
አቶ አባዱላ ገመዳ ከሁለት ሳምንታት በፊት ለዓመታት ከተቀመጡበት የአፈ ጉባኤነት መንበር ላይ ለመልቀቅ መጠየቃቸው ከባለፈው ሳምንት ማብቂያ ጀምሮ ዋነኛ ርዕስ ሆኖ ዘልቋል።
ከፓርቲያቸው ኢህአዴግ/ኦህዴድ እንዲሁም ከእራሳቸው አንደበት ዜናውን ለማስተባበል የተሰማ ነገር ስለሌለ ሥልጣን ለመልቀቅ መጠየቃቸው ሃቅ ወደ መሆኑ ያመዘነ በነበረበት ጊዜ ጥያቄ የማቅረባቸውን እውነትነት እራሳቸው አረጋጥጠዋል።
ወታደራዊው መንግሥት አባዱላ መስራችና አባል የሆኑበት ኦህዴድ በሚገኝበት ኢህአዴግ ተሸንፎ ከተወገደበት ጊዜ አንስቶ በተለያዩ የወታደራዊና የሲቪል ሃላፊነቶች ላይ ቆይተዋል።
አባዱላ ከትግል በኋላ ፓርቲውን የተቀላቀሉ በርካታ አመራሮች ባሉበት ኦህዴድ ውስጥ ተቀባይነት ካላቸው ቀደምት ጥቂት መስራች አባላት ውስጥ ቀዳሚው እንደሆኑ ይነገራል።
ለዚህም ይመስላል በርካታ የኦህዴድ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም በፓርቲውና በክልሉ ከፍተኛ የሃላፊነት ቦታ ላይ ያሉ አመራሮች ዜናው እንደተሰማ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአፈጉባኤውን ምስል በስፋት የሚለጥፉትና የገጻቸው መለያ እያደረጉ ያሉት።
ቅሬታ
አባዱላ ገመዳን በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች፤ በተለይ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ ብዙም ደስተኛ እንዳልነበሩ ይናገራሉ።
እንደሚታወቀው የአዲስ አበባና የኦሮሚያ የተቀናጀ ማስተር ፕላንን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ በክልሉ ውስጥ እስካሁን ለዘለቀው ቅሬታ መነሻ ነበር።
አቶ አባዱላም ችግሩን ለማብረድና መረጋጋት ለማምጣት ከፊት ሆነው ሲሰሩ ከነበሩት ሰዎች መካከል ቀዳሚው ናቸው።
የሥልጣን መልቀቂያ ማቅረባቸው ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ የጥያቄውን እውነትነት ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የውሳኔያቸውን ትክክለኛ ምክንያት ማወቅ ለተቃዋሚዎቻቸው ብቻ ሳይሆን በዙሪያቸው ላሉትም ጥያቄ ሆኗል።
ኦሮሚያ ከሶማሌ ክልል ጋር በሚዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች የተቀሰቀሰው አሳሳቢ ግጭትና መፈናቀል የሚያስቆመው ጠፍቶ ለረጅም ጊዜ መዝለቁም ቅሬታ ሳይፈጥርባቸው እንዳልቀረ የቅርብ ሰዎቻቸው ይናገራሉ።
ከሁሉ በላይ አቶ አባዱላ ወደ ባሌ ዞን በሄዱበት ጊዜ በግጭቱ የከፋ ችግር የደረሰባቸውን ሰዎች ባገኙበት ጊዜ የተሰማቸው ሃዘንና ተስፋ መቁረጥ ለዚህ ውሳኔያቸው አባባሽ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አብረዋቸው የነበሩ ሰዎች ይጠረጥራሉ።
ከማዕከል ወደ ክልል
ኦሮሚያ አርሲ ዞን የተወለዱት አባዱላ ገመዳ በመጪው ሰኔ 60ኛ ዓመታቸውን የሚድፍኑ ሲሆን የልጆች አባትም ናቸው።
አቶ አባዱላ በመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው በሃገር መከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ በተለያዩ ሃላፊነቶች፤ በወታደራዊ መለዮ ስር እስከ የሜጀር ጄኔራልነት ማዕረግ ይዘው ስርተዋል።
ደም ባፋሰሰውና እስካሁን እልባት ባላገኘው የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጦርነትም ሚና ከነበራቸው የጦር መሪዎች ውስጥ ይጠቀሳሉ።
ከጦርነቱ በኋላ በዋናነት በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል ተከትሎ በርካታ የኢህአዴግ አንጋፋ ባለሥልጣናት ከፓርቲና ከመንግሥት ሃላፊነቶች ሲነሱ የሌሎች ክልሎችን ጨምሮ አቶ ኩማ ደመቅሳ ከኦሮሚያ ርዕሰ መስተዳደርነት እንዲለቁ ተደርገው ነበር።
በወቅቱ የተፈጠረውን የሥልጣን ክፍተት ለመሙላትም አባዱላ ገመዳ ወታደራዊ ማዕረጋቸውን በአቶ ተክተው የኦሮሚያ ክልልን የርዕሰ መስተዳድር መንበር ያዙ።
የክልሉ ፕሬዝዳንት በነበሩት ጊዜ ከፍተኛ ተቀባይነትና ድጋፍን ለማግኘት ከመቻላቸውም በላይ ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወናቸውም ይነገርላቸዋል።
ሌሎች ደግሞ የኦሮሚያ ክልልን መሬትን ያለአግባብ ለፈለጉት ሰው በብዛት ሲሰጡ ነበር በማለት ይወቅሷቸዋል።
ከክልል ወደ ማዕከል
በፌደራል መንግሥቱ ውስጥ ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ በተደረጋላቸው ጊዜ በክልሉ ምክር ቤትና በኦህዴድ በኩል ጥያቄዎች ተነስተው ነበረ።

በ2002 ዓ.ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ሆነው ሲመጡ በክልሉ በርካታ የጀመሩዋቸው ሥራዎች እንደነበሩና አመራሩንም በከፍተኛ ደረጃ አንቀሳቅሰው እንደነበረ በመግለፅ ብዙ የድርጅቱ አባላት ቅር መሰኘታቸውን ገልፀው ነበር።
አባዱላ ከኦሮሚያ ክልል ተነስተው የተወካዮች ምክር ቤትን በአፈ-ጉባኤነት ለአምስት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በ2008 በድጋሚ ለሁለተኛ ዙር በነበሩበት ቦታ እንዲቀጥሉ ተደርገዋል።
አባዱላ በትምህርት በኩል በቀዳሚነት በቻይና የመከላከያ ዩኒቨርስቲ ወታደራዊ አመራርን የተማሩ ሲሆን፤ ከዚያም በህዝብ አስተዳደር የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ እንዳላቸው ታሪካቸው ያሳያል።
ወዴት?
የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸው ከታወቀ በኋላ በማህበራዊው የመገናኛ ዘዴ በኩል የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው።
በተለይ የመልቀቃቸው ምክንያትና ቀጣይ እርምጃቸው ምን እንደሚሆን ማወቅ የብዙዎች ጉጉት ሆኗል። እሳቸውም በመጨረሻ ላይ በሰጡት ቃል ወደፊት ጥያቄያቸው ምላሽ ሲያገኝ የመልቀቃቸውን ምክንያት በዝርዝር እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።
የምክር ቤት አባልነታቸውን፣ በኢህአዴግና በኦህዴድ ውስጥ ያላቸውን ኃላፊነቶች በሙሉ ይተዋሉ? ወይስ የአፈ-ጉባኤ ሥልጣናቸውን ብቻ ? የሚለው ጥያቄ የብዎዙች የነበረ ቢሆንም አባዱላ እንዳሉት፤ ”ጥያቄዬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር አፈ-ጉባኤነት የመልቀቅ ቢሆንም፣ የመረጠኝን ሕዝብና ያስመረጠኝን ድርጅት ስለማከብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነቴ እቀጥላለሁ” ብለዋል።
ነገር ግን መንግሥት ለባለሥልጣናት ከሚሰጠው ጥቅማ ጥቅም ውስጥ አንዱ የሆነውንና ለበርካታ ዓመታት ሲኖሩበት የቆዩትን ቤት እንደለቀቁ መነገሩ ደግሞ ውሳኔያቸው ከመንግሥት ሥራዎች መራቅን ሊጨምር ይችላል የሚል ጥርጣሬን አጭሮ ነበር።።
ማግባባት
ቢቢሲ ስለጉዳዩ ለማወቅ አቶ አባዱላን ጨምሮ በፌደራል መንግሥቱና በኦሮምያ ክልል ውስጥ ሰለጉዳዩ ያውቃሉ የሚላቸውን ከፍተኛ ኃላፊዎችን አግኝቶ ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም።
ቢሆንም ግን የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸው እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ ችለናል። ሁሉም ግን ምክር ቤቱ ሲከፈት የሚፈጠረውን ለማወቅ የጓጓ ይመስላል።
አባዱላ ገመዳ ባቀረቡት የሥልጣን መልቀቅ ጥያቄ ፀንተው ከቦታቸው ከተነሱ በኦህዴድ ውስጥ በይፋ ”በቃኝ” በማለት ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ቀጥለው ሁለተኛው የፌደራል መንግሥቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን ይሆናሉ።
In any way we cut and paste, we tear and put together. Whether it is initiated and spiced by TPLF or it is a personal move from the deep conscious of Aba Dula, the tooth paste is out of the tube and you can not put it back. His resignation in my personal opinion is a good thing for the country considering the time and the weakening of TPLF to govern. I really do not care for Aba Dula the person. The action he took is one thing that is not done before by high functioning EPRDF official. One can say Dr. Giddada (the President) the appointee not that much functional. Look the discussion it brought, the excitement of many to say something they never said. The DC area Beer places are filled with customers talking the resignation and its effect. Aba Dula’s action I hope will open the door for many who are trapped in TPLF to follow him.
Secondly his action should be taken by us as something positive and we restrict ourselves from ridiculing him and name calling. Our positive action gives impetus to the many of those trapped and want to leave. Those of us outside and diaspora try to take them with open hand rather than name calling. I have seen some you-tube release with all the negative about Abadula. Judgement day will come for his crimes but for the sake of more to leave this brutal mafia TPLF, we should restrict our-self from one-sided unnecessary comment that will demoralize those who want to leave the system. We have to give some type of motivations that they leave serving and making a continuous damage to our people. The more of them leave the shorter life span TPLF will have.
Let us not forget the other high official who defected these days. That is also a welcome news.
ጎልጉል!ጎልጉል!
One important wisdom in combating an adversary is to weaken it from within. If the weakening comes from within, the other side should be wise enough to understand and appreciate it and welcome the defectors and encourage others to follow suit.
Like the many uncanny paltalkers, media people should think twice before they dare to spit out their half digested, mostly unwise, disgusting and worthless commentaries.
Any thing that stands in TPLF`sway, any action that exposes and weakens TPLF and any person who defects ist rank and file is an added force to the effort in bringing TPLF to ist knees.
It is a big joke for us!!!