• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አስመራ ላይ የሙዚቃ ድግስ ማቅረብ – የቴዲ ተስፋ!

December 28, 2017 11:55 pm by Editor 2 Comments

ለዓመታት በአገር ውስጥ የሙዚቃ ድግስ (ኮንሰርት) እንዳያሳይ የታገደው ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አስመራ ላይ የሙዚቃ ድግስ ለማቅረብ ተስፋ እንደሚያደርግ ተናገረ። ችግሮቻችንን አራግፈን ወደፊት መጓዝ አለብን ብሏል።

ዴይሊ ሜይል አዣንስ ፍራንስ ፕሬስን ጠቅሶ እንደዘገበው በእርሱ ላይ እየደረሰ ያለው ነገር እንዳለ ሆኖ ቴዲ “በኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት ላይ” ትኩረት ማድረግ መቀጠሉን ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤቱ ዘና ባለ ሁኔታ መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል።

የልጅነት ዘመኑን በማስታወስ ቴዲ ሲናገር፤ “ልጅ ሆኜ እንደ አንድ አገር ስንኖር አስታውሳለሁ፤ አንድ የምናውቃት አገር ኢትዮጵያ የምትባል ነበረች፤ አሁን በዚህ ዘመን ግን የምንታወቀው በዘራችን ነው፤ ይህ ደግሞ እጅግ አደገኛ እየሆነ መጥቷል” ብሏል።

ህወሓት በቴዲ የጥበብ ሥራዎች ላይ ማዕቀብ በመጣሉ በተለይ ተደናቂነትን ያገኘው “ኢትዮጵያ” የተሰኘው አዲሱ አልበሙም ሆነ ቀደምት ሥራዎቹ እንደሌሎቹ ባለሙያዎች ህወሓት በተቆጣጠረው ሚዲያ ላይ አይሰሙም። አንዳንዶች ይህንን አስመልክተው ሲናገሩ፤ የቴዲ 17 መርፌ ሙዚቃም ይሁን እቴጌ ወይም ባልደራሱ ወይም ማር እስከ ጧፍ ሁሉም ህወሓትን ያስበረግጉታል።

“ጥቁር ሰው” የተሰኘው አልበሙ ህወሓት ከፈጠረው የዘር ፖለቲካ ጋር ተያይዞ በኦሮሞ ብሔረተኞች ዘንድ ስሙ እንዲጠለሽ ብዙ ተሠርቶበታል። እነ ጃዋር መሐመድ ያደረጉት የበቀል እርምጃ ከህወሓት እኩይ ተግባር ባልተናነሰ መልኩ የቴዲ ሥራ ለሕዝብ እንዳይቀርብ ብዙ እንቅፋትን ፈጥረው አልፈዋል። የቴዲ ኮንሰርት ስፖንሰር አድራጊ የነበረው ሃይኒከን ቢራ በዚህ ዘመቻ ምክንያት ራሱን ማግለሉ የሚታወስ ነው። (ይህንን አስመልክቶ ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ አትሞት የነበረውን ዘገባ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)።

ቤቱ ግድግዳ ላይ በተሰቀለ የምኒልክ ጎራዴ አጠገብ ተቀምጦ ቴዲ ስለተካሄደበት ይህን መሰሉ ህገወጥ ዘመቻ ይህንን ይላል፤ “ስለ ኢትዮጵያ ታሪክና ቀደምት ነገሥታት አሉታዊ አመለካከት ያላቸው ቡድኖች ሊኖሩ ይችላሉ። አመለካከታቸውን ባከብርም የኔን አመለካከት መውደዳቸውም ወይም አለመውደዳቸው እውነቱን አይለውጠውም።”

በሙስሊምና ክርስቲያን መካከል ሰላምና ፍቅር፣ መግባባት እንዲኖር የሚያዜመው ቴዲ ከህወሓት ሌላ በርካታ ነቃፊና ስም አጥፊዎችም በዘመኑ አላጣም። በአድናቂዎቹ ሴቶች ጡት ላይ ይፈርማል በማለት ስለ እርሱ ሲናገሩ ለነበሩ የሰጠው ምላሽ በኢትዮጵያ በውጭ አድናቆትን እንዳተረፈለት ዴይሊ ሜይል ዘግቧል። እንደ ኢትዮጵያዊ ይህንን ዓይነት ነገር ፈጽሞ ሊያደርገው እንደማይችል ነው ቴዲ የተናገረው። ይህንን በመደገፍ ይመስላል የአፍሮ ኤፍ ኤም ፕሮግራም ኃላፊ የሆነው ኢዮኤል ሰሎሞን “(ቴዲ) የሚሰብከው የሚኖረውን ነው፤ እኛ እንወደዋለን፤ ኢትዮጵያውያን ይወዱታል” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።

“ኢትዮጵያ” አልበሙ የምረቃ ፕሮግራም የተቋረጠበት ቴዲ አፍሮ፤ ለአዲሱ ዓመት (2010) ያቀደው ኮንሰርትም ተከልክሏል። አሁንም ግን ተስፋ ሳይቆርጥ ለገና ኮንሰርት ለማቅረብ ያቀረበው ጥያቄ እንዲፀድቅለት እየጠበቀ ነው። ይህ ሁሉ ሆኖ በሙያውና በሙዚቃው ስለ ኢትዮጵያ ከመሥራት ምንም እንደማያዳክመው ተናግሯል።

የቴዲ ምኞት እና ተስፋ ግን በዚህ ብቻ የተገታ አይደለም፤ እስከ አስመራ የዘለቀ ነው። እዚያ የሙዚቃ ድግስ ለማቅረብ ተስፋ ያደርጋል። “የሚያስፈልገን የፍቅር፣ የሰላም፣ የይቅርባይነት መንፈስ ነው። ምክንያቱም አሁን ያሉት ችግሮች የታሪክ ቅሬታዎች ያመጧቸው ውጤቶች ናቸው። ልናራግፋቸው፤ ወደኋላ ትተናቸው ልንሄድ ይገባል” ይላል ቴዲ አፍሮ።

ዘገባው ከነፎቶው የተጠናቀረው ከዴይሊሜይል ድረገጽ ነው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: afro, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, Middle Column, teddy, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 2, 2018 03:20 am at 3:20 am

    ሰዎች!! ቴዲ አፍሮ ስለ ኢትዮጵያዊነት ያትታል፣ ይዘፍናል፣ እኩልነትን አክሎበት ያውቃል?? ቴዲ ስለ ሀገሩ ለመስበክ ብዙ ይቀረዋል። ከመጠምጠም ትምህርት ይቅደም!!

    Reply
    • ለጥይበሉ says

      January 11, 2018 12:20 am at 12:20 am

      ሙሉጌታ!! አንድ መሆን ከእኩልነት የሚልቅ ይመስለኛል። አንድ መሆን በውስጡ እኩልነትንም ይጨምራል። እንደሚገባኝ የቴዲም ሃሳብ ይኸው ነው፣ አንድ እንሁን። እኩልነት የሌለበት “ትክክለኛ አንድነት“ ሊኖር አይችልም። እኩልነት ከሌለ አንድነት የተባለው ነገር ውሸት ወይም ስም ብቻ ይሆናል። ቴዲ የአባትህ ስም እንደሚገባው ይሰማኛል። አንዳርጌ!(አንድ አድርጌ፣ አንድ የሚያደርግ)። እንግዲህ መሰለኝና ተናገርኩ ጎልጉል Speak your mind ስላለ።

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule