• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር ለፍርድ ቤቱ፤ “ጉዳዩ ፖለቲካዊ ነው፤ የሚበጀው ቁጭ ብሎ መነጋገር ነው” አለ

July 16, 2020 11:55 pm by Editor Leave a Comment

ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ተጠርጥሮ በእስር ላይ የሚገኘው ጃዋር ሲራጅ መሃመድ የተከሰሰበት ጉዳይ “ፖለቲካዊ ነው፤ ይህ ችግር የሚፈታው ቁጭ ብሎ በመወያየት ነው” በማለት ለፍርድ ቤቱ ተናገረ።

የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ከጃዋር ጋር አብሮ በቀለ ገርባን ጨምሮ ሌሎችም ተጠርጣሪዎች ሐሙስ ዕለት ነው ልደታ ምድብ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እና አራዳ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት።

ይህንንም ተከትሎ የጃዋር ጠበቃ ደንበኛቸው በዋስ ከእስር ቤት ውጪ ሆኖ ጉዳዩን መከታተል እንዲችል እንዲፈቀድለት ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ያቀረበውን የተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጥያቄ ተቀብሎታል።

በዚህ ጊዜ የተከሳሽ ጠበቆች ደንበኛቸው ምግብ ከቤተሰቡ የሚቀርብለት ቢሆንም፤ ግንኙነታቸው በርቀት በመሆኑ ባለበት ከርቀት አይቶ የመለየት ችግር ቤተሰቦቹን በቅርበት እንዲያገኝ እንዳልተፈቀደለት ለችሎቱ አቤት ብለዋል።

ፖሊስም ይህንን በተመለከተ በሰጠው ምላሽ ታሳሪዎችና ጠያቂዎች መካከል መቀራረብ እንዳይኖር የተደረገው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመቆጣጠር በወጣው ደንብ መሰረት መሆኑን ጠቅሶ ምላሽ ሰጥቷል።

በተጨማሪም ጃዋር ታስሮ የሚገኝበት ክፍል በቂ ብርሃን የሌለው መሆኑና መጸዳጃ ቤት የመጠቀም ችግርን በማንሳት ጠበቃው አቤቱታ ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም ደንበኛቸው ጥፋተኝነታቸው ገና ባልተረጋገጠበት ሁኔታ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ምስላቸው እየቀረበ ዘገባዎች እንደሚቀርቡና ፍርድ ቤቱም ይህንን እንዲያስቆም ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ለእስረኞች መጸዳጃ ቤትን በተመለከተና በማረፊያ ክፍሎች ውስጥ ያለውን ብርሃን በተመለከተ አስፈላጊውን ማስተካከያ እንዲያደርግ ያዘዘ ሲሆን፤ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ስለቀረበው አቤቱታም ጠበቆች ያሏቸውን ተቋማት በስም ለይተው ስላላቀረቡ አቤቱታውን ውድቅ አድርጎታል።

በዚህም መሰረት ፖሊስ ለምርመራ የጠየቀውን የ14 ቀናት ጊዜ ፈቅዶ ጉዳዩን ለመመልከት ሐምሌ 23/2012 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።

ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ቢቢሲ አማርኛ ሳይዘግበው ያለፈው ቁልፍ መረጃ ፍርድ ቤቱ በመጀመሪያው ችሎት ለፖሊስ በሰጠው ቀናት ምን ምርመራ እንዳደረገ የጠየቀው ነበር። የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድንም የሚከተለውን መረጃ ለፍርድ ቤቱ አሰምቷል፤

  • የድምጻዊ ሃጫሉን ግድያ ተከትሎ ተጠርጣሪው ጃዋር በአዲስ አበባና በኦሮሚያ የብሔርና የሃይማኖት የግጭት መቀስቀሱን ያስረዱ የ34 ምስክሮችን ቃል መቀበሉን፤
  • የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር የሃጫሉን አስከሬን ከቡራዩ ኬላ በመቀማት በከተማዋ ከነበሩት የጸጥታ ኃይላት ጋር የእርሱ የታጠቀ ቡድን ተኩስ መክፈቱን የመሰከሩ መኖራቸውና ቃላቸውን መቀበሉን፤
  • አስከሬኑ የምኒልክ ሃውልት ፈርሶ መቀበር አለበት በማለት ወደ ኦሮሚያ ብልጽግና ጽ/ቤት ያመራው የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር የሚመራው የታጠቀ ቡድን በከፈተው ተኩስ አንድ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አባል መገደሉን፣ ሦስት ደግሞ መቁሰላቸውን፤ ይህም በሰው 10 ምስክርና በፎረንሲክ ምርመራ ማረጋገጡን፤
  • በኦኤምኤን ሚዲያ በወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር የተጠራውን የዓመጽ ጥሪ ከብሮድካስት ሚዲያ ባለሥልጣን መቀበሉን፤
  • ከወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር እና ከቡድኑ 10 ክላሽ፣ 1 ቺቺ፣ 10 የተለያዩ ሽጉጦች፣ 9 የሬዲዮ መገናኛ፣ ሕጋዊ አለመሆናቸውን በሚመለከተው አካል ማረጋገጡን፤
  • የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር የሚያስተላልፋቸውን የወንጀል መልዕክቶችን ተከትሎ በአዲስ አበባ 14 ሰዎች እንዲሁም በኦሮሚ ክልል 167 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ ምርመራው ማረጋገጡን፤
  • በኦሮሚያ ክልል የወደመው ንብረት ለጊዜው ያልታወቀ ቢሆንም በአዲስ አበባ ግን ከ200 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን በምርመራው ማረጋገጡን፤
  • የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር የስልክ ልውውጡ ከግጭቱ ጋር የሚያሳየውን ተሳትፎ ምርመራው ማመላከቱን፤
  • ከወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር ቤት የተገኘው የሳተላይት መቀበያ ጨምሮ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ውጤቶች በባለሙያ ማስመርመርና የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር ከኦኤምኤን ጋር ያለውን ግንኙነት እንዲሁም አዲስ አበባ ውስጥ ብጥብጥ እንዲፈጠር ከሚሹ ኃይሎች ጋር ያለውን ግንኙነት በቀጣይ የሚሰራባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን፤
  • ግጭት በተከሰተባቸው ቦታዎች የተላኩት 14 ቡድኖች የሚያመጡትን መረጃ ውጤት በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ቡድኑ ጠቅሶ ሌሎች ግብረአበሮችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል መሆኑን

በመጥቀስ የምርመራ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው የጽሁፍ ሪፖርት አስታውቋል።    

ፍርድቤቱ ይህንን ከፖሊስ ከሰማ በኋላ የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር ሲራጅ መሐመድ እንዲናገር ተፈቅዶለት የተናገረው “የተተኮሰ ጥይትም ሆነ የሞተ ሰው የለም፤ ጉዳዩ ድራማ ነው፤ የሚበጀው ቁጭ ብሎ መነጋገር ነው፤ የአርቲስቱን አስከሬን ወደ አምቦ ለመውሰድ መንገድ ስለተዘጋጋ ወደኋላ ተመለስን እንጂ ሌላ ተልዕኮ አልነበረንም፤ ጉዳዩ ፖለቲካዊ ነው፤ ይህ ችግር የሚፈተታው በፖለቲካዊ ውይይት ነው” ብሏል።

በሌላ በኩል ከእነ በቀለ ገርባ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራዳ ተረኛ ወንጀል ችሎት ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሊሰጥ ይገባል አይገባም በሚለው ላይ ፍርድ ቤቱ ሐሙስ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ባሳለፍነው ሰኞ ሐምሌ 6፣ 2012 ዓ.ም ከወንጀል ተጠርጣሪው በቀለ ገርባ ጋር በተያያዘ መርማሪ ፖሊስ በቀለ በቁጥጥር ሥር ከመዋሉ በፊት በኦሮሚያ ክልል ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ስልክ በመደወል ሁከት እንዲቀሰቀስና ነዋሪዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የመንግሥት ደጋፊዎች ላይም ጥቃት እንዲፈጸም ትዕዛዝ ያስተላለፈበት የስልክ ልውውጥ በማስረጃ መልክ ማግኘቱን ፖሊስ አስታውቋል።

ከዚያም ባለፈ በወንጀል ተጠርጣሪው በቀለ ገርባ ቤት ባደረገው ብረበራ ሁለት ሽጉጦች መገኘታቸውን እና ፍቃድ ይኑራቸው አይኑራቸው ገና እያጣራ መሆኑን መርማሪ ፖሊስ ማስታወቁም ይታወሳል።

የወንጀል ተጠርጣሪው በቀለ ገርባ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የለኝም ለቅሶ ለመድረስ በአሸዋ ሜዳ ስሄድ መንገድ በመዘጋቱ ነው የተመለስኩት እና ወደ ኦሮሞ ባህል ማዕከል ያቀናሁት ቢልም፤ መርማሪ ፖሊስ ግን አስክሬን በኃይል ቀምቶ መስቀል አደባባይ ለ10 ቀናት አቆይቶ ህዝብን በማስለቀስና ብጥብጥ ለመፍጠር አቅዶ የፈጸው መሆኑን በምላሹ ጠቅሷል።

የወንጀል ተጠርጣሪው በቀለ ገርባ ሁለት ልጆች ጋር በተያያዘ መርማሪ ፖሊስ የአባታቸውን ትዕዛዝ ተቀብለው ሁከት ሲያነሳሱ ነው በቁጥጥር ሥር ያዋልኳቸው ያለ ሲሆን፥ ጠበቆቻቸው ደግሞ ልጆቹ ለቅሶ ለመድረስ ከአባታቸው ጋር አብረው ስለተገኙ ብቻ ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት ብሏል።

በኤግዚቢትነት ከተያዙት እቃዎች ውስጥ ወደማስረጃነት የሚቀየሩ ጉዳዮችን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስታውቋል።

ሰባት መርማሪዎች በተለያዩ የአሮሚያ ክልል አካባቢዎች ጉዳት የደረሰባቸው የሰውና የንብረት ጉዳት መጠንን ለመመርመርና ማስረጃ ለመሰብሰብ በማቅናታቸው እነርሱ ይዘው የሚመለሱትንና ሌሎች ማስረጃዎችን ለማሰባሰበ 14 ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ይሰጠኝ ሲል መርማሪ ፖሊስ መጠየቁም ይታወሳል።

ጉዳዮን የተመለከተው ችሎትም የወንጀል ተጠርጣሪው በቀለ ገርባ ላይ 11 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሰጥቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሌላኛው የወንጀል ተጠርጣሪው እስክንድር ነጋ አዲስ አበባ ውስጥ ብጥብጥ እንዲቀሰቀስ በማድረግ፣ ሰዎችን በማሰማራት፣ ገንዘብ በማሰራጨት፣ የዓመጽ ቅስቀሳ በማድረግና ይህንንም ተከትሎ ለሞቱን 14 ሰዎች ተጠያቂ መሆኑን ፖሊስ አመልክቷል።

የወንጀል ተጠርጣሪው ጃዋር ሲራጅ መሃመድ ከፍርድ ሥርዓቱ ይልቅ “መፍትሔው ቁጭ ብሎ መወያየት ነው” በማለት ያቀረበውን የመፍትሔ ሃሳብ ፍርድቤቱ ምላሽም እንኳ ሳይሰጥበት ወደ ማረፊያ ክፍሉ እንዲወሰዱ በማድረግ ችሎቱ አጠናቅቋል።

ከአገር ውስጥ ሚዲያዎች በዘገቡት ቪዲዮ ላይ የወንጀል ተጠርጣሪዎቹ በቀለ ገርባ እና ጃዋር ሲራጅ መሃመድ በብረት ለበስ ወታደራዊ መኪና ተጭነው ተወስደዋል።

(ዜናውን ያጠናቀርነው ከኢቲቪ፣ ከአዲስ ሚዲያ፣ ከቢቢበሲ አማርኛ ነበር)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, News, Right Column Tagged With: bekele gerba, chilot, court, jawar, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule