የታጨደው ሳር ድርቆሽ ነው የከብቶች መኖ በመሆን በበሬ ጫንቃ ድካም ጠግቦ አደር ያደረገን፤ የሞተው የግጦሽ ሳር ነው ጮሌ ፈረስ አሳድጎ በጦር ሜዳ የድል ብሥራት ያቀዳጀን ጀግና ተዋጊ አድርጎ፤ የበሬውን ቆዳ ከበሮ የበሬውን አንጀት ጅማት የፈረሱን ሞት በደል የሸንበቆውን ያካል ስብራት፤ የእንስሳቱን ሞት ከእሳሩ ሞት ጋር ስናዋድደው ከሞት ምንጭ ነው ለካስ የደስታ ጅረት የሚወርደው። የሞተ … [Read more...] about ሞት የሰጠን ደስታ
Literature
ጽፈኪን
ጣምራ ቁስል
ደራሲ፤ ተስፋዬ መኮንን ባይለየኝ (ዶ/ር) ቅኝት፤ መስፍን ማሞ ተሰማ ቀዳሚ፤ እነሆ ከጣምራ ቁስል በፊት “ቀይ አንበሳ” ነበረ። እነሆም ስለ ‘ቀይ አንበሳ’ ‘በማንኪያ’ እናቀምሳለን። እንዲህ ብለን፤ አልኻንድሮ ዴል ባዬ ኩባዊ ነው። ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት ለንደን፤ እንግሊዝ ውስጥ ነበር። በወቅቱ በእንግሊዝ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ሀኪም ወርቅነህ ማርቲን (ደብሊው ማርቲን) በጋዜጣ ላይ ባወጡት ማስታወቂያ አነሳሽነት አምባሳደሩ ፊት በመቅረብ ለአትዮጵያ በፈቃደኝነት ለመዋጋት የሚፈልግ መሆኑን ይገልፃል። አምባሳደር ወርቅነህም ጠየቁት፤ “ከእኛ በኩል ሆነህ ለመታገል ስትል ነው ከአገርህ ድረስ የመጣኸው?” “አይደለም። ከስፔን ገና መምጣቴ ነው። ወደ ኩባ ለመመለስ ነበር እቅዱ። ለውጪ አገር መኮንኖች በአቢሲኒያ ላይ የተቃጣውን ወረራ ለመዋጋት የቀረበውን ጥሪ … [Read more...] about ጣምራ ቁስል
አታስብ ይሉኛል!
ማሰብ ማሰላል - ማጤን ማውጣት ማውረድ፤ ባ'ይምሮ መፀነስ - ሃሳብን ማዋለድድ፤ ከምናብ ጓዳ ውስጥ - ምስጢርን ፈልፍሎ፤ ያይምሮ መረዋን - ማንኳኳት ደውል :: መላ ማፈላለግ - እንዲህ ቢሆን? ማለት ፤ አይምሮን ኮትኩቶ - ዕውቀት ዘርቶ ማምረት፤ ባ'ንዱ ውስጥ ሌላው_ በሌላው ውስጥ አንዱ_ እንዳለ መረዳት:: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) አሥራደው (ከፈረንሳይ) … [Read more...] about አታስብ ይሉኛል!
ፎቶግራፍ እና አጼ ምኒልክ
ከውጪ ሀገር የመጡ ሰዎች ለአፄ ምኒልክ ስለ ፎቶግራፍ እንዲህ ብለው አስረዷቸው "በአውሮጳ አንድ ትንሽ ሳጥን አለች ሰውን፣ ፈረሱን፣ ቤተመንግስቱን ሁሉ ወደ ሳጥኗ ታስገባና ሁሉን ትንሽ አርጋ ታሳያለች" አሏቸው። ምኒልክም በሰሙት ነገር ተገርመው እንዴት ይሆናል ይሄን ነገር ማየት አለብኝ ብለው የፎቶ ማንሻ እንዲመጣ አዘዙ። የፎቶ ማንሻውም (ካሜራ) ከእነ አንሺው በ1875 ዓም ወደ ሀገራችን ገባ። ሆኖም ግን አጼ ምኒልክ ፎቶውን ሊነሱ ሲሉ ቀሳውስቱ መኳንንቱ ከለከሏቸው፣ ርኩስ ነገር ነውና አጥፉልን አሏቸው። ምኒልክም "እግዚአብሔር የፈጠረውን ነገር አታርጉ፣ አትንኩ፣ ነውር ነው ማለት አምላክን መቃውም ነው እንዲህ ያለ ሀሳብ አታስቡ ዞር በሉ ከፊቴ" ብለው ግንቦት 13 ቀን 1875 ዓ/ም አጼ ምኒልክ የምትመለከቱትን የመጀመሪያ ፎቶ ተነሱ። መልካቸውንም በማየታቸው … [Read more...] about ፎቶግራፍ እና አጼ ምኒልክ
ትልቅ ሰው ትልቅን
ይባላል ... ድሮም ይነገራል ትልቅ ሰው ትልቅን ያስከትላል ሲባል በፊትም ሰምተናል ይኸው ዕውነት ሆኖ ሲፈጸም አየን ቃሉ በነጋሽ ገ/ማርያም፣ በተስፋዬ ሳህሉ የሐምሌ ወርን የሰላሳ ቀናት እቅፍ በነኀሴ ተክተን ሳናልፍ ሁለቱን ታላላቅ የጥበብ ከዋክብት አከታትለን አጣን የአዛውንቶች ክበብን ዘጋን ፀጋዬ ገ/መድህን በጻፈው አባተ መኩሪያ ባዘጋጀው አውላቸው ደጀኔ፣ ወጋየሁ ንጋቱ በተጫወቱበት ዓለሙና ሲራክ አብረው በሆኑበት እነ አስናቀች ወርቁ፣ በላይነሽ አመዴ፣ እነ አባተ መኩሪያ መላኩ አሻግሬና ዘነበች ታደሰ እነ ሠይፈ አርኣያ ሙናዬ መንበሩ፣ ኃይማኖት ዓለሙ፣ እነ አስራት አንለይ በኃይሉ መንገሻ፣ ሱራፌል በጋሻው፣ ያ ፍስሀ በላይ በተካፈሉበት ... የላይ ቤት ትዕይንት ተባብረው አብረው አንድ … [Read more...] about ትልቅ ሰው ትልቅን
ትዝታ – ሀዲስ አለማየሁ
ቅኝት - መስፍን ማሞ ተሰማ የቃኚው ማስታወሻ፤ ጎልጉል ድረገፅ ጋዜጣ ጁላይ 2 / 2017 “ራስ እምሩን በተመለከተ” በሚል ርዕስ አንድ ፅህፍ ለንባብ አብቅቷል። ይህ የጎልጉል ድረገፅ ጋዜጣን አቋም ያንፀባረቀው ፅሁፍ ሙያዊ ሥነምግባርን (ፕሮፌሽናል ኤቲክስ) ከብቃትና ከሃላፊነት ጋር ያዋደደ ስህተቱንም በግልፅና ያለማወላወል የተቀበለና ለእርማቱም መፍትሄን ያመላከተ መሆኑ የድረገፁን ዝግጅት ክፍል የሚያስወድሰውና በአርአያነትም ከመጀመሪያው ረድፍ የሚያቆመው ይሆናል። የሚዲያ ተልዕኮ መሰረቱ እንዲህ ሲሆን ተዓማኒነቱንና ሚዛናዊነቱን ያረጋግጣልና። በፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በተፃፈው ‘አዳፍኔ’ መፅሀፍ ላይ ክቡራ ልዑል ራስ እምሩ ሃይለ ሥላሴ በአርበኝነታቸው ሳይሆን ‘ከጣሊያን ደሞዝ ተቆራጭ የሆነላቸው ባንዳ’ ተደርገው ከባንዶች የስም ዝርዝር ውስጥ መግባታቸው ለዚህ ቃኚ … [Read more...] about ትዝታ – ሀዲስ አለማየሁ
ስምህን ሳላነሳ፣ የተወጋ አይረሳ!
ስምህን ሳላነሳ፣ ምኑን ሆንከው ፀጋ ለአብሮነት መኖር፣ እየሆንክ አደጋ፣ አድርገህ ከያዝከው፣ የሙሉቀን ሥራ ለማቃባት ደም፣ ኦሮሞን ካማራ። ‘ጀሃዳዊ ሃረካት’፣ እና ‘አኬል ዳማ’ በለምለሟ አርሲ፣ በአኖሊ ከተማ ወያኔ ያቆመው፣ የጥላቻ ሃውልት የተሸከመው እጅ፣ የተቆረጠ ጡት ሆነ ውጤት አልባ፣ አነሰ አሉህ እንዴ አሽከርካሪዎችህ፣ ፍጠር ሌላ ዘዴ? ጦርና ጎራዴ ሕዝቡን ለማማዘዝ ድንገት ቱግ ብለህ፣ የምትረጨው መርዝ። ዕውቀት ነበርኮ፣ ወገንን ለመጥቀም ተከባብሮ እንዲኖር፣ ተዋዶ በሰላም አየ ያንተስ መማር፣ “በረከተ መርገም”!! ተስፋ ለቆረጠ፣ ቀን ለጨለመበት ለጭቁን ወገኑ፣ መላ ለጠፋበት ታጭዶ ለሚወቃው፣ በአግዓዚ ጥይት በአላሚ እሩምታ፣ በቅሊንጦ ታጥሮ ዶጋመድ ለሆነው፣ በሳት ተንጨርጭሮ ፍዳውን ለሚያየው፣ እሥር ቤት ታጉሮ እርቃኑን ለቀረው፣ … [Read more...] about ስምህን ሳላነሳ፣ የተወጋ አይረሳ!
New book unveils 12 soft skills that make or break one’s success
FOR IMMEDIATE RELEASE Press Release Soft Skills That Make or Break Your Success: 12 soft skills to master self, get along with, and lead others successfully by Assegid Habtewold- a leadership expert and soft skills workshop facilitator, is now available. The book is based on a story and shares great insights, approaches, and tools essential to develop the 12 vital soft skills that make or break one’s success. Silver Spring, MD, July 13 … [Read more...] about New book unveils 12 soft skills that make or break one’s success
ካየሁት ከማስታውሰው
ማስታወሻ ከቃኚው፤ ይህ የልዑል ራስ እምሩ ሃይለ ሥላሴ መፅሀፍ ቅኝት በቅድሚያ ጥቅምት 2004 ዓ/ም - ኖቬምበር 2011- በሌሎች ድረገፆች ላይ ለንባብ ቀርቧል። በዚህ ወቅት በጎልጉል ድረገፅ ጋዜጣ ላይ መቅረብ ያስፈለገበት ምክንያትም በቅርቡ ጎልጉል 'የኢትዮጵያ አርበኞች ውለታና የባንዳዎች ዕዳ' በሚል በግንቦት ወር ላይ አርበኞቻችንን ለመዘከር ባወጣው ፅሁፍ ራስ እምሩ ከ'ባንዳዎች' የስም ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ባስነሳው ውዝግብ ነው። ይህ ፅሁፍ/ቅኝት እዛ ውዝግብ ውስጥ አይገባም። ሆኖም ክቡር ልዑል ራስ እምሩ ሀገራችን ከነበረቻቸው ታላላቅና ስመጥር ኢትዮጵያውያን አርበኞቻችን አንዱ መሆናቸውን ቃኚው የሚያምንና እጅግም ከበሬታ ያለው በመሆኑ በህይወት ዘመናቸው ፅፈው የተዉልንን ማስታወሻ መመርመሩ መቃኘቱ ተገቢ መሆኑን ስላመነበት እነሆ የተከበረው የጎልጉል ድረገፅ ጋዜጣ ፈቃዱ … [Read more...] about ካየሁት ከማስታውሰው
“ደግ ሰዉ አለፈ ..”
አባት ያቆየዉን ልጅ እዲጠብቀዉ የተከበሩ ኮ/ል አስናቀ እንግዳ፤ ኢትዮጵያን ለሚረከበዉ ወጣት ትዉልድ አዘዉትረዉ እንዲህ ይሉ ነበር። "አንተ የዛሬ ትዉልድ ሆይ! አንድ ጊዜ ቆም ብለህ አዳምጠኝ። ከተቻለ አባቶችህ ከሠሩት ላቅ ያለ፤ በስተቀር የእነሱን ያህል ካልሠራህ ሐገር አይኖርህም። የእኔ ትዉልድ በስልጣኔ ኋላ ቀር ቢሆንም፤አባቶቹ ከሠሩት በላይ አከናዉኖ አደራዉን ተወጥቶ፤ሀገሪቱን አስረክቦሃል።አንተም ለልጆችህ ይህችን ጥንታዊ ሐገር በክብር ለማስረከብ እንድትችል፤ ወኔ ይኑርህ። ወኔ እንዲኖርህ ለሆድህ አትገዛ። ኩራት ራት ነዉ ብለህ፤ ለራስህ ኀሊና ተገዛ " ይሉ ነበር። እንግዲህ ይህን የመሰለ ቁምነገር ሲያስተምሩ የኖሩ አባት፤ የወጣትነት ጊዚአቸዉ ምን እንደሚመስል ከአርበኝነትና ከጠቅላላ የትግል ታሪካቸዉ የቀነጨብኩትን ከዚህ በታች በግጥም እያቀረብኩ፤ኮ/ል አስናቀ እንግዳ በርግጥ … [Read more...] about “ደግ ሰዉ አለፈ ..”