• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት ራሱን በራሱ ሸንጎ አስገምግሞ የእጁን ደም ሊያጸዳ ነው

March 28, 2016 01:44 am by Editor 3 Comments

ህወሃት በኦሮሚያና በአማራ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸመውን ወንጀልና ርህራሄ አልባ ግፍ ራሱ አጣርቶ፣ ራሱ አጠናክሮ፣ ራሱ በፈጠረው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አማካይነት አቅርቦ፣ በራሱ ሸንጎ በማጸደቅ እጁን ከደም ሊያጸዳ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ይፋ መሆኑንን ተከትሎ ለሪፖርቱ ማዳመቂያ የምስል ቪዲዮዎች መዘጋጀታቸው ታወቀ።

በኦሮሞና በአማራ ህዝብ ላይ የተወሰደውንና እየተወሰደ ያለውን የኃይል ርምጃ አስመልከቶ ድራማ እየተሰራ ነው ሲል የጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ሪፖርተር የኢህአዴግ ጽ/ቤት ምንጮቹን ጠቅሶ ነው ስለ ሁኔታው የዘገበው። ህወሃት በአዋጅ ያቋቋመው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መሪ ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር ቀደም ሲል በጉዳዩ ዙሪያ ሪፖርት ያቀረቡትን የመብት ተሟጋች ድርጅቶች እንደማይታመኑ ተናግረዋል።

በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር መመሪያ ሰጪነት ህወሃት በኦሮሚያና በአማራ ክልል ሰላማዊ ጥያቄ ባነሱ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ላይ ሲያከናውን የቆየውንና አሁንም እየተካሄደ ያለውን ገደብ የለሽ ግፍ፣ የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ግድያ፣ እስር፣ አካላዊ ስቃይ፣ ማሳደድና አፈና  አስመልክቶ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆነውን ሂውማን ራይትስ ዎችን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማትና መንግሥታት አውግዘውታል። አሁንም እያወገዙት ነው።

ህወሃት ለአገዛዙ ይጠቅመው ዘንድ በየደረጃው ካቋቋማቸው ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መሪ አዲሱ ገብረእግዚአብሔር ባለፈው ሰኞ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በመግለጫቸው “ስለሰብዓዊ መብት ጥሰት ስናውራ ጥሰቱን ማን ፈጠረው” ተብሎ መሬት ተወርዶ ምርመራ መካሄድ እንደሚገባው አስገንዝበዋል። አያይዘውም በስም ባይጠሩትም ሂውማን ራይትስ ዎችን “የት ሆነው ሪፖርቱን እንደሚሰሩት ባናውቅም…” ሲሉ ህወሃትን ጥፋተኛ በማድረግ ድርጅቱ ያወጣውን ሪፖርት ሊታመን የማይችል ሲሉ ከወዲሁ ተችተዋል።

የቀድሞው የምርጫ ቦርድ ምክትል ኃላፊ የሚመሩትና “ሃቀኛ ሪፖርት ያቀረባል” የተባለው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በጥቂት ቀናት ውስጥ ይፋ የሚያደርገው ሪፖርት ኢህአዴግ ጽ/ቤት እንደተጠናቀረ የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ አመልክቷል። እንደ ዘጋቢው፣ ሪፖርቱ ከክልል የደኅንነትና ጸጥታ መዋቀሮች የተሰበሰቡትን መረጃዎች በኮሚሽኑ ስም የሚያዘጋጀው የኢህአዴግ ጽ/ቤት፣ በኦሮሚያ የኦህዴድ ሃላፊዎች ላይ የተወሰደውን ርምጃ ያጎላል። ከህዝብ ጋር በተደረጉ “ውይይቶች” በሚል የተወሰደው የኃይል ርምጃ ከተቀሰቀሰው ረብሻ ጋር ሲነጻጸር እንደማይጋነን ህዝብ ምስክርነት እንደሰጠበትና ፈጣን ምላሽ የተወሰደበትን ጉዳይ ከጀርባ የውጪ ኃይሎች ወደ ረብሻ እንደቀየሩት አድርጎ ያሳያል።

ከዚህም በላይ የእስልምና አክራሪዎች እጅ ከጀርባ እንዳለበት በማጉላት ህወሃት የወሰደው ርምጃ “እጅግ ትዕግስት የተሞላበትና የተመጣጠነ” እንደሆነ በሪፖርቱ ይንጸባረቃል። በተጨማሪም ለማረጋጋት ተሰማራ በተባለው ሰራዊት ላይ፣ ባካባቢ ሚሊሺያዎች፣ ፖሊሶችና የሌላ ብሄር አባላት ላይ የግድያ ሙከራ መደረጉንና ቤተክርስቲያን መቃጠሉን ሪፖርቱ ህወሃት ለተጨማለቀበት ደም ማጽጃ በረኪና አድርጎ እንደሚያቀርብ ተመልክቷል።

ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም “ጥፋተኞች ነን፤ ህዝብን ይቅርታ እንጠይቃለን” ማለታቸውን ተከትሎ ይፋ የሚሆነው ሪፖርት፣ ህወሃት በውክልና አገሪቱን እንዲያስተዳድሩለት የመደባቸውን ካድሬዎች ማገዱ፣ ማባረሩ፣ በህግ ለመጠየቅ መዘጋጀቱ ከወንጀሉ በስተጀርባ ሆነው ትዕዛዝ ሲሰጡ የነበሩትን የህወሃት ሹማምንቶች ነጻ እንደሚያወጣ ኦህዴድን አጋፍጦ እንደሚሰጠው ለማወቅ ተችሏል። በዚህም የፌደራል አስተዳደሩ ጣልቃ ገብቶ የማስተካከሎ ስራ መስራቱ በበጎ ጎኑ የሚቀርብ እንደሆነ ከወዲሁ ታውቋል።

አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ መንግሥታት ኢህአዴግን ለወጉም ቢሆን ማብራሪያ እየጠየቁ መሆኑ፣ እንደ ሂውማን ራይትስ ዎች አይነት የሰብዓዊ መብት ተቋማት ያቀረቧቸውን ሪፖርቶች ለማጣጣል፣ ሪፖርቱ ከታሰበው ጊዜ በፊት ተጠናቅሮ እንዲወጣ ታምኖበታል። ከዚያም “በኢህአዴግ ሸንጎ ክርክር ተደርጎበት፣ ዳብሮና ተሻሽሎ ጸደቀ” ይባላል። የፖለቲካ ጨዋታ መሆኑ ቢታወቅም ለውጪው ዓለም ሚዛን ማሳቻ ይውል ዘንድ ህጋዊ ሽፋን ይሰጠዋል። ከዚያም ለፕሮፖጋንዳው ክፍሎች ተበተኖ ሥራ ላይ እንደሚውል ዘጋቢያችን አመልክቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት (ሒውማን ራይትስ ዎች) ዘገባውን ካወጣ በኋላ ለአሜሪካ መንግሥት ኃላፊዎች በዝግ ተጨማሪ ማብራሪ የተሰጣቸው መሆኑን ጎልጉል የደረሰው መረጃ ይጠቁማል። በዘገባው ላይ ያልተጠቀሱ ተጨማሪ መረጃዎችና ማብራሪያዎች ለኃላፊዎቹ የተሰጣቸው በመሆኑ ባለፉት ቀናት የሕዝብ እንደራሴዎች በተለይ የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱን (ስቴት ዲፓርትመትን) ለኮንግረስ ዘገባ እንዲያቀርብ መጠየቃቸው ተዛማጅነት እንዳለው ይነገራል።

አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ሪፖርቱ በሚወጣበት ቀንም ሆነ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በሁለቱም ክልሎችና በኮንሶ፣ እንዲሁም በጋምቤላ የደረሰውን ግፍና ወንጀል በማጠናከር ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ሚዲያዎች፣ ለኤምባሲዎች፣ ለተለያዩ አገራትና በተለይም ለህዝብ በሚቻለው መንገድ ሁሉ ይፋ ማድረግ አግባብ ነው። በተለይም አስቀድሞ ለውጭ ሚዲያዎች መግለጫ በመስጠት ሪፖርቱን ራሱ ህወሃት ያዘጋጀው እንደሆነ ማስታወቅ አግባብ እንደሆነ ተገልጾዋል። ቢቻል ሪፖርቱ እየቀረበ ባለበት ወቅት የህወሃት አንጋቾችና ታማኞች እስካሀን ድረስ ያለማቋረጥ የፈጸሙትን አሰቃቂ ግፍ በማህበራዊ ገጾች ላይ አጉልቶ ማሳየት እንደሚገባ ጠቁመዋል። ባገር ቤት ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሪፖርቱን አስመልክተው ይፋ ከመሆኑ በፊት ከወዲሁ ስራ መስራት እንደሚገባቸው ይመክራሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    March 28, 2016 05:18 pm at 5:18 pm

    ወንድሜ አዲሱ ገ/እግዚአብሔር!!!

    እስከ አሁን ድረስ በመንፈሳዊ ህይዎትዎ ጥንካሬ በርካታ ምስክሮች አሉኝ፤ የእግዚአሔር ልጆች በእግዚአብሔር መንፈስ ይመራሉ በሌላ በምንም አይመራም።
    ዳንኤል በቤተ መንግሥት አምላኩን አስከበረው! ሙሴ የፈሮን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ! አስቴር ማን ያውቃል? ወደ ቤተ መንግሥት የመጣሽው ለዚህ እንደሆነ ማን ያውቃል?

    ወንድማዊ የሆነው ምክሬ በሚያልፍ ክብር በእጅዎ ያለውን የማያልፈውን የዘላለም እንቁ እንዳይጥሉና የሚወዱት የእግዚአብሔር ስም እንዳይሰደብ ይጠንቀቁ??? እኔም ጌታ በረዳኝ መጠን በጸሎት አስብዎታለሁና ይበርቱ እውነቱን በፍቅና በጥንቃቄ ለሕዝብ/ለአገር ጥቅም ያውጡት???

    እግዚአብሔር ሞገስ ይጨምርልዎት
    እውነቱ

    ከቻሉ በ eunethiwot@gmail.com ያግኙኝ

    Reply
  2. gud says

    March 28, 2016 08:10 pm at 8:10 pm

    To green eyed persons

    We have millions of projects on the pipe line .
    We learn from failures and march on .

    Reply
  3. Yikir says

    March 29, 2016 09:07 pm at 9:07 pm

    Kediowinu yehaset zegebawin mawitat yichil neber.Neger gin yemigedilew,akal ye agodilew,setochin keye universitiw be awirew agazi eskemiyasdefirachew ….bemetages new. Be ethiopia lijoch dem yeteshimonemonu gazetegnoch aluh 100 gize bilefelifu man yisemal .ASEB WEDEBIN ASIREKIBEH SITABEKA “ETHIOPIAN YEDEREK WEDEB BALEBET ADEREGINAT “BILEHI yemitawera awire ,shifta,zerafi ,kehadi,ariwos mehonihin manim yawikal.ATO H/MARIAM BEMAYAYEW AYINE BEKUL YALEWIN NEGER ALASTEWALKUM ENDATIL waaaaaaa;)!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule