• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምነው ደም ደም አይለን?

June 8, 2018 05:11 am by Editor 1 Comment

ፍትህ ሳያደርቀው የፈሰሰን ፍዳ፣
ንስሀ ሳያጥበው የቆሸሸን ጓዳ፣
ዱለትን መቋደስ ከገዳዮች ጋራ፣
የሐጥያትም ሐጥያት የታሪክም ዕዳ!

ፍትህ ነፃነትን መብትን ተርበው፣
ኢፍታዊነትን እንደ አውሬ ተናንቀው፣
ስንቶቹ ተሰው ባሩድ ተመግበው?

ነፃነት ወይም ሞት በቃ ዘራፍ ብለው፣
ስንቶች ተሰውልን ጫካ ዱር ሸፍተው?

በእሬቻ በጥምቀት በመስጊድ ሰገዳው፣
በሰፈር መንደሩ በገጠር ከተማው፣
እንደ ፋሲካ በግ የታረደ ስንት ነው?

ባዶ ስድስት ጉድጓድ በጪስ የታፈነው፣
ቃሊቲ ዓለም በቃኝ የተዘቀዘቀው፣
ቅሊንጦና ዝዋይ በእሳት የነደደው፣
ሽሮሜዳ ታስሮ ጥፍሩ የወለቀው፣
ብር ሸለቆ አዘዞ ጉረኖ የገባው፣
ማሰቃያ ቦታው ጭራሽ ያልታወቀው፣
ስንት መከረኛ ምን ያህል ዜጋ ነው?

የጋንቤላን ምድር ሽፍን ያደረገው፣
ኦጋዴን በርሃን በጎርፍ የጠረገው፣
ምን ያህል ሬሳ ስንት በርሜል ደም ነው?

ጎንደር ደብረታቦር በባሩድ ያለቀው፣
ባህርዳር ወልድያ ስናይፐር የፈጀው፣
አምቦ ደብረ ዘይት ጥይት ያረገፈው፣
መች ተቆጥሮ ያልቃል ቆጣሪ ቢኖረው?

በሽሽት በስደት በአውሬ የተበላው፣
ባህርን ሲሻገር ድንብልዝ ያሰመጠው፣
ምን ያህል ኮረዳ ምን ያህል ጎበዝ ነው?

ወልቃይት ራያ ዘሩ የመከነው፣
በደኖ በገደል የተወረወረው፣
አሶሳ መተከል የተቆራረጠው፣
ከፋ ኢሉባቦር ሜጫ የከተፈው፣
አይምሯችን ያስላ ምን ያህል ሕዝብ ነው?

ይኸ ግፍ ሲፈጠም ለካስ ያለቀስነው፣
እርሾና አብሲት ጥለን በትኩስ ደማቸው፣
በተሰውት አጥንት ዳቦ ልንጋግር ነው፡፡

ጅቦቹ ሰው በሉ ስንል የነበረው፣
ለካስ የውሻ ጠጉር ካባ ደርበን ነው፣
ትርፍራፊ ልፋጭ መጎተት አምሮን ነው፡፡

በየ አደባባዩ ስንጮህ የነበርነው፣
ለካስ በሙታን ደም ገንፎ ልንሰራ ነው፡፡

አይ ጊዜ ፈታኙ አይ ጊዜ መስካሪው፣
ስንቱን አጭበርባሪ ከርሳም አጋለጥከው፡፡

በእርቅና በሰላም እያመካኘ፣
ስንቱ ይሁዳ ሰው ለሰይጣን ሰገደ፡፡

ዓለም ፍርደ-ገምድል ዓለም ወለወልዳ፣
ቀጣፊን አጽዳቂ ሐቀኛን ኮንና፡፡

በእርቅና በሰላም ስንት ሆዳም ነገደ፣
የሰማእት እሬሳ እየተራመደ፡፡

የሰማእት ሥጋ ቅርጫ ለመቃረጥ፣
በሙታንም አጥንት ንግድ ቤት ለመክፈት፣
ከገዳዮች ጋራ አብረን ስንዶልት፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ገዳይ ችሎት ሳይቀርብ ሟችም ሳያገኝ ፍርድ፣
ፍትህ ገደል ገብታ ንስሃ እንጦሮጦስ፣
እርምን ልንጠሸቅም ከገዳይ ስንቀርብ ማድ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይሰቀጥጥ?

ሥጋውን እንጀራ ደሙንም ሰርተን ወጥ፣
እየሸመለልን ሰማእት ልንውጥ፣
ከነፍሰ በላዎች አብረን ስንቀመጥ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ይገርማል! ሰው ከንቱ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ሰኔ ሁለት ሺ አስር ዓ.ም.

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. እውነቱ ይነገር says

    June 18, 2018 05:05 pm at 5:05 pm

    ወገኔ አቶ በላይነህ

    I would like to say thank you for your message. Please keep it up!

    ጥያቄ አለኝ???

    እውነተኛና ግልጽ መልስ ያለው ሰው በመረጃ አስደግፎ ይመልስልኝ!

    1)የኢትዮጵያውያን ዓይኖች መቼ ነው እንባቸው የሚደርቀው/የሚታበሰው?

    2)እየተባባሰ ለመጣው ለኢትዮጵያውያን የዘመናት እንባ ምክንያቱ/ምንጩ በእውነት ምንድነው?

    3)የውጭ ሃገር ወራሪ ጠላት ያላስለቀሰን እኛ ኢትዮጵያውያንን ለምንድነው የራሳችን ወገኖች የደም እንባ እንድናነባ የሚያደርጉን????

    4)አማራው በእውነት በተናጠል ኢትዮጵያንን በሙሉ በማን አለብኝነት ረግጦ በገፍ ገዝቷልን????

    5)በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በእውነት አንዱ ብሔረ ሰብ በሌላው ብሔረ ሰብ ሆነ ብሎ በደል ሠርቷል ወይስ እንደ ማንኛውም ሃገር የሕብረተሰብ እድገት-ታሪክ ሃይልና ጉልበት ያገኘው ጎሳና ሰፈርተኛ በነበረው ንቃተ ህሊና ላይ ተመስርቶ በሚፈጠር ግጭት የመጣ ማንነት ላይ የተመሰረተ ታሪክ?

    6)የሸዋ መሳፍንት ታሪክ ሲጠና ስንቱ አማራ ስንቱ ደግሞ ኦሮሞ እንደነበረ እስቲ በዳታ አስረዱኝ???

    7)በሃይለ ስላሴ፣ በደርግና በወያኔ መንግሥት ዘመናት ወቅት አመራር ላይ የነበረውን አካል በብሔረሰብ ደረጃ በመረጃ አስደግፋችሁ/አሁን ዛመኑ የመረጃ ጊዜ ስለሆነና በአሉባልታና በወሬ ወለደ ወሬ ይህን ትውልድ ማታለል ስለማይቻል/ እስቲ ንገሩን???

    ሁሉም የዘራውን ስለሚያጭድ እንጠንቀቅ?
    ወንድምን ከወንድሙ ጋር ማጋጨቱ ይብቃ?
    እውነት ነጻ ያወጣልና በጋራ
    ለእውነተኛ የጋራ ሃገርና
    መልካም ሥራ በእውነት እንነሳ?

    ወስብሐት ለእግዚአብሔር
    ሕዝባችንን ማስተዋል ይስጥልን!
    አሜን።

    እውነቱ ይነገር
    ከለሁበት

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule