ፍትህ ሳያደርቀው የፈሰሰን ፍዳ፣ ንስሀ ሳያጥበው የቆሸሸን ጓዳ፣ ዱለትን መቋደስ ከገዳዮች ጋራ፣ የሐጥያትም ሐጥያት የታሪክም ዕዳ! ፍትህ ነፃነትን መብትን ተርበው፣ ኢፍታዊነትን እንደ አውሬ ተናንቀው፣ ስንቶቹ ተሰው ባሩድ ተመግበው? ነፃነት ወይም ሞት በቃ ዘራፍ ብለው፣ ስንቶች ተሰውልን ጫካ ዱር ሸፍተው? በእሬቻ በጥምቀት በመስጊድ ሰገዳው፣ በሰፈር መንደሩ በገጠር ከተማው፣ እንደ ፋሲካ በግ የታረደ ስንት ነው? ባዶ ስድስት ጉድጓድ በጪስ የታፈነው፣ ቃሊቲ ዓለም በቃኝ የተዘቀዘቀው፣ ቅሊንጦና ዝዋይ በእሳት የነደደው፣ ሽሮሜዳ ታስሮ ጥፍሩ የወለቀው፣ ብር ሸለቆ አዘዞ ጉረኖ የገባው፣ ማሰቃያ ቦታው ጭራሽ ያልታወቀው፣ ስንት መከረኛ ምን ያህል ዜጋ ነው? የጋንቤላን ምድር ሽፍን ያደረገው፣ ኦጋዴን በርሃን በጎርፍ የጠረገው፣ ምን ያህል ሬሳ … [Read more...] about ምነው ደም ደም አይለን?
Literature
ጽፈኪን
ቋንቋን በቋንቋ
ስለ ቋንቋ የተለያዩ እይታዎች መኖራቸው አዲስ አይደለም። የሚገርመው ይልቅ፣ ብዙዎች እንደ ሹምና አቡን ትእዛዝ ሲሰጣጡ ማየት ነው። ትእዛዙን ማን፣ እንዴት ይፈጽም? እይታዎችን ማቀራረብና መተግበርስ ይቻላል? መቸ በምን ቅደም ተከተል? ወዘተ። ይህን ያሰቡበት ቢኖሩ ድምጻቸው አልተሰማም። የራስን አጉልቶ፣ የሌላኛውን ማድበስበስ የተለመደ በመሆኑ፣ የጽሑፌ ይዘት ለያንዳንዱ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፣ የተዘነጉ ጥቃቅን አሳቦችን ማነጋገር ይሆናል። ቋንቋ ቢያንስ ሀ/ ድንበር ተሻጋሪ መሆን ይኖርበታል፤ አማርኛ ተናጋሪ፣ እርስ በርሱ ብቻ ከሆነ፣ ከኬላው ውጭ በምን ይግባባል? ለ/ ድንበር ተሻግረን እንግሊዝኛ፣ አማርኛ፣ ወዘተ፣ የቆነጠርን ቢያንስ አኗኗራችንን ለማሻሻል እንደ ሆነ አንርሳ ሐ/ ቋንቋ ተሻጋሪ እንዲሆን፣ ድልድይ የሚሆን ቋንቋ ይሻል። አማርኛ ድልድይ ነው። እርግጥ፣ ሁሉን ቋንቋ ማወቅ … [Read more...] about ቋንቋን በቋንቋ
እኛም እንዳንሰቅለው!
እንደምን? ይመጣል! ከናዝሬት ላይ ነብይ፣ ልክ እንደተባለው ከወያኔም ዓብይ፣ ተገኝቶ ከመጣ - ጌታ ከመረጠው፣ ፈራሁኝ እንደሱ እኛም እንዳንሰቅለው! (ወለላዬ ከስዊድን) … [Read more...] about እኛም እንዳንሰቅለው!
ስማኝ ሰማእቱ!
ከባርነት ሞትን የመረጥከው ወንዱ፣ አፉን ክፍት አርጎ የዋጠህ መቃብሩ፣ የማዋይህ አለኝ ስማኝ ሰማእቱ፡፡ የፈሰሰው ደምህ በህልሜ እየታየኝ፣ አጥንትህ ከመቃብር እየጎራበጠኝ፣ እሾህ ቀጋ ሆኖ አላስተኛህ አለኝ፡፡ ለፍትህ ስትጮህ የቀረኸው ባጭር፣ ጎንደር ደብረታቦር ወልድያ ባህርዳር፣ ቡሬና ዳንግላ ማጀቴና አቸፈር፣ ዛሬም ወንድሞችህ ታስረዋል ግዮን ዳር፡፡ በስናይፐር የፈጁህ ህሊና ቢሶቹ፣ ለውጥ አመጣን ብለው ያንኑ ደገሙ፣ አንድ አስገዳይ ነቅለው ሌላውን ተከሉ፡፡ አጥንትህን ከአምቦ ከእሬቻ ለቃቅሞ፣ መሰላል አረገው ከለማ ጋር ሰርቶ፡፡ በስንት በጎች ደም እንደተነከረ፣ እጁን ሳይታጠብ አቢይ ቀደሰ፡፡ ኢያሱና ሙሴን ተከተሉ እያሉ፣ ስንቱን ዘልዛላ እንከፍ ከጀርባ አሰለፉ፡፡ ተመራጩ አስገዳይ መራጩም ገዳይ ነው፣ የሌላው ማሽቃበጥ ምን … [Read more...] about ስማኝ ሰማእቱ!
ዓመፀኛ ዋሻ
መነሻ፤ ወርሃ የካቲት ለነፃነትና ለባንዲራ ከወራሪዎች ጋር ተናንቀው ኢትዮጵያን በነፃነት ያቆምዋትን ሠማዕታት አብናቶቻችንን (አባት እናቶቻችንን) የምንዘክርበትና ስለባንዲራና ስለኢትዮጵያ ቃል ኪዳናችንንም የምናድስበት ወር ነው። እነሆ ደግሞ በዚህ ዘመን ኢትዮጵያን ካነቀው ሀገር በቀል ዘረኛ ወራሪ የህወሃት አገዛዝ ነፃነቷንና ክብሯን ለመመለስ በሚደረገው የህልውና ትንቅንቅ በህወሃት ወህኒ ቤቶች ወደር አልባ ናዚስታዊ ግፍና ሰቆቃ የተፈፀመባቸውን የነፃነት ታጋዮች ለማስፈታት ይህ ወጣት ትውልድ /ቄሮ ወፋኖ/ ባልተቋረጠው ሠላማዊ ትግል በትንግርተኛው ወርሃ የካቲት እንደ አብናቶቹ ታሪክ ሰርቷል፤ ህወሃትን በግማሽ አንበርክኮ ናሙናውን ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝንም አሰናብቷል። እነሆም ናዚስት ህወሃት በህዝባዊ እምቢተኝነት ማንቁርቱን ታንቆ ያለ ውዴታው ተገዶ በየወህኒው የዘጋባቸው … [Read more...] about ዓመፀኛ ዋሻ
እስክንድር ነጋ “ሃሳብን የመግለጽ መብት” ሽልማት
በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ዘ ሄግ ከተማ ትናንት ምሽት በተካሄደው የ2018 የፔን እና የኦክስፋም ኖቪፕ - "ሃሳብን የመግለጽ መብት" አዋርድ ተሸላሚ ሆኗል። ሽልማቱን ያዘጋጁት ኦክስፋም ኖቪፕ እና ፔን ኢንተርናሽናል የተሰኙ አለማቀፍ ተቋማት ሲሆኑ ከእስክንድር ነጋ ጋር የአመቱ ተሸላሚ ሆና የተመረጠችው የቬኒዙዌላዋ ጋዜጠኛ ሚላግሮ ሶካሮም ልብ የሚነካ ንግግር አድርጋለች። እስክንድር ነጋ በስፍራው ተገኝቶ ሽልማቱን መቀበል ባይችልም ከእስር ቤት ሆኖ የላከው I SHALL PERSEVERE (እኔ እጸናለሁ) የሚለው መልእክቱ በምሽቱ ዝግጅት ላይ ተነብቧል። በጃዝ ሙዚቃ እና በግጥም የታጀበው ይህ የስነጽሁፍ እና የሽልማት ዝግጅት እጅግ ደማቅ ነበር። ሄግ ትያትር በተዘጋጀው በዚህ አለም ዓቀፍ የስነ ጽሁፍ ምሽት መክፈቻ ላይ የከተማዋ ከንቲባ - የኦክስፋም … [Read more...] about እስክንድር ነጋ “ሃሳብን የመግለጽ መብት” ሽልማት
“መንግሥት ሲኖረኝ ቀስቅሱኝ”
በዚህች ምድር ላይ የቆየው ለ40 ዓመታት ብቻ ነው፤ ከ1970 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 2010 ዓ/ም። ተስፋዋና ፍሬዋ ለልጆቿ እንደ መንግሥተ ሠማያት መንፈስ ብቻ በሆነው ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ከተማ በመከረኛዋና ታሪካዊዋ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ - ጨርቆስ - ተወልዶ አደገ። ብሩህ አእምሮን የተቸረ በዕውቀት ቀሳሚነቱ የናረና ከሁሉም በላይ ግን ሀገራዊና ወገናዊ ሰብዕናን ከስነ ምግባር ጋር ያዋሃደ የኢትዮጵያ ልጅ ኢትዮጵያዊ ሆነ። ስለ ሀገሩና ስለህዝቧም ሲል በናዚስት የዘረኝነት አስተምህሮ ካበዱት ከግፍ ጠማቂዎቹ ናዚስት ወያኔ ገዢዎች የሀገሩን የፍዳ ገፈት ተግቶና ከሀገሩ ተገፍቶ በሰው ሀገር በስደት ተንከራትቶ አለፈ። እሱም ጋዜጠኛና የሰብዐዊ መብት ተሟጋቹ ኢብራሂም ሻፊ ይባላል። ግፈኞቹና በግፍ ዘመነ ሥራ ዕድሜ የጠገቡት ሀገሩን ኢትዮጵያን ሲቆጣጠሩ በ1983 ዓ/ም እሱ ገና አስራዎቹን … [Read more...] about “መንግሥት ሲኖረኝ ቀስቅሱኝ”
ዳግም ተገናኘን!
... “ያሰብኩት ተሳካ ያለምኩት ደረሰ፣ ሃሳቤም ተሟላ መንፈሴም ታደሰ፤...” ለዛሬዋ ጽሁፌ መግቢያነት የመረጥኳት ግጥም፣ በእውቁ ድምጻዊ በጥላሁን ገሠሠ ከተቀነቀኑት አያሌ የማኅበራዊ ዘርፍ ዘፈኖች አንዱ የሆነው ዘፈን አዝማች ናት(በሃሳባችሁ ዜማውን እያስታወሳችሁ ተከተሉኝ፤ በተለይ ከአጃቢ የሙዚቃ መሳሪያዎች መካከል ጎልታ የምትሰማዋን፣ የአየለ ማሞን የማንዶሊን ዜማ እያዳመጣችሁ)። ... ከዛሬ አንድ ዓመት በፊት “አማኒ ኢብራሂም — ’ያልታወቀው‘የጥበብ ሰው” በሚል ርዕስ አንድ መጣጥፍ ቢጤ በኢትዮጵያውያኑ ድረ-ገጾች (በኢትዮ-ሚድያ፣ በኢኤምኤፍ፣ በቋጠሮ፣ በጎልጉል...) ላይ ለንባብ አብቅቼ ነበር። ጽሑፉ እንደወጣ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ፣ ከሰላሣ ዓመታት በላይ የትና እንዴት እንዳለ ያላወኩትን፣ በሙዚቃ ሙያ በእጅጉ የተካነውን፣ ሁሌም ብዙዎች በአርዓያነት የሚጠቅሱትንና … [Read more...] about ዳግም ተገናኘን!
“ያን እኔን አፋልጉኝ!”
የዘመኑን ፈሊጥ የመኖርን ምስጢር ሳስተውለው ውዬ ቆሜ ስመረምር ጥበቡ ገብቷቸው መሄጃውን አውቀው መላ የጨበጡት ስሌት አስተካክለው ከተጠቀሙበት ኃያል ብልሃቶች አንዱ ማስመሰል ነው ለመኖር ከሰዎች እንደውም አንዳንዱ ከማስመሰል አልፎ በረቀቀ ጥበብ በተንኮል ቆልፎ ለተዘጋጀበት ላሰበበት ዕቅድ ማሰለፍ ይችላል በግድና በውድ እንዲሁም ሌላውን አድርጎ መሰላል ሁሉንም አሟልቶ እላይ በመንጠልጠል ሲፈልግ አጣልቶ፤ ሲሻው በማስታረቅ ሌላን እየጎዳ ጥቅሙን በማስጠበቅ በተገኘው መላ ባዘጋጀው መንገድ መረቡን ዘርግቶ ገንዘብ ለማሳደድ ምንም ጊዜ - የትም እሱን አስበልጦ አምሮ ተሽቀርቅሮ በአልባሳት አጊጦ ድሮውንም ያለው የቱጃር ቤተሰብ ገና በልጅነት ያየ ብዙ ገንዘብ ሃይማኖት አክባሪ ጿሚ ጸሎተኛ እጁ እማይታጠፍ ካየ ችግረኛ መምሰሉ አስገርሞኝ በማውቀው … [Read more...] about “ያን እኔን አፋልጉኝ!”
ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]
የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]፤ 2009ዓ.ም፤ አ/አ፤ አታሚ አልተገለጸም፤ 10ዶላር፣ 100 ገጽ የማለዳ ድባብ፣ ለ በዕውቀቱ ሥዩም አራተኛ የግጥም ሥራው ነው። መጽሐፉ ሦስት ክፍሎች አሉት፤ “ግጥምና የዘመን መንፈስ” [ገጽ 5-9]። ግጥሞች [ገጽ 17-91]። “ጉደኛ ስንኞች” እና “ሙሾና ባለቅኔ” [ገጽ 93-100]። መድብሉ፣ ቀድሞ ካስነበባቸው ላይ አዳዲሶች ተጨምረውበት የተዘጋጀ ነው [ገጽ 9]። የትኞቹ አዳዲሶች እንደሆኑ አልተገለጸም። ግጥም ከስድ ንባብ ይልቅ የግል እይታዎችን፣ ማህበራዊ ትረካዎችን ለመቋጠርና ለማስታወስ ይረዳል። ቅኝቱና አወራረዱ ለጆሮና ለዐይን ይጥማል። ግጥም ማህበራዊ እሴት አለው፤ በሥልጣን ለሚባልጉ እርምት ለመስጠት [“ይድረስ ለጥም ሚኒስትር”፣ ቁ.71]፣ የሕይወትን አጭርነት ለማሳሰብ፣ ከሚታየው ውጭ የላቀ ተስፋ እንዳለ ለማወጅ፣ የግለሰብ … [Read more...] about ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]