የለንደኑ ጸረ-ሕዝብ አመጸኛ፣ አንድ እርምጃ ሲወስዱ፣ ሕዝቡ ሁለት እርምጃ ቀድሞአቸው ይጠብቃቸዋል። ሲበዛ ተንኰለኛ በመሆናቸው፣ አንድ ቀን ተሳስተውም ደግ ነገር ሠርተው ቢገኙ፣ የሚያምናቸው ሰው አይኖርም። በዓይነ ቁራኛ ነው እንቅስቃሴአቸውን የምንቆጣጠረው። በዕውነት ተጸጽተው እንኳን ቢያለቅሱ፣ የአዞ ዕምባ ብሎ ነው ሰው የሚሸሻቸው። አሁንም ተነቃቅተናል። አባ ተባዩ አስመሳይ መነኵሴ፣ የሚጠቅማቸው መስሎአቸው፣ ለወየኔ የመሽሎኪያ ቀዳዳ አበጀተውለት አስጠቁን። “የአስተዳደር መዋቅሩ አይሻሻልም፣ እኔም ከሥልጣኔ አልወርድም” - እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ሁኖባቸው ለወያኔ ወደው ገብተው እኛን በሶልዲ ሸጡን። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) (Click here to read the report and video by the local Guardian) … [Read more...] about እባብ ለእባብ፣ ይተያያል በካብ
Opinions
የኔ ሃሳብ
ስንቱን አጣን!
እንደኢትዮጵያ ባለ ኋላቀር አገር አገር ውስጥ መሠልጠን ብዙ ችግር አለበት፤ እኔ ራሴ በኮምፒዩተር መጻፍ ከጀመርሁ ሠላሳ ዓመት ሊሆነኝ ነው፤ ታዲያ መብራት ጠፋና የምሠራው ባጣ የቆዩ ወረቀቶችን ሳገላብጥ አንድ እአአ በዲሴምበር 26 1965 ከዱሮ ተማሪዬ የተጻፈልኝን ደብዳቤ አገኘሁ፤ በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በነበረ ከአንድ በጣም ጎበዝ ወጣት የተላከልኝ ነበረ፤ ከተመረቀ በኋላ በአንድ ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ ለጥቂት ዓመታት ሠርቶ ትምህርቱን ለመቀጠል ወደአሜሪካ ሄዶ በሎዝ አንጄለስ አካባቢ ከሚገኝ ትምህርት ቤት ገብቶ ነበር፤ ደብዳቤውን የጻፈልኝ ከዚያ ነው፤ ደብዳቤው ሰባት ገጾች አሉት፤ ከሰባቱ ገጾች አምስቱ ስለኢትዮጵያ ያለውን ስጋት የሚገልጽ ነው፤ በሎዝ አንጀለስ አካባቢ ካሉ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት በሚያደርግበት ጊዜ ሁሉ ብዙዎቹ የሚያሳዩት የመንደረኛነት ስሜት እያበሳጨው የተማሩት … [Read more...] about ስንቱን አጣን!
ፓለቲካዊ መግባባት እና 18 የፓልቶክ ታዳሚዎች
ይህ ጥያቄ እና መልስ ከ18 የፓልቶክ ታዳሚዎች ጋር ስለ ፓለቲካዊ መግባባት ("ብሄራዊ መግባባት") የተደረገ ነው። ጥያቄ እና መልስ የተደረገበት ጊዜ ከSeptember 16-20, 2013 ሲሆን ፡ ጠያቂ አቶ ያዬ አበበ ነው (Paltalk nick name: Beruhan)። የዚህ ጥያቄ እና መልስ አላማ የፓልቶክ ታዳሚዎች ስለ ፓለቲካዊ መግባበት ያለቸውን ግንዛቤ ለማሰስ ሲሆን ፡ በተጨማሪ የአሰሳውን ውጤት በመጠቀም ስለ ፓለቲካዊ መግባባት በዲያስፓራ መወያያ መድረኮችና ሚዲያዎች ግንዛቤ የሚያስጨብጥና ጥልቀት ያለው የፓለቲካ ውይይት የሚፈጥር ጥንስስ ለመጀመር ነው። ((ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)) … [Read more...] about ፓለቲካዊ መግባባት እና 18 የፓልቶክ ታዳሚዎች
አባ አጋግዮስ
ባለፈው ሳምንት የዘንድሮውን የደመራ በዓል አከባበር በዜና ማሰራጫዎች የተመለከቱ ግሪካዊ ቄስ ባነሱት ጥያቄ የተቀሰቀሰብኝን ስሜት፤ ለዚህች ክታብ መግቢያ ላደርገው ፈለኩ። “ባገርህ የተደረገውን የመስቀሉን በዓል በመገናኛ ዘዴወች አይቼው በጣም ደስ ይላል። ሄደህ ነበር? ብለው ጠየቁኝ። “አልሄድኩም” አልኳቸው። “ለምን አልሄድክም? ብለው መልሰው ጠየቁኝ። ያሰለቼኝ ጥያቄ ስለሆነ የጥያቄቸውን መስመር በመቀየር “እርስዎን ምኑ ነው ያስደሰተዎ? ብየ ጠየኴቸው። “አከባበሩ ደስ ይላል” አሉኝ። “የእርሰዎ መንፈስ የተማረከው ባከባበሩ መብልጭልጭ ነው። የኔን መንፈስ የሚማርከው ደግሞ በበዓሉ የሚወሱት እነ ቆስጠንጢኖስ፤ ዲዮቅልጥያኖስ፤ እነ ቅድስት እሌኒና የአባ አጋግዮስ አስከፊ ባህርይ ነው። ከዚህም ጋር ደመራ የሚለው የበዓሉ መጠሪያ እንደሚያመለክተው፤ ከልጅነት ጀምሮ ለበዓሉ የክብር መርገፎች … [Read more...] about አባ አጋግዮስ
መንገድ ወድቆ አየሁት
ርሃብ፣ ድካም እና ሰቆቃው ለላፉት 12 ወራት ተፈራርቀውበታል። አንዴ በሰሃራ በረሃ ሌላ ግዜ ደግሞ በሜዲትራንያን ባህር የሰው አእምሮ ሊቀበለው የማይችል ስቃይ አልፎ እግሩ አውሮፓን ምድር ከረገጠ እነሆ አንድ ሌሊት አለፈ። ሰነድ ገብረጻድቅ ይባላል። ፊቱ እጅግ ተጎሳቅሏል። ከሰውነቱ ላይ አጥንቶቹ ይቆጠራሉ። ወጣቱ ተስፋ ወዳደረገባት የአውሮፓ ምድር ለመግባት የተነሳው ከአመት በፊት ነው። እንብርቱ የተቀበረችበትን ሃገር ተሰናብቶ ከወጣ ጀምሮ የደረሰበት መከራ ይህ ነው አይባልም። ሰነድን እመንገድ ወድቆ ነበር ያገኘሁት። ለጥቂት ደቂቃ አነጋገርኩት። ንግግሩ የሚረብሽ ነው። አጭር የቪዲዮ ቆይታችንን ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ። ከ 300 በላይ የኢትዮጵያውያ እና የኤርትራ ተወላጆች የፈጀው የላምፔዱሳ እልቂት በአለም አቀፍ ዜና እየታወጀ ባለበት ሰዓት፤ ሌላ መርከብ ከሊቢያ ተነስታ … [Read more...] about መንገድ ወድቆ አየሁት
የምርትና የሕዝብ እድገት እሽቅድድም
እአአ በ1798 (ከሁለት መቶ አሥራ አምስት ዓመታት በፊት) መምሬ ቶማስ ሮበርት ማልቱስ የሚባል የ32 ዓመት የብሪታንያ ቄስ የዘመኑን የነገረ ንዋይ አስተሳሰብ የለወጠ አዲስ ሀሳብን የያዘ መጽሐፍ አሳተመ፤ ሀሳቡ በጣም ግልጽ ነበረ፤ የሰው ልጆች ቁጥር እድገት መጠኑ እያጠፈ የሚሄድ ነው፤ የሕዝብ ቁጥር 1፣ 2፣ 4፣ 8፣ 16፣ 32፣ 64፣ 128፣ እያለ የሚጨምር ነው፤ ከእርሻ የሚገኘው ምርት ደግሞ የእድገቱ መጠን አያጥፍም፤ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8፣ 9፣ 10፣ እያለ የሚሄድ ነው፤ የመምሬ ማልቱስን ሀሳብ በሌላ መንገድ ካየነው የበላተኞች ቁጥር እያጠፈ ሲያድግ የምግቡ አቅርቦት የሚያድገው ግን በጣም በዝግተኛ ፍጥነት ነው፤ የሚል ነው፤ እንግዲህ የሕዝብ ቁጥርና የምርት አቅርቦት እኩል መጓዝ ሲገባቸው የሕዝቡ ቁጥር እየቀደመ ስለሚገኝ፣ መምሬ ማልቱስ የደረሰበት … [Read more...] about የምርትና የሕዝብ እድገት እሽቅድድም
መሬት የማን ነው?
አገር ማለት በአባቶች፣ በአያቶችና በቅድማያቶች አጥንትና ደም ተገንብቶ የታጠረ መሬት ነው፤ የዶር. በድሉ ዋቅጅራን ዋይታ እየኮረኮረ የሚያወጣውና የሚያስተጋባው የፍቅር ስሜት ምንጭ ነው። የተከሰከሰውና ተፈረካክሶ አፈር የሆነው አጥንትና የወረደው የአያቶችና የቅድማያቶች ደም እየፈሰሰ መሬቱ ላይ በሚገኙ ወንዞች ውስጥ ሁሉ ገብቶአል፤ እንዲያውም እነዚህ ወንዞች ወስደው በቀይ ባሕር፣ በሜዲቴራንያን ባሕርና በሕንድ ውቅያኖስ ጨምረውታል፤ ይህ በአጥንትና በደም የታጠረ መሬት የማን ነው? በመሬቱ ላይ የባለቤትነት መብትን ለማስከበር ከውጭ ኃይሎች ጋር የተጋደሉት ጥንታውያን ነፍጠኞች ቅድሚያን የሚያገኙ ይመስለኛል፤ እነዚህ ጥንታውያን ነፍጠኞች ብቻቸውን አልነበሩም፤ ለምግብ የሚሆናቸውን ሁሉ የሚያመርቱ ገበሬዎች ነበሩ፤ ለልብስ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ የሚፈትሉና የሚሸምኑ ባለሙያዎች ነበሩ፤ … [Read more...] about መሬት የማን ነው?
“ያላወቂ ሳሚ … ይለቀልቃል”
የጎልጉል ጥብቅ ማሳሰቢያ! ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ዋናው ዓላማ የሕዝብ እንደመሆኑ በጨዋነት የሚላኩልንን ጽሁፎች የምናትም መሆናችንን ስንገልጽ ቆይተናል፡፡ ሆኖ ግን አልፎ አልፎ የሚላኩልን ጽሁፎች በግለሰብ ዙሪያ ያጠነጠኑ ከመሆናቸው ባሻገር ምንም እንኳን ጸያፍ ቃላትን በግልጽ የሚታይባቸው ባይሆንም የሚሰነዘሩት ሃሳቦች ግን የግለሰቦችን ሰብዕና የሚነካ ከመሆኑ ባሻገር በስራችን ላይ ከፍተኛ ውስብስብ ነገር የሚፈጥርና ወደ አልተፈለገ እንካሰላንቲያ የሚመራ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ በመሆኑም በእንደዚህና መሰል ጽሁፎች ላይ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለየት ያለ የኤዲቶሪያ ፖሊሲ በመጠቀም ጽሁፎችን እንደሁኔታው እያየን የምናትም መሆናችንን እንገልጻለን፡፡ በተለይ ከዚህ በታች በተጠቀሰው አስተያየት ዙሪያ የሚላክልንን ማንኛውንም ጽሁፍ የማንቀበል መሆናችንን እንገልጻለን፡፡ በጉዳዩ ለመነጋገር … [Read more...] about “ያላወቂ ሳሚ … ይለቀልቃል”
የልማት መጀመሪያው ሰብዓዊ መብትን ማክበር ነው!
የመግለጫውን ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ:: … [Read more...] about የልማት መጀመሪያው ሰብዓዊ መብትን ማክበር ነው!
A Journalist kidnapped, Threatened, and Beaten by Intelligence and Security Agents in Ethiopia
The Ethiopian journalist Bisrat Woldemichael was kidnapped, threatened, humiliated, and beaten by the Ethiopian intelligence and security agents on 28 August, 2013. He has reported this incident today to journalists. Bisrat reported that the dreadful incident took place at Gotera, a place in the capital Addis Ababa as he was walking home from work. He said he was victimized for exercising his right to free expression in conjunction with the related right to press freedom. Bisrat Woldemichael … [Read more...] about A Journalist kidnapped, Threatened, and Beaten by Intelligence and Security Agents in Ethiopia









