላ እነሱም ውሃና የሚቀመስ አግኝተው ባሉበት ቆዩ። ከዚያም ወደ “አገራቸው” ኢትዮጵያ አቀኑ። አዲስ አበባ ሲደርሱ የህወሃት ነፍጥ አንጋቾች ተረከቧቸው። ጉዞው በህወሃት አሸናፊነት ተጠናቀቀ። ለጉዞው አሜሪካኖቹ ከፍተኛ ወጪ አውጥተዋል።

ርክክቡ ከተጠናቀቀ በኋላ ሁሉም በየተራ ቃለመጠይቅ ተደረገላቸው። መከረኛው የብሔር ጥያቄ ቀረበ። ጠያቂዎቹ የህወሃት ሰዎች የብሄር ጥያቄውን ተከትሎ ወጣቶቹን እንደ እህል በዘር መደቧቸው። እናትና አባታቸው የኢትዮጵያ ሶማሌና አማራ፣ ሃረሪና ኦሮሞ የሆኑት ሁለቱ፣ እንዲሁም ሁለት የጅጅጋ ነዋሪዎችና የኢትዮጵያ ሶማሌ ተወላጆች እና ሙሉ በሙሉ የሃረሪ ተወላጅ እንደሆነ የተናገረውን ጨምሮ አምስቱ ተመርጠው “አማርኛ በደንብ ትችላላችሁ ግን ኢትዮጵያዊ አይደላችሁም” ተብለው ወደ አሜሪካ እንደተመለሱ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባው አሜሪካ ኤምባሲ ከከፍተኛ የህወሃት መሪዎች ጋር ዘለግ ያለ ንትርክ አካሂደዋል። ራሱ “ዜጎቼ” ብሎ ደብዳቤ በመጻፍ ተላልፈው እንዲሰጡት ጠይቆ ሲያበቃ፣ ራሱ የጉዞ ሰነድ አዘጋጅቶ፣ ራሱ እስር ቤት ድረስ ሄዶ እጅና እግር አስሮ፣ ራሱ ነፍጥ አንጋች አሰልፎ አቀባበል አድርጎ፣ ከአንድ የትግራይ ልጅ በስተቀር ሁሉንም በአማርኛ አነጋግሮ በስተመጨረሻ አምስቱን “ኢትዮጵያውያን አይደላችሁም” ብሎ ወደ አሜሪካ እንዲመለሱ ማድረጉ “አውራ ፓርቲ” የሚባለውን ኢህአዴግን ቅሌት ውስጥ እንደጣለው ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ አመልክተዋል።

“አሜሪካ ያለው ኢህአዴግና አዲስ አበባ ያለው ኢህአዴግ የማይተዋውቁበት ደርጃ ደርሰዋል” ሲሉ አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል የአሜሪካ ዘጋቢ ገልጸዋል። አክለውም “ይህ የሚያሳየው ድርጅቱ በተግባር መዋቀሩ የተሽመደመደ፣ ማዕከላዊነት የሚባል ነገር መጥፋቱን፣ ሁሉም በየፊናው ሩጫ መጀመሩን፣ እንደ አገር የክስረት ማመላከቻ ነው” ሲሉ በተፈጸመው ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።deportee letter

ከተመለሱት መካከል ያነጋገሯቸው እንዳሉ ያስታወቁት ኦባንግ፤ ካሁን በኋላ ልጆቹ እስር ቤት የሚቆዩበት አንዳችም ምክንያት ባለመኖሩ እንደሚፈቱ ጠቁመዋል።

“ኑሮዬ ሳይስተካከል የት እንዳለሁ እንኳን ለቤተሰቦቼ አልገለጽኩም። እናትና አባቴ ልሙት፣ ልኑር አያውቁም፤ ከተለየኋቸው ጊዜ ጀምሮ ስልክ ሳልደውል አራት አመት ከአስራ አንድ ወራት አልፈውኛል” በሚል የድረሱልኝ ጥያቄ ጨምሮ ዘጠኙን ወገኖች ለማስፈታት አቶ ኦባንግ ባለቀ ሰዓት መረጃው ደርሷቸው የሚቻላቸውን ሁሉ ጥረው ነበር። “የድረሱልን ጥሪውን እንደተቀበልኩ ወዲያውኑ ስደተኞቹን የሚወክል ጠበቃ ያዝኩ። የወጣቶቹ ከስድስት ወር በላይ መታሰር ከህግ አንጻር አግባብ ባለመሆኑና ስደተኞቹ ሊመለሱ እንደማይገባ ለማውቃቸው እንደራሴዎችና ሴናተሮች በማስረዳት የእስር ውሳኔ ላስተላለፉት ዳኛ ደብዳቤ ሊላክ የሰዓታት ዕድሜ ሲቀር ነበር የመላካቸውን ጉዳይ የሰማሁት” በሚል ነበር ሃዘናቸውን የገለጹት።

ቀደም ሲል በአስራ አንደኛው ሰዓት ጉዳዩን የያዘው ጠበቃ የልጆቹን መመለስ ሲሰማ መገረሙን፤ ሌሎችም አካላት በተመሳሳይ በሰሙት ሁኔታ በኢትዮጵያ በመንግሥት ደረጃ ያለው ሥርዓት አልበኝነት ያስደነገጣቸው መሆኑን ያመለከቱት ኦባንግ፣ ጉዳዩ ህጉ በሚያዝው መሰረት እንደሚከናወን አመልክተዋል። በርግጠኛነት ልጆቹ በቅርቡ እንደሚፈቱም አክለዋል። በሌላ መልኩ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በሚገኙ እስር ቤቶች ተመሳሳይ የድረሱልኝ ጥሪ ያሰሙ ወገኖች መኖራቸውንና እነዚህን ወገኖች ለመርዳት በሳቸው በኩል የሚደረገውን ሁሉ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሊቢያ ዜጎች ስልክ ሲደውሉ ጆሮዋቸው ላይ በመዝጋት፣ ስልክ እንዳይደውሉ በመከልከል፣ በተለያዩ አረብ አገራት እህቶቻችን ላይ ሰቃይ ሲደርስና ሲገደሉ፣ በደቡብ አፍሪቃ በዜጎች ላይ ተመሳሳይ አደጋ ሲደርስ ህወሃት ያሳየውን ቸልተኛነት ያስታወሱት ኦባንግ “ብሔርን፣ ዘርን፣ ወገንን፣ … ለይቶ የሚፈጸሙ ጥፋቶች ፈር እየለቀቁ የማንመልሰው ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ለናርቃቸው ይገባል” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። ዜጎች ከዘር ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ በመስጠት እርስ በርስ መደጋገፍ ላይ እንዲያተኩሩም አሳስበዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. moon says

    March 23, 2016 08:18 am at 8:18 am

    What do you really need .
    If accepted , you say they were sent to woyane
    If deported , you say they are denied access to ETHIOPIA . Confused guys !

    Reply
  2. Yikir says

    March 29, 2016 10:41 pm at 10:41 pm

    Enem ende h/aram 1 ayin mehone inji ethiopiawi negni.A A YALEW “WEYANE “SIHON U S A YALEW KETARIK ANITSAR TINISH MORAL YELELEW BANDA YE ETHIOPIA EMBASSY NEW. 100% ethiopian yemiwekilu embasiwoch bemulu 666 nachew.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule