• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እስክንድር ነጋ “ሃሳብን የመግለጽ መብት” ሽልማት

January 19, 2018 01:23 pm by Editor 3 Comments

በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ዘ ሄግ ከተማ ትናንት ምሽት በተካሄደው  የ2018  የፔን እና  የኦክስፋም ኖቪፕ – “ሃሳብን የመግለጽ መብት” አዋርድ ተሸላሚ ሆኗል። ሽልማቱን ያዘጋጁት ኦክስፋም ኖቪፕ እና ፔን ኢንተርናሽናል የተሰኙ አለማቀፍ ተቋማት ሲሆኑ ከእስክንድር ነጋ ጋር የአመቱ ተሸላሚ ሆና የተመረጠችው

ሚላግሮ ሶካሮ

የቬኒዙዌላዋ ጋዜጠኛ ሚላግሮ ሶካሮም ልብ የሚነካ ንግግር አድርጋለች። እስክንድር ነጋ በስፍራው ተገኝቶ ሽልማቱን መቀበል ባይችልም ከእስር ቤት ሆኖ  የላከው I SHALL PERSEVERE (እኔ እጸናለሁ) የሚለው መልእክቱ በምሽቱ ዝግጅት ላይ ተነብቧል።

በጃዝ ሙዚቃ እና በግጥም የታጀበው ይህ የስነጽሁፍ እና የሽልማት ዝግጅት እጅግ ደማቅ ነበር።

ሄግ ትያትር በተዘጋጀው በዚህ አለም ዓቀፍ የስነ ጽሁፍ ምሽት መክፈቻ ላይ የከተማዋ ከንቲባ – የኦክስፋም ኖቪፕ እና ፔን ኢንተርናሽናል ፕሬዚዳንቶች በመገኘት ስለ ፕሬስ አፈና ንግግር አድርገዋል። ጋዜጠኛ እስክንድር ለዚህ ሽልማት የበቃው በከፍተኛ አፈና እና ስቃይ ውስጥ ሆኖ ለፕሬስ ነጻነት በከፈለው ዋጋ እንደሆነ የፔን ኢንተርናሽናል ፕሬዚዳንት ሚስ ጃኒፈር ክሌመንት ተናግረዋል።

የኮክስፋም ኖቪፕ ፕሬዝዳንት ሚስ ፋራ ካሪሚም እስክንድር ነጋ በከፍተኛ ተጽእኖ ውስጥ ሆኖ ሃሳቡን በመግለጹ መታሰሩን ገልሰው – ለእስክንድር እና እንደ እስክንድር ላሉ የፕሬስ ነጻነት ተፋላሚዎች ትልቅ ክብር እንደሚሰጡዋቸው ተናግረዋል።

በሽብር ተወንጅሎ 18 አመታት የተፈረደበት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የዓለም አቀፍ ሽልማት ሲያገኝ ይህ የመጀመርያው አይደለም። በከፍተኛ ተጽእኖ ውስጥ ሆኖ ሃሳቡን በመግለጹ እና በዚህም ለፍትህ አልባ እስር በመዳረጉ፤ እ.ኤ.አ. በ2011  የፔን አሜሪካ አዋርድ በኒውዮርክ ፤ በ2012 ፔን ባርባራ ጎልድስማን፤ በ 2014 ፔን ዋኒፍራ ጎልደን አዋርድ፤ በ2015 ፔን ካናዳ አዋርድ እንዲሁም  ሂዩመን ራይት ዋች ባዘጋጀው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ተሸላሚ መሆኑ የሚታወስ ነው።

የእስክንድር ባለቤት ሰርካለም ፋሲል ሽልማቱን በባለቤትዋ ስም እንድትቀበል ብትጠራም በአንዳንድ የጉዞ እክሎች ሄግ ላይ መገኝት አልቻለችም። ሰርካለም ከቨርጂንያ የላከችው ልብ የሚነካ መልእክት ግን በአዳራሹ ለታደመው ሕዝብ እንዲነበብ ተደርጋል። ከጫፍ እስከጫፍ ጢም ያለው በዚህ አዳራሽ ውስጥ በርካታ ሎሬቶች፤ አለም አቀፍ ደራሲያን እና ገጣሚዎች እንዲሁም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተገኝተዋል።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Social Tagged With: eprdf, eskinder, Milagros Socorro, Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 20, 2018 10:37 pm at 10:37 pm

    ሰዎች!!! እስክንድር ነጋን መልቀቅ ማለት እውጭ ያለውን ተቃዋሚ ሃይል ማጠናከር ማለት ነው። ባለበት ቢቆይ ለራሱም ይሁን ለቤተሰቡ ደህንነት እንጂ ጉዳት የለውም። የዶ/ር ብርሃኑ ነጋን ሃይል የበለጠ በጎረቤት ሃገር ማደራጀት ይሆናል። ሁላችንም የሃገራችንን ደህንነት እንፈልገዋለን። ሰላምም እንመኛለን።

    Reply
  2. Tadesse says

    January 22, 2018 03:33 pm at 3:33 pm

    Be honest,why should any one suffer for any thing,ye eskendir Nega ke esir melekek manenm aygodam,bezi yetegodanew beteley egna le netsanet yemnwagaw Tigrewoch nen,netsanet le zelealem.

    Reply
  3. Tadesse says

    January 22, 2018 04:03 pm at 4:03 pm

    I am so deeply sorry for what is done in the name of the people of Tigray.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule