• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ?

October 10, 2017 12:36 am by Editor 1 Comment

የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው የዘመኑ “ሚዲያ” የአባዱላን ከአፈጉባኤነት መልቀቅ በሰበር ዜናነት ማናፈሱ ቆም ብሎ ላየው ራስን ትዝብት ላይ የሚጥል ነው። የአባዱላ መልቀቂያ ማስገባት “ምስጢር” በቅርቡ የሚለይለት ቢሆንም በህወሓት ተለክቶና ተጠፍጥፎ የተሠራ ድርጅትና ስብዕና ያለው ለዚህ ዓይነት የሞራል ልዕልና ይደርሳል ብሎ መገመት ህወሓትን ካለማወቅ ወይም ራስን ከመሳት የሚመነጭ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

በበርካታ የሙስና ተግባራትና ህይወት ማጥፋት አለበት እየተባለ የሚነገርለት አባዱላ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት ተማርኮ በሻዕቢያ ፈቃድና በህወሓት ፈጣሪነት አዲስ ስብዕና ተሰጥቶት ኦህዴድ የሚባል የጀመረ መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። ይህ ስብዕናው ህወሓት በህንፍሽፍሽ ልትበታተን ስትል የኦሮሞውን ክንፍ ይዞ መለስን የታደገ በመሆኑ ባለውለታነቱ ለማን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ ሆኗል።

በሌላው አንጻር አባዱላ የኦሮሚያ ዋና ኃላፊ በነበረበት ጊዜ ጁነዲን ሳዶ በኦሮሚያ የፈጠረውን ካቢኔ እና አደረጃጀት በማፍረስ አዲስ ለመለመላቸው የኦህዴድ አባላት “አትደግፉን ነገር ግን የክልሉን ልማት አታደናቅፉ” በማለት እስከ ቀበሌ የደረሰ አዲስ የካድሬ አደረጃጀት አዋቅሮ ነበር። አባዱላ ይህንን ተፈጻሚ ሲያደርግ የሄደበት የአደረጃጀት መንገድ የኦነግም ሆነ የተቀናቃኝ ፓርቲ አባላትን የኦህዴድ ጭምብል በማልበስ ነበር። ለዚህ ድፍረት ያበቃውም በህንፍሽፍሹ የነ ስዬና ተወልደን ውህዳን ቡድን በመቃወም ከመለስ ጋር በመወገን ኦህዴድን ለህወሓት በማዳኑ ከመለስ በተሰጠው “በኦሮሚያ ያሻህን አድርግ” ፈቃድ ነበር። ለካድሬው “ነጻነት” በመስጠት የተወዳጀው አባዱላ ባንድ ወገን ይህ ድርጊቱ የካድሬውን ፍቅር ሲቸረውና “ጃርሳው” ሲያስብለው በሌላው ግን ከአላሙዲ ጋር በግብር ጉዳይ፤ ከመለስ ጋር ደግሞ በተወዳጅነት ቅንዓት ጥርስ ውስጥ አስገባው። እንደ ሰይጣን ወዳጅ የሌለው ህወሓትም አባዱላን አፈጉባኤ በማለት አከሸፈው።

አንድ የማይካድ ሐቅ ቢኖር አባዱላ ኦሮሚያን ከለቀቀ ወዲህ ኦሮሚያ እንደቀድሞው መሆን አቅቷታል። የጁነዲን አርሲ ተኮር ኦህዴድ በጃርሳው ከተናደ በኋላ ኦህአዴድም እንደ ድርጅት የህወሓት ሎሌነቱን በበላይ አመራሩ ብቻ ወስኖ የመካከለኛውና የበታቹ ከከዳ ሰንብቷል። በሙክታር ከዲር የሥልጣን ዘመን ከመለስ ሞት ጋር ተዳምሮ ህልውና ያጣውን ኦህዴድን ወደነበረበት የመመለስ ሥራ የለማ መገርሳ ትከሻ የማይሸከመው ሆኗል።

የመናገር፣ የመጻፍ፣ ሃሳብን የመግለጽ፣ ወዘተ መብቶች በማይታሰቡባት ኢትዮጵያ እንደ ብአዴን በህወሓት ተጠፍጥፎ የተሠራው ኦህዴድና ከስም እስከ ስብዕና ተለክቶ የተሰጠው አባዱላ በቴሌቪዥን ቀርቦ “ሥልጣኔን እለቃለሁ” ብሎ በነጻነት መናገሩ አእምሮ ላለው “እንዴት” ብሎ እንዲጠይቅ የሚያስገድድ ተግባር ነው። በአደባባይ “ስኳር እወዳለሁ፤ ይጣፍጠኛል” አስብሎና አዋርዶ አብሮ የታገለውን ታምራት ላይኔን ያዋረደው ህወሓት፤ በርካታ “በቁምሳጥን ውስጥ የተደበቁ አጽሞች” ያሉበትን አባዱላ ለዚህ “ዕድል” ማብቃቱ ከአባዱላ የመልቀቂ ጥያቄ በላይ በሰበር ዜናነት ሊበሰር የሚገባው ነበር።

ለማንኛውም ሁኔታው በቅርቡ ግልጽ ይሆናል። የኦሮሚያ ጉዳይ እጅግ መከራ ውስጥ ያስገባው ህወሓት አባዱላን በጃርሳውነት ወደ ኦሮሚያ (ጨፌ) ይመልሰው ይሆናል (ከአፈጉባኤነት እንጂ ከድርጅቴ አለቀኩም ማለቱን ያጤኗል) ወይም በቅርቡ በሙስና ጉዳይ ተጠርጣሪ ከአገር እንዲስኮበልል አድርጓል፣ አንጃ ሆኗል፣ በሙስና ተጨማልቋል፣ … ብሎ ወደ ሸቤ ይወረውረዋል። አለበለዚያም ፋይሉ እንደ ተዘጋ ጉዳይ በመዝገብ ቤት በኩል ወደ “ዴድ ፋይል” ክፍል ይልከዋል። ከዚህ ይልቅ ኢትዮጵያን እንደ አገር ለመቆየት የሚያሰጋት በርካታ ጉዳይ መኖሩን ሳንዘነጋ ጥይታችንን በእንደዚህ ዓይነት አናሳ ዜና ላይ ከማባከን ይልቅ በህወሓት ላይ ማድረጉ ነጻነታችንን ቅርብ ያደርግልናል።

ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ታዛቢው ነኝ ከታላቋ እስርቤት ኢትዮጵያ (አዲሳባ) (ፎቶ፡ በተለምዶ አባዱላ የሚባለው ቶዮታ ሚኒባስ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    October 11, 2017 03:00 am at 3:00 am

    ወደ ሸቤ ነው!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule