• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስማኝ ሰማእቱ!

April 4, 2018 05:56 am by Editor Leave a Comment

ከባርነት ሞትን የመረጥከው ወንዱ፣
አፉን ክፍት አርጎ የዋጠህ መቃብሩ፣
የማዋይህ አለኝ ስማኝ ሰማእቱ፡፡

የፈሰሰው ደምህ በህልሜ እየታየኝ፣
አጥንትህ ከመቃብር እየጎራበጠኝ፣
እሾህ ቀጋ ሆኖ አላስተኛህ አለኝ፡፡

ለፍትህ ስትጮህ የቀረኸው ባጭር፣
ጎንደር ደብረታቦር ወልድያ ባህርዳር፣
ቡሬና ዳንግላ ማጀቴና አቸፈር፣
ዛሬም ወንድሞችህ ታስረዋል ግዮን ዳር፡፡

በስናይፐር የፈጁህ ህሊና ቢሶቹ፣
ለውጥ አመጣን ብለው ያንኑ ደገሙ፣
አንድ አስገዳይ ነቅለው ሌላውን ተከሉ፡፡

አጥንትህን ከአምቦ ከእሬቻ ለቃቅሞ፣
መሰላል አረገው ከለማ ጋር ሰርቶ፡፡

በስንት በጎች ደም እንደተነከረ፣
እጁን ሳይታጠብ አቢይ ቀደሰ፡፡

ኢያሱና ሙሴን ተከተሉ እያሉ፣
ስንቱን ዘልዛላ እንከፍ ከጀርባ አሰለፉ፡፡

ተመራጩ አስገዳይ መራጩም ገዳይ ነው፣
የሌላው ማሽቃበጥ ምን እሚሉት ጉድ ነው?

ትናንትናም ያአድጊ ዛሬም ይህአድጊ ነው፣
አሸርጋጅ የበዛው የምን ለውጥ አይቶ ነው?

አጋዚ ሰው ፈጅ እያለ እሚጮኸው፣
ጆሮ ጠቢ አቢይን ቅዱስ አርጎ አረፈው፡፡

እንኳን ፈሪሳውያን እነ ሆድ አምላኩ፣
እነ ኦባንግ ሜቶም ለይሁዳ ሰገዱ፡፡

ስንቱ ወለወልዳ ስትሞት ያለቀሰው፣
አዛኝ አንጓች መስሎ የአዞ እምባ ያነባው፣
አስገዳይህ ሲነግስ ደስ ይበልህ አለው፡፡

ስንቱን ላስፈጀ ጉድ ድጋፍ እየሰጡ፣
የፍትህ ታጋይ ነን ብለውን አረፉ፡፡

እንዳንተ በጽናት መታገል ሲለግሙ፣
በአጥንቶችህ ባላ አቢይን ሰቀሉ፡፡

ታሪክ በደም ጥፈህ በክብር ያለፍከው፣
ስማኝ ሰማእቱ የኔ መልእክት ይህ ነው፡፡

አንተ ሙተህ አዝነን ሳይወጣ ሳልስትህ፣
የምዕራብ ዲፕሎማት እንዲሁም ገዳይህ፣
ፖለቲካ ቁማር ዘረጉ እመቃብርህ፡፡

የሞትክለት ህልምህ እንዳይደርስ ከዳሩ፣
የነደደው እሳት እንዲጠፋ ፍሙ፣
ትልቅ ማዳፈኛ ከምድጃ ጎለቱ፡፡

አስገዳይ ለማንገስ ፓርላማ ከተሙ፣
የሕዝብ ተወካዮች ብለው አፍጣጮቹ፣
እንደ ኦሪት ሁሉ ህማማትን ጣሱ፣
መነኩሳትን አስረው እነሱ እያሽካኩ፣
ድግስ እየዋጡ ዳንኪራ እየመቱ፣
ጉልቻን አንስተው ጉልቻ ጎለቱ፡፡

እየታገልን ነው ሲሉ የነበሩ፣
በራሳቸው እምነት ብቃትን ስላጡ፣
ወደ ላይ አንጋጠው አቢይ አቢይ አሉ፣
እንኳን የሞቱትን ፈጣሪን ረሱ፡፡

የራሱን ልብ አሞት የተጠራጠረ፣
በካድሬው አቢይ ቃል አመነና ማለ፡፡

ዳሩ ይህም ቢሆን እንዳይልህ ክፍት፣
አርማህን አንስቷል ፍም ጎራሹ ወጣት፡፡

ብቁ ሰማእታት እንደ አንተ የፀኑ፣
ነፃነት ወይም ሞት ብለው የቆረጡ፣
ሞረሽ ይጣራሉ በዱር በገደሉ፡፡

ያሳደደህ ቢነግስ በህማማቱ እለት፣
አዳኝህ ይነሳል ቅዳምሽ እሁድ ማግስት፡፡

ሐዋርያት ዝቅዝቅ ታስረው ቢታረዱ፣
ክርስትና ሰፍቷል ቁመትና ወርዱ፡፡

ክርስቶስ ተሰቅሎ ተቀብሮ እንዳልቀረው፣
ያንተም ህልም እሚያርግ ዘላለም ህያው ነው፡፡

ገዳይ አስገዳዮች አንተን የሰውቱ፣
አስገዳይ ለማንገስ አንተን የረሱቱ፣
እንደ ፈሪሳውያን ይሁዳ ዘ አስቆርቱ፣
ታሪክ ሲመትራቸው ሲያርዳቸው ይኑሩ፡፡

ምድር ታሪክህን እንዳሳማረችው፣
ሰማዩም ነፍስህን በምቾት ያኑረው፣
እኛም አደራህን አኝከን አንብላው፣
ስማኝ ሰማእቱ መልእክቴ ይኸው ነው፡፡

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)
መጋቢት ሁለት ሺ አሥር ዓ.ም.

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule