• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምነው ደም ደም አይለን?

June 8, 2018 05:11 am by Editor 1 Comment

ፍትህ ሳያደርቀው የፈሰሰን ፍዳ፣
ንስሀ ሳያጥበው የቆሸሸን ጓዳ፣
ዱለትን መቋደስ ከገዳዮች ጋራ፣
የሐጥያትም ሐጥያት የታሪክም ዕዳ!

ፍትህ ነፃነትን መብትን ተርበው፣
ኢፍታዊነትን እንደ አውሬ ተናንቀው፣
ስንቶቹ ተሰው ባሩድ ተመግበው?

ነፃነት ወይም ሞት በቃ ዘራፍ ብለው፣
ስንቶች ተሰውልን ጫካ ዱር ሸፍተው?

በእሬቻ በጥምቀት በመስጊድ ሰገዳው፣
በሰፈር መንደሩ በገጠር ከተማው፣
እንደ ፋሲካ በግ የታረደ ስንት ነው?

ባዶ ስድስት ጉድጓድ በጪስ የታፈነው፣
ቃሊቲ ዓለም በቃኝ የተዘቀዘቀው፣
ቅሊንጦና ዝዋይ በእሳት የነደደው፣
ሽሮሜዳ ታስሮ ጥፍሩ የወለቀው፣
ብር ሸለቆ አዘዞ ጉረኖ የገባው፣
ማሰቃያ ቦታው ጭራሽ ያልታወቀው፣
ስንት መከረኛ ምን ያህል ዜጋ ነው?

የጋንቤላን ምድር ሽፍን ያደረገው፣
ኦጋዴን በርሃን በጎርፍ የጠረገው፣
ምን ያህል ሬሳ ስንት በርሜል ደም ነው?

ጎንደር ደብረታቦር በባሩድ ያለቀው፣
ባህርዳር ወልድያ ስናይፐር የፈጀው፣
አምቦ ደብረ ዘይት ጥይት ያረገፈው፣
መች ተቆጥሮ ያልቃል ቆጣሪ ቢኖረው?

በሽሽት በስደት በአውሬ የተበላው፣
ባህርን ሲሻገር ድንብልዝ ያሰመጠው፣
ምን ያህል ኮረዳ ምን ያህል ጎበዝ ነው?

ወልቃይት ራያ ዘሩ የመከነው፣
በደኖ በገደል የተወረወረው፣
አሶሳ መተከል የተቆራረጠው፣
ከፋ ኢሉባቦር ሜጫ የከተፈው፣
አይምሯችን ያስላ ምን ያህል ሕዝብ ነው?

ይኸ ግፍ ሲፈጠም ለካስ ያለቀስነው፣
እርሾና አብሲት ጥለን በትኩስ ደማቸው፣
በተሰውት አጥንት ዳቦ ልንጋግር ነው፡፡

ጅቦቹ ሰው በሉ ስንል የነበረው፣
ለካስ የውሻ ጠጉር ካባ ደርበን ነው፣
ትርፍራፊ ልፋጭ መጎተት አምሮን ነው፡፡

በየ አደባባዩ ስንጮህ የነበርነው፣
ለካስ በሙታን ደም ገንፎ ልንሰራ ነው፡፡

አይ ጊዜ ፈታኙ አይ ጊዜ መስካሪው፣
ስንቱን አጭበርባሪ ከርሳም አጋለጥከው፡፡

በእርቅና በሰላም እያመካኘ፣
ስንቱ ይሁዳ ሰው ለሰይጣን ሰገደ፡፡

ዓለም ፍርደ-ገምድል ዓለም ወለወልዳ፣
ቀጣፊን አጽዳቂ ሐቀኛን ኮንና፡፡

በእርቅና በሰላም ስንት ሆዳም ነገደ፣
የሰማእት እሬሳ እየተራመደ፡፡

የሰማእት ሥጋ ቅርጫ ለመቃረጥ፣
በሙታንም አጥንት ንግድ ቤት ለመክፈት፣
ከገዳዮች ጋራ አብረን ስንዶልት፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ገዳይ ችሎት ሳይቀርብ ሟችም ሳያገኝ ፍርድ፣
ፍትህ ገደል ገብታ ንስሃ እንጦሮጦስ፣
እርምን ልንጠሸቅም ከገዳይ ስንቀርብ ማድ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይሰቀጥጥ?

ሥጋውን እንጀራ ደሙንም ሰርተን ወጥ፣
እየሸመለልን ሰማእት ልንውጥ፣
ከነፍሰ በላዎች አብረን ስንቀመጥ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ይገርማል! ሰው ከንቱ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ሰኔ ሁለት ሺ አስር ዓ.ም.

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. እውነቱ ይነገር says

    June 18, 2018 05:05 pm at 5:05 pm

    ወገኔ አቶ በላይነህ

    I would like to say thank you for your message. Please keep it up!

    ጥያቄ አለኝ???

    እውነተኛና ግልጽ መልስ ያለው ሰው በመረጃ አስደግፎ ይመልስልኝ!

    1)የኢትዮጵያውያን ዓይኖች መቼ ነው እንባቸው የሚደርቀው/የሚታበሰው?

    2)እየተባባሰ ለመጣው ለኢትዮጵያውያን የዘመናት እንባ ምክንያቱ/ምንጩ በእውነት ምንድነው?

    3)የውጭ ሃገር ወራሪ ጠላት ያላስለቀሰን እኛ ኢትዮጵያውያንን ለምንድነው የራሳችን ወገኖች የደም እንባ እንድናነባ የሚያደርጉን????

    4)አማራው በእውነት በተናጠል ኢትዮጵያንን በሙሉ በማን አለብኝነት ረግጦ በገፍ ገዝቷልን????

    5)በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በእውነት አንዱ ብሔረ ሰብ በሌላው ብሔረ ሰብ ሆነ ብሎ በደል ሠርቷል ወይስ እንደ ማንኛውም ሃገር የሕብረተሰብ እድገት-ታሪክ ሃይልና ጉልበት ያገኘው ጎሳና ሰፈርተኛ በነበረው ንቃተ ህሊና ላይ ተመስርቶ በሚፈጠር ግጭት የመጣ ማንነት ላይ የተመሰረተ ታሪክ?

    6)የሸዋ መሳፍንት ታሪክ ሲጠና ስንቱ አማራ ስንቱ ደግሞ ኦሮሞ እንደነበረ እስቲ በዳታ አስረዱኝ???

    7)በሃይለ ስላሴ፣ በደርግና በወያኔ መንግሥት ዘመናት ወቅት አመራር ላይ የነበረውን አካል በብሔረሰብ ደረጃ በመረጃ አስደግፋችሁ/አሁን ዛመኑ የመረጃ ጊዜ ስለሆነና በአሉባልታና በወሬ ወለደ ወሬ ይህን ትውልድ ማታለል ስለማይቻል/ እስቲ ንገሩን???

    ሁሉም የዘራውን ስለሚያጭድ እንጠንቀቅ?
    ወንድምን ከወንድሙ ጋር ማጋጨቱ ይብቃ?
    እውነት ነጻ ያወጣልና በጋራ
    ለእውነተኛ የጋራ ሃገርና
    መልካም ሥራ በእውነት እንነሳ?

    ወስብሐት ለእግዚአብሔር
    ሕዝባችንን ማስተዋል ይስጥልን!
    አሜን።

    እውነቱ ይነገር
    ከለሁበት

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule