የሰራህን በዓይንህ አይተህ ሲወሻክት ወይም ሰምተህ ልታቆመው ብትነሳ በዝምታ ፊት ብትነሳ አፍሮ ይተው እንዳይመስልህ ስምህን ነው ሚከትፍልህ ከዛ - ይልቅ ነገርህን አ’ርገህ ድብቅ ትንሽ ጊዜ ብትጠብቅ እንደወትሮው ሱሱን ሊያደርስ ካ’ንዱሊቀምስ ካ’ንዱ ሊልስ ከሰው ጋራ ሲቀላቀል ባልታሰበ የፊት ተንኮል ተይዞልህ ፊትህ ሲቀል መፋረጃህ ያን ጊዜ ነው ተቀላቅለህ አብረህ በለው ወይንም በዓይንህ ገድለህ ማረው (ወለላዬ ከስዊድን) … [Read more...] about ገድለህ ማረው
Literature
ጽፈኪን
“ደሸት” የብርሃን እውነት!
“ደሸት” የብርሃን እውነት! የማጂ፣ የጂማ፣ የመንዲ፣ የመደባይ አባት የማራ፣ የዥማ፣ የገንቲ፣ የአሬቲ ... አያት የአማራው፣ የኦሮሞው፣ ... የዘር ግንድ አውራ የመተሳሰሪያ እውነተኛ ምንጭ አሻራ! “ደሸት” ኢፋ ዹጋ ፍጥረተ ማለዳ የዘር ሀረግ ገመድ ምስጢራዊ ጓዳ አባ ቃሉ አባ ውሉ አያ ፍቅሩ ትስስሩ ዘረ ሸጋ ኢፋ ዹጋ መሆንህን አምኖ አማራ ኦሮሞ ስምህን በስሙ አትሞ “ደ”ን ደግ ብሎ አንብቦ “ሸ”ን ሸበበ ብሎት አንግቦ “ት”ን ትስስር ይለዋል ውልደቱን ከትቦ “ደሸት” የዘር ምንጩ አባ እቅጩ ስመ ክብሩ ውስጠ ምስጢሩ “ደሸት” የብርሃን እውነት! (ኢፋ ዹጋ!) ዘሩን ሲያበዛ ሲዘረጋ ማጂ፣ ጂማ፣ መንዲ፣ መደባይ ብሎ ሰይሞ የዘር ሲሳይ መደባይ ስሙን ከስሙ … [Read more...] about “ደሸት” የብርሃን እውነት!
ወንዙ እና ዛፉ
ስርሽን አየሁት ቁልቁል ተዘርግቶ፣ ረዝሞ ተባዝቶ፣ አንድ አንቺን ሊያሳድግ፣ አንድ አንቺን ሊያቀና፣ እጅግ ተበራክቶ፣ በዚህ ከቀጠለ የጉዞ ርዝመቱ፣ ውፍረት ከጨመረ፣ ካደገ ቁመቱ፣ ወንዙ አንጀቱ ታልቦ፣ መቅኒው ተመጥምጦ፣ አፅመ ወዙ ደርቆ፣ ደም ውሃው ተመጦ፣ መላ አካሉ ፈርሶ እርቃኑን ተጋልጦ፣ ባዶ መቅረቱ ነው ድንጋይ ጥርሱ ገጦ፣ ወለላዬ ከስዊድን (welelaye2@yahoo.com) … [Read more...] about ወንዙ እና ዛፉ
Kidane Alemayehu, My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia
The journey which author Ato Kidane Alemayehu chronicles in his new book takes him through Lesotho, Tanzania, Uganda, United Arab Emirates and the Horn of Africa as a representative of the United Nations, and ultimately to establish an organization dedicated to confronting “Fascist Italy and the Vatican.” His book contributes valuable information to the history of East Africa, the United Arab Emirates, and to the rationale behind Ethiopia’s struggle to win recompense from Italy for crimes … [Read more...] about Kidane Alemayehu, My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia
ደም ነው ሥርየቱ
ዐባይ ቢሻው ይጉረፍ በጣና ላይ ነግሶ አሎሃ ይደፍርስ ተከዜም ደም ለብሶ ማሂንም አቋሽም ጓንግም በሙላቱ መሻገሪያ ይንሳ እስኪያልፍ ክረምቱ ይፎክር ያቅራራ ይኩራ በጉልበቱ ድሮም እንዳይፀዳ በጎርፍ ውኃ ታጥቦ የጀግና ሰው ሞቱ ያውቃሉ እናውቃለን ዛሬም እንደ ጥንቱ ደም በደም ይፀዳል ደም ነው ሥርየቱ። ለጀግና ዕምባ አይረጩም ፀጉርም አይላጩም ዋይታና ለቅሶ ሙሾ አይደረድሩም ወይም ፊት አይነጩም እንደ አባት አደሩ እንደ ጎንደር በሃል ደም ነው ሥርየቱ ደም በደም ይፀዳል። አለፋ ጣቁሳ ደንቢያና ፎገራ ጭልጋ ገለድባ ከሽንፋ እስከ ቋራ ጎዛምን በላያ ከመተክል ፓዌ ከሻግኔ ወንበራ ከፍኖተ ሰላም ማንኩሳ እንጅባራ መተማ ሰራቆ ጫቆና አዳኝ አገር ቆላ ደጋ ዳሞት ቋሪትና አቸፈር እነሴና ነብሴ ሞጣ ቀራኒዎ ጭስ ዐባይ ባህር ዳር ነፋስ መውጫ ጋይንት እስቴ ደብረ … [Read more...] about ደም ነው ሥርየቱ
ዕዘኑ ለቀሪ
የመቅደላው ደባ ቋጠሮ የተቀበረው በቂም ጓሮ የምስጢሩ ገመና ለሥልጣኑ ንግሥና ከጠላት ጋር ወግኖ በተቸረው ኃይል መቅኖ መይሳውን አስገድሎ ለመግዛት ተደላድሎ በትረ መንግሥቱን ምራጭ ካሳ የጨበጠበት ድርጊት ጠባሳ ደረስጌን በውቤ ብሎ የቂም ብድሩን ከፍሎ የጎንደሮች መሬት ቁርሾ የበደሉ ዋይታ ሙሾ የግፉ ክፋት ገመና ይደረደራል ገና በበገና በበገና። ያችን የሙታን እናት አጉል ድከሚ ብሏት ያለ ፋይዳ ከንቱ ልፊ ዘርሽንም በዘር አጥፊ ለማለት ይመስላል መለእክቱ ነገረ ሥራው ኩነቱ። ለባለ ቀኑ ድሎት የማይጓደል አቅርቦት ይረጋገጥ ዘንድ ታልሞ የራሱን ኩራዝ አጨልሞ በየመብራቱ ምሰሶ ስር ዘብ መቆሙ ደብረታቦር ምፀቱ ለገብርዬ... ለገልሞ በአግራሞት አስደምሞ የትንብቱ ቅላጼ መዋዕሉ ለካስ ጊዜ ኖሯል ባለድሉ። ለጎንደሮች መከራ ለባለ … [Read more...] about ዕዘኑ ለቀሪ
አዲስ እንደ ቬኒስ
“አንተስ…?”
ዓይኔን በዓይኔ ያየሁበት፣ በስተእርጅና ያገኘሁት፣ የትናንቱ ማሙዬ፣ ያሳደኩት አዝዬ የንግሊዞችንወረራ ሰምቶ፣ በቴዎድሮስ ሞት ተቆጥቶ፣ ለምን? ለምን ሞተ? ብሎ ሲያለቅስ፣ የዓይኑን ዕንባ ላደርቅ- የልቡን መሰበር ላድስ፣ ጀግኖቻችንን ቆጥሬ- ታሪካችንን ባወድስ፣ ዕንባውን ዋጥ አድርጎ- በአትኩሮት ዓይኔን እያየኝ፣ «አንተስ...?» አንተስ!- ምን ሰርተሀል? በማለት ጠየቀኝ። እድሜ ቢደራረብ ተግባር ሳይላበስ፣ እንደዚህ እንደኔ ያስጠይቃል ለካስ! (ወለላዬ) … [Read more...] about “አንተስ…?”
ላንዲት መስቲካ ሻጭ ህጻን
በደብተርሽ ምትክ ትንሽ ሱቅ ታቅፈሽ ካልፎሂያጅ እግር ስር፤ እንደ ድንቢጥ ከንፈሽ ጋሼ ግዙኝ ስትይ፤ ኣንጋጠሽ ወደ ላይ ለጉድ ተጎልቸ፤ ምታረጊውን ሳይ ራሴስ ይታመም፤ ምላሴን ምን ነካው ግራዋ ይመስል፤ መረረኝ ማስቲካው:: ኣፈር ጠጠር ለብሶ ፤በዶዘር ተድጦ መስኩ ከነጎርፉ ሰማይ ከነዶፉ ለጌቶች ተሽጦ ኣተር ነው እያሉ፤ ኣፈር ዘግኖ መፍጨት ገነት ነው እያሉ፤ መስክ ላይ መፈንጨት ጠበል ነው እያሉ፤ ተጎርፉ መራጨት ይህንን ማን ሰጦሽ ገና በልጅነት፤ ልጅነት ኣምልጦሽ፡፡ በምቢልታ በዋሽንት፤ በከበሮ ታጥሮ በክራር ተማግሮ በቆመ ከተማ እምባሽ ቅኝት የለው ፤ለሰው ኣይሰማ፡ ጠዋት የፎከረ ፤ቀትር ላይ ሲረታ ዛሬ ዝሎ ሲወድቅ ፤ትናንት የበረታ ኑሮን ያህል ሸክም፤ ያላንቀልባ ሲያዝል፡፡ ምን ጸጋ ለብሶ ነው፤ ትከሻሽ የማይዝል፡፡ (በእውቀቱ … [Read more...] about ላንዲት መስቲካ ሻጭ ህጻን
“የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!
ለረጅም አመታተ የጣልኩትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው እንድመዝ አስገደደኝ - በ ኢትዮ-ሚዲያ (Ethiomedia) እና በጎልጉል (Googlgule) ድህረ-ገፆች ላይ ከወራት በፊት በዶክተር ፍቃዱ በቀለ በተባሉ ግለሰብ በ"የተቆለፈበት ቁልፍ" መፅሐፉ ላይ የቀረበ አንድ ፅሑፍ። "ሃያሲው" በዘመናችን አቻ ያላገኙለት (ወደር የሌለው) መፅሐፉ መሆኑን ነው የገለፁልን። "...የስነ-ጽሁፍም ዋና ዓላማው በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉትን አስቀያሚም ሆነ ቆንጆ ነገሮች ስዕላዊ በሆነ መልክ መግለጽ ሲችሉና አንባቢውን በልዩ ሃሳብ ውስጥ ተመስጦ እንዲዋኝ ማድረግ ሲችሉ ብቻ ነው።..." በማለት ካብራሩ በኃላ ከ`ዚህ አንፃር "የተቆለፈበት ቁልፍ" እንደተዋጣለት መሰክርነታችውን ይሰጣሉ። አንዲህ ሲሉ "....በታሪካችን ውስጥ በመጀመሪያ ጊዜ በልዩ አቀራረብ የተዘጋጀና የተጻፈ ትምህርታዊ መጽሀፍ ነው … [Read more...] about “የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!