• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ የሚያልቧት እንደዚህ ነው፤ “ገንዘብ ባለበት ጩኸት አለ”

September 12, 2024 02:30 am by Editor 3 Comments

የአገራችን “ሃብታሞች” ወግ ከፍቶ ውስጡን ላየው ያስደነግጣል። “ገንዘብ ባለበት ሁሉ ጩኸት አለ” የሚለው አባባል በተለይ በኢትዮጵያ እውነት እንደሆነ ማረጋገጫም ነው። ጎልጉል ባገኘው መረጃ መሠረት የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ሲጋልቡ የነበሩ አካላት፣ አሁን ላይ “ይህ ለምን ቀረብን?” ወይም “ገና ለገና ሊቀርብን ነው” በሚል ሥጋት አንድ ላይ አገር እየናጡ ነው።

ከዚህ ቀደም “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው” በሚል ርዕስ ስለ አዲሱ ማክሮ ኢኮኖሚክ ፖሊሲ ስንዘግብ ውሳኔው “በኢትዮጵያ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ሳይሆን አዲስ መጽሐፍ ነው፤ ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው፤ ከዚህ አኳያ ፖሊሲው እንከን የማይወጣለት ነው” በሚል አቶ ኤርሚያስ አመልጋን ጠቅሰን እንደነበር ይታወሳል።

ይህን ዘገባ ተከትሎ የአዲስ አበባ ተባባሪያችን ባገኘነው መረጃ የተደራጁ ወይም በደም የተገናኙ የባንኩን ክፍለ ኢኮኖሚ፣ የመንግሥትን የፋይናንስ ሥርዓትና የአገሪቱን የገንዘብ ዝውውር አንቀው እንዴት አድርገው እንደሚጋልቡት የሚያሳይ ነው።

ጉዳዩ እንደዚህ ነው፤ … ከላይ እንደተጠቀሰው፣ ደም ቆጥረው፣ አካባቢ ወስነው፣ ዝምድናና አምቻ ለክተው አንድ የተመረጠ ግለሰብን ወይም ነጋዴን ለማገዝ ይታቀዳል። መረጃው እንደሚያሳየው ዕቅዱ ሲታቀድ ለዚያ የተመረጠ ነጋዴ ወይም ያገር ልጅ ብር ይዋጣለትና መቶ ሚሊዮን ገደማ የሚገመት ንብረት ወይም ቤቶች ወይም ሕንጻ እንዲገዛ ይደረጋል።

እንደ ጎልጉል መረጃ ሰዎች ብቻ ሳይሆን መንግሥትና ለባንኮች አሠራር ቅርብ የሆኑ በተደጋጋሚ እንደሚሉት ዘርፉ በሰፈር፣ በአካባቢ፣ በዘርና በክልል የታጠረ በዘመናዊ ዓለም ዘመናዊ አሠራርን በዘርና ደም ቀብቶ የሚንቀሳቀስ ኋላ ቀር የቤተሰብ ማኅበር ዓይነት ነው። ብዙዎች እንደሚሉት አብዛኞቹ ባንኮች በቅርቡ ዕጣ ፈንታቸው መደርመስ እንደሆነ የሚናገሩትም በዚሁ የአፈጣጠራቸውና የአሠራራቸው ባህርይ መነሻነት ትክክለኛ ባንኮች ወደ አገር ቤት ሲገቡ ተወዳዳሪ ሊሆኑ ስለማይችሉ ነው። ይህ እንደሚሆን በድፍረት የሚናገሩ ወገኖች በቢሊዮን የሚገመት ገንዘብ በጣት ለሚቆጠሩ ባለሃብቶች ብድሩን በማይመጥን መያዣ አሁን ያሉት ባንኮች ማበደራቸውን አብነት ያደርጋሉ። ሌሎችም ምክንያቶች አሏቸው።

እናም በዚሁ የደም ወይም የዘር ወይም የአምቻ ቆጠራ ንብረት የተገዛለት “ታዳጊ ባለሃብት” ያንን መቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ንብረት አስይዞ መቶ ሚሊዮን ብር ከባንክ እንዲበደር የባንኮቹ አፈጠጠር ጭምር ስለሚፈቅድ በዕቅዱ መሠረት ይበደራል።

የብድሩ ሒደት በድል ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የተበደረውን ብር ሌላ ባንክ ቆልፎ ያስቀምጥና በዓመት አስራ አራት ሚሊዮን ብር ወለድ ይቀበልበታል። አስቡት ቅጠል ሳይበጥስ፣ አንድ ብር ግብር ሳያስገባ አስራ አራት ሚሊዮን ብር ቋቱ ይከታል። ይህ የመጀመሪያውና ቀላሉ የሃብት መሰብሰቢያ መንደርደሪያ ነው። ሲያዩት ሕጋዊ ነው።

የመጀመሪያውን ዕቅድ ካሳኩ በኋላ ወደ ቀጣዩ ይዛወራሉ። መረጃውን ያደረሱት ሕግና አሠራር ጠቅሰው እንደሚሉት አንድ ነጋዴ መቶ ሚሊዮን ብር ካለው እና አስመጪ ከሆነ በዓመት ስድስት መቶ ሺህ ዶላር ከባንክ እንዲወስድ ይፈቀድለታል። በዚሁ አሠራር መሠረት ዶላሩን ለመውሰድ የአስመጪ ፈቃድ ያወጣና ትንሽ ዕቃ ከውጭ በማስመጣት የስድስት መቶሺ ዶላር ፍቃዱን ይረከባል።

በዓመት 600 ሺህ ዶላር የሚያስገኘው ፈቃድ ታዳጊው ባለሃብት እጅ ሲገባ “እልል በቅምጤ” ይዘፈናል። ከዚያም ከባንኩና ከሌላ አነስተኛ አስመጪዎች ጋር በመነጋገር ዶላሩን እያወጣ በጥቁር ገበያ ዋጋ ይሸጥላቸዋል። በዚሁ ሕጋዊ ፈቃድ ሕግን እየጨፈለቀ፣ ለባንኩ ኃላፊዎች ጉቦ በመክፈል ንግዱ ይከናወናል። በዚሁ አግባብ በትንሹ እስከ ሠላሳ ሚሊዮን ብር ያገኝበታል።

አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ሰሞኑን ሲናገር እንደነበረው አስመጪዎች ከባንኮች ዶላር የሚገዙበት ዋጋ ከጥቁር ገበያው ዋጋ በላይ ነው፤ ምክንያቱም ከእያንዳንዱ ዶላር በትንሹ 50 ብር በትርፍ ይታሰብበታል ብሎ ነበር። በመሆኑም ይህ 600 ሺህ የተፈቀደለት “ነጋዴ” ከባንኩ ኃላፊዎች ጋር “በመነጋገር” ለእነርሱ የደንቡን አድርሶ አንዱን ዶላር ውጪ አውጥቶ ሲሸጠው ቢያንስ 50 ብር ያተርፍበታል።

ይህ “ወጠጤ” ባለሃብት “ማን ነው፣ ከየት አመጣው” የሚለው ጉምጉምታ በወጉ ሳይሰማ ይህ ሰው፣ ምንም ሥራ ሳይሠራ ገቢው ሽቅብ ይምዘገዘጋል። በዓመት የሚያገኘው ገቢ ከላይ በተገለጸው አግባብ ከአንድ ባንክ የተበደረውን ብድር ሌላ ባንክ ወስዶ በመቀርቀር ብቻ በወለድ ከሚያገኘው አስራ አራት ሚሊዮን ብር ጋር ተደምሮ አርባ አራት ሚሊዮን ብር ይሆንለታል።

በመቶ ሚሊዮን የገዛው ንብረት እየተከራየ በሚሊዮን የሚቆጠር ገቢ ያስገባለታል ቢባል እና ይህንን ለኑሮው፤ “ለወጪዎቹ” መሸፈኛ ያውለዋል ብለን ብንወስድና የተወሰነ ትርፍ ብናስብ ባጠቃላይ በዓመት ይህ ወጠጤ ባለሃብት እስከ ሃምሳ ሚሊዮን ብር ምንም ሳይለፋ ገቢ ማግኘት እንደሚችል የአዲስ አበባ ተባባሪያችን መረጃ ያስረዳል።

በመዋጮ ብር ንብረት ተገዝቶለት ከባንክ ለተበደረው መቶ ሚሊዮን ብር በየዓመቱ ሃያ ሚሊዮን አካባቢ ወለድ ጨምሮ መክፈል እንዳለበት ውል ያስገድደዋል። ይህ ሲቀነስ ሰላሳ ሚሊዮን አካባቢ እጁ ላይ ይቀራል። ሲጀምር ዕቅድና ሂሳብ ተሰልቶ መቶ ሚሊዮን ላበደሩት ዘመዶቹ ከሰላሳ ሚሊዮኑ ቢያንስ ሃያውን ቢከፍላቸው እስከ አምስት ዓመት ውስጥ ዕዳውን ይዘጋል።

ከዚያ በኋላ በያመቱ ቢያንስ ሃምሳ ሚሊዮን ብር ምንም ሳይሠራ እየሰበሰበ በተራው ቤተሰቡን በተመሳሳይ ያደራጃል። ንብረት እየገዛ ያገላብጣል። ዋጋ እንዳሻቸው ከሚሰቅሉት ማኅበርተኞች ጋር አብሮ ኑሮ ያጦዛል። የጥቁር ገበያውን በተፈለገው ዋጋ ያንረዋል፤ በኮንትሮባንድ ንግድ በቀላሉ ይሰማራል፤ ሌሎችም ለአገር የሚያሰጉ “የንግድ ተግባራትን” ይፈጽማል።

ብር በማገላበጥ ብቻ ግብር የማይከፍልበት፣ ቫት የሌለው ትርፍ እየሰበሰበ የሚኖረው ወጠጤ ባለሃብት፣ ራሱን የመከላከያ ሚዲያም እንደሁኔታው ይከፍታል፤ የዩትዩብ ወሬኛ፣ የፌስቡክ ለፍላፊ፣ የቲክቶክ አርበኛ በያይነቱ ያሰማራል፤ ከዚህ ሁሉ በነጻ ከመጣ ትርፍ ፍርፋሪውን ለሚጮኹለት ቢወረውር ጥቅሙን እያሰበ ነው። ታላላቆቹ ሠራዊት ስለሚያደራጁ እሱ የሳይበር አውሬ ያረባና እንዳሻው የሚዘርፍበት መንገድ እንዳይነካ በደቦ ውግዘት እንዲሰራጭ እያደረገ አገር ያተራምሳል። አገር ስትበላ የኖረችውና የሚዲያው ሁሉ ቅጥ የጠፋበት ጩኸት መልኩ ይህ ነው ።

ይህ የመቶ ሚሊዮን ብር ስሌት ነው። ብሩ ባደገ ቁጥር ገቢው እንዴት እንደሚያድግ ማስላት ዘረፋውን ወገግ አድርጎ ያሳያል። እዚህ ላይ በሩጫ አዘጋጅነት ተመዝገበው ለካኔቴራ ማስመጫ በሚል ዶላር ወስደው ከአደይ አበባ ጨርቃጨርቅ ጥብቆ የሚገዙና የማስታወቂያ ገቢ የሚሰበስቡትንም ሲከፈቱ የሚያሳፍሩ አካላት እንዳሉ ማሰብ እንደሚያሻ፣ ወደፊትም አስፈላጊ ሲሆን ዝርዝር የሚቀርብበት ጉዳይ እንደሆነ የዜናው ባለቤቶች ይገልጻሉ።

ላለፉት ሁለት ዓመታት ገበያው ላይ የተረጨውን ብር በዲጂታል ግብይትና ብድር ላይ ሸምቀቆ በማበጀት ሲሰበስብ የኖረው መንግሥት አዲሱን የዶላር ፖሊሲ ማውጣቱን ተከትሎ በሚከፍሏቸው ሚዲያዎቻቸው አማካይነት በደቦ ጫጫታ ያስነሱት ጥቅማቸው ስለሚነካ ለመሆኑ ከላይ የሰፈረው ሕገወጥ የሃብት መሰብሰቢያ መንገድ በራሱ አንድ በቂ ማሳያ ነው።

ያለ አንዳች ድካም ይህንን ያህል ንጹህ ትርፍ ሲያግበሰብሱ የኖሩት ወጠጤ ሃብታሞች ባደራጇቸው ሚዲያዎችና የማኅበራዊ ገጾች ሽብር ሲያስነሱ ነገሩ ያልገባቸው የዝርፊያው ሰለባዎች አብረው እንዲጮሁ አድርገዋል። ይህንን ለመተግበር ደግሞ የዘር፣ የሃይማኖት፣ የብሔር፣ … ማንኛውንም ማንነት እስከ ግድያ ድረስ በመፈጸም ሕዝብ እንዲቆጣ፣ ሥርዓት እንዲናጋ፣ … የተገኘውን መንገድ ሁሉ ይጠቀማሉ፤ ጉዳዩ የሚሊዮኖች ጨዋታ መሆኑን ልብ ይሏል።   

የገንዘብ ፖሊሲው የወጣ ሰሞን ለዚህ ነው ስለ ኢኮኖሚው ጉዳይ አንዳች እውቀት የሌላቸው ተቀላቢ ሚዲያዎቻቸው ያለ ሃፍረት የማያውቁትን ጉዳይ አንሰተው ትንታኔ ለመስጠት ሲውተረተሩ የታየውና እየታየ ያለው “በሕዝብ ቁስል እንጨት ስደድበት” በሚለው ከከርሳቸው የሚመነጭ ብሒል መነሻ እንደሆነ ጉዳዩን በትነው የሚያውቁት አስረድተዋል።

እነዚህ ዓይነ ደረቆች ውሸቱን እውነት አድርገው ሕዝቡን ያወዛግቡታል። ሆድ እንዲብሰው፣ እንዲቆጣና እነሱ ከርሳቸው እንዳይጎድል አስበው የሚጠምቁትን ሤራ እንዲጋት ያስገድዱታል። ይህን የተረዱ እንደሚሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዋና ደረጃ የተጠሉት በፖለቲከኞች ሳይሆን በወጠጤና ደንዳና የዘረፋ ተዋናይ ሌባ “ሃብታሞች” ነው።

በዚህ መልኩ ዋጋ አንረው፣ ኑሮውን አጉነው፣ ግሽበት እንዲያይል ምክንያት ሆነው የሰበሰቡትን ሃብት ወደ ቋሚ ንብረት በመለወጥ ዘመቻ መረባረባቸው በአገሪቱ የቤትና፣ የመሬት ዋጋ በብርሃን ፍጥነት እንዲተኮስ አደረገ። የታየውን ይህን አስደንጋጭ የዋጋ ንረት በመረጃ አስደግፈው የሚናገሩት የዘርፉ ምሥጢር አዋቂዎች እንደሚሉት፣ አብዛኞቹ የሪል ስቴት አልሚዎች አሁን ላይ በዩቲዩቡ የሚጮሁትና በየቴሌግራሙ ቻናል ማስታወቂያ የሚያወጡት ያላሰቡት ስለገጠማቸውና ሃያ በመቶ ካሽ ከፍሎ የሚገዛ ደንበኛ ባለማግኘታቸው ነው።

ያከማቹትን ንብረት ሕንጻ ጭምር ሸጠው ብድራቸውን ለመክፈል ቢፈልጉም ገዢ ማግኘት አልቻሉም። አሁን ላይ የሕንጻና የቤት ዋጋ እያሽቆለቆለ መሆኑን የሚገልጹት የመረጃው ሰዎች፣ በቅርቡ በአንዳንድ ሪል ስቴቶች አካባቢ ባንኮች የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ እንደሚያወጡ ፍንጭ ሰጥተዋል።

ከዚህ በፊት ብድር የማሸጋሸጊያ ዕድል ስድስት ጊዜ ነበር፤ በአዲሱ ፖሊሲ ግን ወደ ሁለት ወርዷል፤ በርካታዎቹ ባለሃብቶች ደግሞ ስድስቱንም ቀርጥፈውታል። ከዚህ በኋላ በግድ ብድራቸውን መክፈል ይጠበቅባቸዋል።

መፍትሔውም ሁለት ነው፤ አንደኛው የብር ዋጋ ይወድቃል ብለው ብራቸውን ወደ ዶላር እየቀየሩ ያስቀመጡትን ወደ ብር እየቀየሩ መጠቀም ነው። ይህ በገበያው ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን የዶላር መጠን በመጨመር የምንዛሬ መጠኑን ዝቅ ሊያደርግ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። ካልሆነም ሁለተኛው “አማራጭ” ንብረታቸውን በሐራጅ እንዲሸጥ መፍቀድ ነው። ከዚህ አኳያ በመጪው ዓመት (2017) በርካታ የሐራጅ ሽያጭ የሚታይበት ዓመት ይሆናል ተብሎ ተገምቷል።

“ብር የሌለበት ፖለቲካ በስልሳዎቹ ቀረ” የሚሉ ወገኖች የኢትዮጵያን ሁኔታ ከቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ጋር ያገናኙታል። የኬኔዲ ጠላቶች ፖለቲከኞች ብቻ አልነበሩም። ነገር ግን በጠላቶቻቸው ሽፋኑ ፖለቲካ ተደርጎ ቀረበ እንጂ። የማፊያ ሰዎች፣ የዕጽ አስተላላፊዎች፣ አሻጥረኛ ትልልቅ ነጋዴዎች፣ የቬይትናምን ጦርነት አስቆማለሁ በማለታቸው ያኮረፉና የወታደራዊ ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ሰዎች፣ ወዘተ ከፖለቲከኞቹ ውጪ ተጠቃሾች ነበሩ።

ኬኔዲ ወንድማቸውን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አድርገው የማፊያና የውንብድና ሥራዎችን የሚሠሩ ሁሉ ወደ ሕግ አግባብ በማምጣት ኔትዎርካቸውን መበጣጠስ ጀምረው ነበር። የተቀናጀ የወንጀል ተግባራትን ይፈጽሙ የነበሩት የኩባ ማፊያዎች በኬኔዲ አስተዳደር ከፍተኛ ጥቃት እየተሰነዘረባቸውና እየፈራረሱ የነበረ መሆኑ ሌላው ተጠቃሽ ነው። እነዚህ ሁሉ ጥቅማቸው የተነካባቸው የኬኔዲ ጠላቶች ሆኑ፤ እንዳሁኑ የማኅበራዊ ሚዲያ በዚያን ዘመን ቢኖር ምናልባት ኬኔዲ በጥይት ሳይሆን በፌስቡክና በዩትዩብ “ጥይቶች” ይገደሉ ነበር።

በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተከሰተውም ከዚህ በብዙ አይለይም። እጅግ ግፈኛ፣ ዘረኛ፣ ከፋፋይ፣ ወንበዴና መሠሪ በሆነው የትህነግ 30 የሰቆቃ ዓመታት በመንግሥት ተቋማት ሕግ ወጥቶላቸው ረቂቅ ግፎች ሲፈጸሙ እንዳልነበር ትህነግ ከሥልጣን ከተወገደ በኋላ በተለያዩ እንደ አሸን በፈሉ ቡድኖች እጅግ ሰቅጣጭ እና ሕዝብ ስሜት ውስጥ እንዲገባ ታይተውና ተሰምተው የማይታወቁ ወንጀሎች ሲፈጸሙ ለመመልከት በቃን።

በወያኔ የግፍ አገዛዝ ዘመን ታይተውና ተሰምተው እንዲሁም ተከስተው የማያውቁ ሰቆቃዎች ወያኔ ከሥልጣን ከለቀቀ በኋላ ልክ ጊዜ ተሞልቶላቸው እንደተቀበሩ ፈንጂዎች ለምን በየቦታው ፈነዳዱ? ለዚህ ጥያቄ አሁን መልስ አንሰጥም፤ ግን የወንበዴው ትህነግ አመራሮች በየጊዜው ሲሉ የነበሩትን ለማስታወስ እንጠቅሳለን፤ “እኛ ከሥልጣን ከለቀቅን አገሪቷ ትፈራርሳለች፤ ትፈነዳለች” እያሉ ነበር ሲያስፈራሩን የነበረው።

ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ ባወጣው ዘገባ መሠረት እኤአ በ2022/2023 በነበረው ዓመት የባንኩ ኢንዱስትሪ ለባለሃብቶች ያበደረው 1.9 ትሪሊዮን ብር ነበር። ከዚህ ብር ውስጥ ሩብ ያህሉን አካባቢ ማለትም 23.5 በመቶውን የተበደሩት 10 (አስር) ግለሰቦች ብቻ ሲሆኑ የወሰዱት የብድር መጠንም 450 ቢሊዮን ብር ነው። በሌላ አነጋገር እያንዳንዳቸው በነፍስወከፍ 45 ቢሊዮን ብር አካባቢ ወስደዋል ማለት ነው። ገንዘብ ባለበት ጩኸት አለ፤ በየዕለቱ በየማኅበራዊ ሚዲያ የሚበተነው መርዝ ባዶ ፖለቲካ አይደለም፤ እያንዳንዱ የማኅበራዊ ሚዲያ ፖስት፣ ወሬ፣ አሉባልታ፣ የሐሰት ዜና፣ ወዘተ አገር የታለበችበት የደም ገንዘብ ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, Money Laundering, Nationa Bank of Ethiopia, NBE, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tasserw Assefa says

    September 9, 2024 03:53 pm at 3:53 pm

    መሬቱን አሲዞ የተበደረውን ሌላ ባንክ እስቀምጦ ወለድ የሚበላው ሰው፣ ላበደርው ባንክ እሱም በተራው ወለድ ይከፍላል፣ ባንኮች ላስቀማጮች የሚከፍሉት ወለድ ላብደሩት የሚጠይቁት ወለድ ስለሚበልጥ፣ እንዴት ሊያተርፍ ይችላል?

    Reply
    • Editor says

      September 11, 2024 08:57 am at 8:57 am

      Tasserw Assefa
      ለአስተያየቱ እናመሰግናለን፤ ያልኸውን ግን ጠቅሰን ጽፈናል፤ ደግመህ አንብበው።

      Reply
      • ጥላሁን ነኝ says

        November 28, 2024 12:07 pm at 12:07 pm

        ለትንተናችሁ እና ለዘገባችሁ በጣም አመሰግናለሁ። በተለይ ባንኮች “ለባለሃብቶች ያበደረው 1.9 ትሪሊዮን ብር ነበር። ከዚህ ብር ውስጥ ሩብ ያህሉን አካባቢ ማለትም 23.5 በመቶውን የተበደሩት 10 (አስር) ግለሰቦች ብቻ ሲሆኑ የወሰዱት የብድር መጠንም 450 ቢሊዮን ብር ነው” የሚለው አሃዝ አስደንጋጭ እና ክትትል የሚያስፈልገው ነው። እንደዚህ አይነት በአሃዝ ላይ የተሞረክዘ ጥናታዊ ዘገባ ጠቃሚ ስለሆነ በርትታችሁ ቀጥሉበት።

        ከላይ አቶ ጣሰው ያለው ግን የሚገፋ (brushed off) የሚደረግ ሳይሆን፣ መልስ የሚያስፈልገው ነው። የባንኮች መሰረታዊ ግብይት (fundamental business) የሚከነወነው፤ ተቀማጭ በመሰብሰብ እና ብድር በማበደር ነው (ሌሎች ተያያዥ ንግዶችን ተወት አድርገን)። በዚህ ግብይት ላይ ደግሞ ባንኮች የሚያተርፉት፤ ለተቀማጭ የሚከፍሉት ወለድ ለተበዳሪዎች ከሚያስከፍሉት ወለድ በጣም ሲያንስ ነው። ለተቀማጭ ከሚከፍሉት በጣም የበለጠ ወልድ ተበዳሪን ሲያስከፍሉ ነው። ታዲያ የጥናታችሁ ተብዳሪ በተበደረው 100 ሚሊዮን ላይ፣ በዐመት 14 ሚሊዮን ወለድ (14%) ካገኘ አበዳሪው ባንክ ለተመጣጣኝ ብድር የሚያስክፍለው ከ 18% በላይ መሆን አለበት። ይህ ደግሞ ብሩን ቁጭ ካረገው ኪሳራ እንጂ ትርፍ አያመጣም። ትርፍ ሊሆን የሚችልበት 3 መንገዶች አሉ፡
        1) ብሩን ያስቀመጠበት ባንክ ላስቀማጮች የሚከፍለው ወለድ (14%ቱ) አበዳሪው ባንክ ለተበዳሪዎች ከሚያስከፍለው ወለድ የበለጠ ከሆነ።
        2) ብድሩ ከወለድ ነጻ፤ የሆነ የእፎይታ ጊዜ (Grace period) ካለው ወይም
        3) በብድሩ የመጀመሪያ እድሜ ላይ ብድሩ በጣም አነስተኛ (5% ወይም ያነሰ) ወለድ የምክፈያ የእፎይታ ጊዜ ካለው ብቻ ነው። አይመስላችሁም???

        Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule