• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስማኝ ሰማእቱ!

April 4, 2018 05:56 am by Editor Leave a Comment

ከባርነት ሞትን የመረጥከው ወንዱ፣
አፉን ክፍት አርጎ የዋጠህ መቃብሩ፣
የማዋይህ አለኝ ስማኝ ሰማእቱ፡፡

የፈሰሰው ደምህ በህልሜ እየታየኝ፣
አጥንትህ ከመቃብር እየጎራበጠኝ፣
እሾህ ቀጋ ሆኖ አላስተኛህ አለኝ፡፡

ለፍትህ ስትጮህ የቀረኸው ባጭር፣
ጎንደር ደብረታቦር ወልድያ ባህርዳር፣
ቡሬና ዳንግላ ማጀቴና አቸፈር፣
ዛሬም ወንድሞችህ ታስረዋል ግዮን ዳር፡፡

በስናይፐር የፈጁህ ህሊና ቢሶቹ፣
ለውጥ አመጣን ብለው ያንኑ ደገሙ፣
አንድ አስገዳይ ነቅለው ሌላውን ተከሉ፡፡

አጥንትህን ከአምቦ ከእሬቻ ለቃቅሞ፣
መሰላል አረገው ከለማ ጋር ሰርቶ፡፡

በስንት በጎች ደም እንደተነከረ፣
እጁን ሳይታጠብ አቢይ ቀደሰ፡፡

ኢያሱና ሙሴን ተከተሉ እያሉ፣
ስንቱን ዘልዛላ እንከፍ ከጀርባ አሰለፉ፡፡

ተመራጩ አስገዳይ መራጩም ገዳይ ነው፣
የሌላው ማሽቃበጥ ምን እሚሉት ጉድ ነው?

ትናንትናም ያአድጊ ዛሬም ይህአድጊ ነው፣
አሸርጋጅ የበዛው የምን ለውጥ አይቶ ነው?

አጋዚ ሰው ፈጅ እያለ እሚጮኸው፣
ጆሮ ጠቢ አቢይን ቅዱስ አርጎ አረፈው፡፡

እንኳን ፈሪሳውያን እነ ሆድ አምላኩ፣
እነ ኦባንግ ሜቶም ለይሁዳ ሰገዱ፡፡

ስንቱ ወለወልዳ ስትሞት ያለቀሰው፣
አዛኝ አንጓች መስሎ የአዞ እምባ ያነባው፣
አስገዳይህ ሲነግስ ደስ ይበልህ አለው፡፡

ስንቱን ላስፈጀ ጉድ ድጋፍ እየሰጡ፣
የፍትህ ታጋይ ነን ብለውን አረፉ፡፡

እንዳንተ በጽናት መታገል ሲለግሙ፣
በአጥንቶችህ ባላ አቢይን ሰቀሉ፡፡

ታሪክ በደም ጥፈህ በክብር ያለፍከው፣
ስማኝ ሰማእቱ የኔ መልእክት ይህ ነው፡፡

አንተ ሙተህ አዝነን ሳይወጣ ሳልስትህ፣
የምዕራብ ዲፕሎማት እንዲሁም ገዳይህ፣
ፖለቲካ ቁማር ዘረጉ እመቃብርህ፡፡

የሞትክለት ህልምህ እንዳይደርስ ከዳሩ፣
የነደደው እሳት እንዲጠፋ ፍሙ፣
ትልቅ ማዳፈኛ ከምድጃ ጎለቱ፡፡

አስገዳይ ለማንገስ ፓርላማ ከተሙ፣
የሕዝብ ተወካዮች ብለው አፍጣጮቹ፣
እንደ ኦሪት ሁሉ ህማማትን ጣሱ፣
መነኩሳትን አስረው እነሱ እያሽካኩ፣
ድግስ እየዋጡ ዳንኪራ እየመቱ፣
ጉልቻን አንስተው ጉልቻ ጎለቱ፡፡

እየታገልን ነው ሲሉ የነበሩ፣
በራሳቸው እምነት ብቃትን ስላጡ፣
ወደ ላይ አንጋጠው አቢይ አቢይ አሉ፣
እንኳን የሞቱትን ፈጣሪን ረሱ፡፡

የራሱን ልብ አሞት የተጠራጠረ፣
በካድሬው አቢይ ቃል አመነና ማለ፡፡

ዳሩ ይህም ቢሆን እንዳይልህ ክፍት፣
አርማህን አንስቷል ፍም ጎራሹ ወጣት፡፡

ብቁ ሰማእታት እንደ አንተ የፀኑ፣
ነፃነት ወይም ሞት ብለው የቆረጡ፣
ሞረሽ ይጣራሉ በዱር በገደሉ፡፡

ያሳደደህ ቢነግስ በህማማቱ እለት፣
አዳኝህ ይነሳል ቅዳምሽ እሁድ ማግስት፡፡

ሐዋርያት ዝቅዝቅ ታስረው ቢታረዱ፣
ክርስትና ሰፍቷል ቁመትና ወርዱ፡፡

ክርስቶስ ተሰቅሎ ተቀብሮ እንዳልቀረው፣
ያንተም ህልም እሚያርግ ዘላለም ህያው ነው፡፡

ገዳይ አስገዳዮች አንተን የሰውቱ፣
አስገዳይ ለማንገስ አንተን የረሱቱ፣
እንደ ፈሪሳውያን ይሁዳ ዘ አስቆርቱ፣
ታሪክ ሲመትራቸው ሲያርዳቸው ይኑሩ፡፡

ምድር ታሪክህን እንዳሳማረችው፣
ሰማዩም ነፍስህን በምቾት ያኑረው፣
እኛም አደራህን አኝከን አንብላው፣
ስማኝ ሰማእቱ መልእክቴ ይኸው ነው፡፡

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)
መጋቢት ሁለት ሺ አሥር ዓ.ም.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule