• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምነው ደም ደም አይለን?

June 8, 2018 05:11 am by Editor 1 Comment

ፍትህ ሳያደርቀው የፈሰሰን ፍዳ፣
ንስሀ ሳያጥበው የቆሸሸን ጓዳ፣
ዱለትን መቋደስ ከገዳዮች ጋራ፣
የሐጥያትም ሐጥያት የታሪክም ዕዳ!

ፍትህ ነፃነትን መብትን ተርበው፣
ኢፍታዊነትን እንደ አውሬ ተናንቀው፣
ስንቶቹ ተሰው ባሩድ ተመግበው?

ነፃነት ወይም ሞት በቃ ዘራፍ ብለው፣
ስንቶች ተሰውልን ጫካ ዱር ሸፍተው?

በእሬቻ በጥምቀት በመስጊድ ሰገዳው፣
በሰፈር መንደሩ በገጠር ከተማው፣
እንደ ፋሲካ በግ የታረደ ስንት ነው?

ባዶ ስድስት ጉድጓድ በጪስ የታፈነው፣
ቃሊቲ ዓለም በቃኝ የተዘቀዘቀው፣
ቅሊንጦና ዝዋይ በእሳት የነደደው፣
ሽሮሜዳ ታስሮ ጥፍሩ የወለቀው፣
ብር ሸለቆ አዘዞ ጉረኖ የገባው፣
ማሰቃያ ቦታው ጭራሽ ያልታወቀው፣
ስንት መከረኛ ምን ያህል ዜጋ ነው?

የጋንቤላን ምድር ሽፍን ያደረገው፣
ኦጋዴን በርሃን በጎርፍ የጠረገው፣
ምን ያህል ሬሳ ስንት በርሜል ደም ነው?

ጎንደር ደብረታቦር በባሩድ ያለቀው፣
ባህርዳር ወልድያ ስናይፐር የፈጀው፣
አምቦ ደብረ ዘይት ጥይት ያረገፈው፣
መች ተቆጥሮ ያልቃል ቆጣሪ ቢኖረው?

በሽሽት በስደት በአውሬ የተበላው፣
ባህርን ሲሻገር ድንብልዝ ያሰመጠው፣
ምን ያህል ኮረዳ ምን ያህል ጎበዝ ነው?

ወልቃይት ራያ ዘሩ የመከነው፣
በደኖ በገደል የተወረወረው፣
አሶሳ መተከል የተቆራረጠው፣
ከፋ ኢሉባቦር ሜጫ የከተፈው፣
አይምሯችን ያስላ ምን ያህል ሕዝብ ነው?

ይኸ ግፍ ሲፈጠም ለካስ ያለቀስነው፣
እርሾና አብሲት ጥለን በትኩስ ደማቸው፣
በተሰውት አጥንት ዳቦ ልንጋግር ነው፡፡

ጅቦቹ ሰው በሉ ስንል የነበረው፣
ለካስ የውሻ ጠጉር ካባ ደርበን ነው፣
ትርፍራፊ ልፋጭ መጎተት አምሮን ነው፡፡

በየ አደባባዩ ስንጮህ የነበርነው፣
ለካስ በሙታን ደም ገንፎ ልንሰራ ነው፡፡

አይ ጊዜ ፈታኙ አይ ጊዜ መስካሪው፣
ስንቱን አጭበርባሪ ከርሳም አጋለጥከው፡፡

በእርቅና በሰላም እያመካኘ፣
ስንቱ ይሁዳ ሰው ለሰይጣን ሰገደ፡፡

ዓለም ፍርደ-ገምድል ዓለም ወለወልዳ፣
ቀጣፊን አጽዳቂ ሐቀኛን ኮንና፡፡

በእርቅና በሰላም ስንት ሆዳም ነገደ፣
የሰማእት እሬሳ እየተራመደ፡፡

የሰማእት ሥጋ ቅርጫ ለመቃረጥ፣
በሙታንም አጥንት ንግድ ቤት ለመክፈት፣
ከገዳዮች ጋራ አብረን ስንዶልት፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ገዳይ ችሎት ሳይቀርብ ሟችም ሳያገኝ ፍርድ፣
ፍትህ ገደል ገብታ ንስሃ እንጦሮጦስ፣
እርምን ልንጠሸቅም ከገዳይ ስንቀርብ ማድ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይሰቀጥጥ?

ሥጋውን እንጀራ ደሙንም ሰርተን ወጥ፣
እየሸመለልን ሰማእት ልንውጥ፣
ከነፍሰ በላዎች አብረን ስንቀመጥ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ይገርማል! ሰው ከንቱ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ሰኔ ሁለት ሺ አስር ዓ.ም.

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. እውነቱ ይነገር says

    June 18, 2018 05:05 pm at 5:05 pm

    ወገኔ አቶ በላይነህ

    I would like to say thank you for your message. Please keep it up!

    ጥያቄ አለኝ???

    እውነተኛና ግልጽ መልስ ያለው ሰው በመረጃ አስደግፎ ይመልስልኝ!

    1)የኢትዮጵያውያን ዓይኖች መቼ ነው እንባቸው የሚደርቀው/የሚታበሰው?

    2)እየተባባሰ ለመጣው ለኢትዮጵያውያን የዘመናት እንባ ምክንያቱ/ምንጩ በእውነት ምንድነው?

    3)የውጭ ሃገር ወራሪ ጠላት ያላስለቀሰን እኛ ኢትዮጵያውያንን ለምንድነው የራሳችን ወገኖች የደም እንባ እንድናነባ የሚያደርጉን????

    4)አማራው በእውነት በተናጠል ኢትዮጵያንን በሙሉ በማን አለብኝነት ረግጦ በገፍ ገዝቷልን????

    5)በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በእውነት አንዱ ብሔረ ሰብ በሌላው ብሔረ ሰብ ሆነ ብሎ በደል ሠርቷል ወይስ እንደ ማንኛውም ሃገር የሕብረተሰብ እድገት-ታሪክ ሃይልና ጉልበት ያገኘው ጎሳና ሰፈርተኛ በነበረው ንቃተ ህሊና ላይ ተመስርቶ በሚፈጠር ግጭት የመጣ ማንነት ላይ የተመሰረተ ታሪክ?

    6)የሸዋ መሳፍንት ታሪክ ሲጠና ስንቱ አማራ ስንቱ ደግሞ ኦሮሞ እንደነበረ እስቲ በዳታ አስረዱኝ???

    7)በሃይለ ስላሴ፣ በደርግና በወያኔ መንግሥት ዘመናት ወቅት አመራር ላይ የነበረውን አካል በብሔረሰብ ደረጃ በመረጃ አስደግፋችሁ/አሁን ዛመኑ የመረጃ ጊዜ ስለሆነና በአሉባልታና በወሬ ወለደ ወሬ ይህን ትውልድ ማታለል ስለማይቻል/ እስቲ ንገሩን???

    ሁሉም የዘራውን ስለሚያጭድ እንጠንቀቅ?
    ወንድምን ከወንድሙ ጋር ማጋጨቱ ይብቃ?
    እውነት ነጻ ያወጣልና በጋራ
    ለእውነተኛ የጋራ ሃገርና
    መልካም ሥራ በእውነት እንነሳ?

    ወስብሐት ለእግዚአብሔር
    ሕዝባችንን ማስተዋል ይስጥልን!
    አሜን።

    እውነቱ ይነገር
    ከለሁበት

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule