• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አስመራ ላይ የሙዚቃ ድግስ ማቅረብ – የቴዲ ተስፋ!

December 28, 2017 11:55 pm by Editor 2 Comments

ለዓመታት በአገር ውስጥ የሙዚቃ ድግስ (ኮንሰርት) እንዳያሳይ የታገደው ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አስመራ ላይ የሙዚቃ ድግስ ለማቅረብ ተስፋ እንደሚያደርግ ተናገረ። ችግሮቻችንን አራግፈን ወደፊት መጓዝ አለብን ብሏል።

ዴይሊ ሜይል አዣንስ ፍራንስ ፕሬስን ጠቅሶ እንደዘገበው በእርሱ ላይ እየደረሰ ያለው ነገር እንዳለ ሆኖ ቴዲ “በኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት ላይ” ትኩረት ማድረግ መቀጠሉን ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤቱ ዘና ባለ ሁኔታ መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል።

የልጅነት ዘመኑን በማስታወስ ቴዲ ሲናገር፤ “ልጅ ሆኜ እንደ አንድ አገር ስንኖር አስታውሳለሁ፤ አንድ የምናውቃት አገር ኢትዮጵያ የምትባል ነበረች፤ አሁን በዚህ ዘመን ግን የምንታወቀው በዘራችን ነው፤ ይህ ደግሞ እጅግ አደገኛ እየሆነ መጥቷል” ብሏል።

ህወሓት በቴዲ የጥበብ ሥራዎች ላይ ማዕቀብ በመጣሉ በተለይ ተደናቂነትን ያገኘው “ኢትዮጵያ” የተሰኘው አዲሱ አልበሙም ሆነ ቀደምት ሥራዎቹ እንደሌሎቹ ባለሙያዎች ህወሓት በተቆጣጠረው ሚዲያ ላይ አይሰሙም። አንዳንዶች ይህንን አስመልክተው ሲናገሩ፤ የቴዲ 17 መርፌ ሙዚቃም ይሁን እቴጌ ወይም ባልደራሱ ወይም ማር እስከ ጧፍ ሁሉም ህወሓትን ያስበረግጉታል።

“ጥቁር ሰው” የተሰኘው አልበሙ ህወሓት ከፈጠረው የዘር ፖለቲካ ጋር ተያይዞ በኦሮሞ ብሔረተኞች ዘንድ ስሙ እንዲጠለሽ ብዙ ተሠርቶበታል። እነ ጃዋር መሐመድ ያደረጉት የበቀል እርምጃ ከህወሓት እኩይ ተግባር ባልተናነሰ መልኩ የቴዲ ሥራ ለሕዝብ እንዳይቀርብ ብዙ እንቅፋትን ፈጥረው አልፈዋል። የቴዲ ኮንሰርት ስፖንሰር አድራጊ የነበረው ሃይኒከን ቢራ በዚህ ዘመቻ ምክንያት ራሱን ማግለሉ የሚታወስ ነው። (ይህንን አስመልክቶ ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ አትሞት የነበረውን ዘገባ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)።

ቤቱ ግድግዳ ላይ በተሰቀለ የምኒልክ ጎራዴ አጠገብ ተቀምጦ ቴዲ ስለተካሄደበት ይህን መሰሉ ህገወጥ ዘመቻ ይህንን ይላል፤ “ስለ ኢትዮጵያ ታሪክና ቀደምት ነገሥታት አሉታዊ አመለካከት ያላቸው ቡድኖች ሊኖሩ ይችላሉ። አመለካከታቸውን ባከብርም የኔን አመለካከት መውደዳቸውም ወይም አለመውደዳቸው እውነቱን አይለውጠውም።”

በሙስሊምና ክርስቲያን መካከል ሰላምና ፍቅር፣ መግባባት እንዲኖር የሚያዜመው ቴዲ ከህወሓት ሌላ በርካታ ነቃፊና ስም አጥፊዎችም በዘመኑ አላጣም። በአድናቂዎቹ ሴቶች ጡት ላይ ይፈርማል በማለት ስለ እርሱ ሲናገሩ ለነበሩ የሰጠው ምላሽ በኢትዮጵያ በውጭ አድናቆትን እንዳተረፈለት ዴይሊ ሜይል ዘግቧል። እንደ ኢትዮጵያዊ ይህንን ዓይነት ነገር ፈጽሞ ሊያደርገው እንደማይችል ነው ቴዲ የተናገረው። ይህንን በመደገፍ ይመስላል የአፍሮ ኤፍ ኤም ፕሮግራም ኃላፊ የሆነው ኢዮኤል ሰሎሞን “(ቴዲ) የሚሰብከው የሚኖረውን ነው፤ እኛ እንወደዋለን፤ ኢትዮጵያውያን ይወዱታል” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።

“ኢትዮጵያ” አልበሙ የምረቃ ፕሮግራም የተቋረጠበት ቴዲ አፍሮ፤ ለአዲሱ ዓመት (2010) ያቀደው ኮንሰርትም ተከልክሏል። አሁንም ግን ተስፋ ሳይቆርጥ ለገና ኮንሰርት ለማቅረብ ያቀረበው ጥያቄ እንዲፀድቅለት እየጠበቀ ነው። ይህ ሁሉ ሆኖ በሙያውና በሙዚቃው ስለ ኢትዮጵያ ከመሥራት ምንም እንደማያዳክመው ተናግሯል።

የቴዲ ምኞት እና ተስፋ ግን በዚህ ብቻ የተገታ አይደለም፤ እስከ አስመራ የዘለቀ ነው። እዚያ የሙዚቃ ድግስ ለማቅረብ ተስፋ ያደርጋል። “የሚያስፈልገን የፍቅር፣ የሰላም፣ የይቅርባይነት መንፈስ ነው። ምክንያቱም አሁን ያሉት ችግሮች የታሪክ ቅሬታዎች ያመጧቸው ውጤቶች ናቸው። ልናራግፋቸው፤ ወደኋላ ትተናቸው ልንሄድ ይገባል” ይላል ቴዲ አፍሮ።

ዘገባው ከነፎቶው የተጠናቀረው ከዴይሊሜይል ድረገጽ ነው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Social Tagged With: afro, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, Middle Column, teddy, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 2, 2018 03:20 am at 3:20 am

    ሰዎች!! ቴዲ አፍሮ ስለ ኢትዮጵያዊነት ያትታል፣ ይዘፍናል፣ እኩልነትን አክሎበት ያውቃል?? ቴዲ ስለ ሀገሩ ለመስበክ ብዙ ይቀረዋል። ከመጠምጠም ትምህርት ይቅደም!!

    Reply
    • ለጥይበሉ says

      January 11, 2018 12:20 am at 12:20 am

      ሙሉጌታ!! አንድ መሆን ከእኩልነት የሚልቅ ይመስለኛል። አንድ መሆን በውስጡ እኩልነትንም ይጨምራል። እንደሚገባኝ የቴዲም ሃሳብ ይኸው ነው፣ አንድ እንሁን። እኩልነት የሌለበት “ትክክለኛ አንድነት“ ሊኖር አይችልም። እኩልነት ከሌለ አንድነት የተባለው ነገር ውሸት ወይም ስም ብቻ ይሆናል። ቴዲ የአባትህ ስም እንደሚገባው ይሰማኛል። አንዳርጌ!(አንድ አድርጌ፣ አንድ የሚያደርግ)። እንግዲህ መሰለኝና ተናገርኩ ጎልጉል Speak your mind ስላለ።

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule