• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአባዱላ አጣብቂኝ

December 22, 2017 03:52 pm by Editor Leave a Comment

ከሁለት ወራት በፊት “ … አሁን በደረስኩበት ደረጃ በዚህ ኃላፊነት ለመቀጠል የማያስችሉኝ ሁኔታዎች ስላሉና ፍላጉቱም ስለሌለኝ ለመልቀቅ ድርጅቴንና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ጠይቄያለሁ” ያለው አባዱላ ገመዳ ዛሬ ኦህዴድን ለህወሓት ሲያግባባ በገሃድ ታይቷል።

“የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን ህገ-መንግስታዊ ልዩ ጥቅም አስመልክቶ በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ህዝባዊ ውይይት ለማካሄድ” በሚል ህወሓት የሚዘውረው “ፓርላማ” ዛሬ ስብሰባ ጠርቶ ነበር። የኦህዴድ ተወካዮች በኦሮሚያ ችግር እያለ፤ የኦሮሞ ሕዝብ በረቂቅ አዋጁ ላይ በአግባቡ ሳይወያይ እንዲሁም የሁሉም አካባቢ ተወካዮች ሳይገኙና በአገሪቱ በአጠቃላይ ያለው ችግር ሳይፈታ ውይይት ማድረግ ተገቢ አይደለም ብለው ተቃውሞ አሰምተዋል።

ከወራት በፊት “አሁን በደረስኩበት ደረጃ በዚህ ኃላፊነት ለመቀጠል የማያስችሉኝ ሁኔታዎች ስላሉና ፍላጉቱም ስለሌለኝ” ከሁሉም ነገር እለቃለሁ ብሎ መግለጫ የሰጠው አባዱላ በዚያው መግለጫው ላይ “ጥያቄዬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር አፈ ጉባዔነት የመልቀቅ ቢሆንም፣ የመረጠኝን ሕዝብና ያስመረጠኝን ድርጅት ስለማከብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነቴ እቀጥላለሁ። ከዛ ውጪም ለሕዝብ ይጠቅማል በምላቸው ሥራዎች ባለኝ ጊዜ ተሰማርቼ የማገለግል ይሆናል” ማለቱ የሚታወስ ነው። የዛሬው የማግባባት ተግባሩ ከየትኛው ጎራ እንደሚያሰልፈው ጉልህ ማስረጃ የሰጠ ነው ተብሏል።

በዛሬው የህወሓት ስብሰባ ላይ ከህወሓቱ አስመላሽ ወልደሥላሴ ጋር በመሆን ስብሰባውን የተቃወሙትን ለማግባባት ሲጥር የተስተዋለው አባዱላ “… በክልሉ (በኦሮሚያ) ውስጥ ችግር ቢኖርም ምክር ቤቱ ስራውን መስራት ስለሚጠበቅበትና ጉዳዩም የተለያዩ በመሆኑ ውይይቱ መቀጠል አለበት … እስካሁን የህዝብ ውይይት አለመደረጉ ስህተት ነው፤ በመሆኑም አሁን የባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ጭምር በመሆኑ ቢቀጥል የተሻለ ነው፤ ሃሳቦች ማንሳት፣ መከራከርና ማዳበር ተገቢ ሲሆን፤ ቀጣይ የሚነሱ ሃሳቦችን በመያዝ ምክር ቤቱ የሚወስንበት ጉዳይ ይሆናል” በማለት ተናግሯል።

“የለውጥ አራማጆች” ተነስተዋል በሚባልበት እና የእርሱም የሥልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ከዚሁ የለውጥ ማዕበል ጋር የተያያዘ ነው በሚል ሲዘገብለት የነበረው “ጃርሳው” ከኢህአዴግ የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ በኋላ ጀርባውን ለኦህዴድ መስጠቱ ሁሉንም ነገር በዜሮ የሚባዛው ሆኗል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ “አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ” በሚል ባተመው ዘገባ ላይ ይህንን ብሎ ነበር፤ የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው የዘመኑ “ሚዲያ” የአባዱላን ከአፈጉባኤነት መልቀቅ በሰበር ዜናነት ማናፈሱ ቆም ብሎ ላየው ራስን ትዝብት ላይ የሚጥል ነው። የአባዱላ መልቀቂያ ማስገባት “ምስጢር” በቅርቡ የሚለይለት ቢሆንም በህወሓት ተለክቶና ተጠፍጥፎ የተሠራ ድርጅትና ስብዕና ያለው ለዚህ ዓይነት የሞራል ልዕልና ይደርሳል ብሎ መገመት ህወሓትን ካለማወቅ ወይም ራስን ከመሳት የሚመነጭ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

በበርካታ የሙስና ተግባራትና ህይወት ማጥፋት አለበት እየተባለ የሚነገርለት አባዱላ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት ተማርኮ በሻዕቢያ ፈቃድና በህወሓት ፈጣሪነት አዲስ ስብዕና ተሰጥቶት ኦህዴድ የሚባል የጀመረ መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። ይህ ስብዕናው ህወሓት በህንፍሽፍሽ ልትበታተን ስትል የኦሮሞውን ክንፍ ይዞ መለስን የታደገ በመሆኑ ባለውለታነቱ ለማን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ ሆኗል። (ፎቶዎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተወሰዱ ናቸው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: News Tagged With: abadula, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, gemeda, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule