• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንግሥትና ኦዲፒ የጃዋርን የድጎማ በጀት ጥያቄ ውድቅ አደረጉ

October 17, 2019 06:39 am by Editor Leave a Comment

የኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስኪያጅና ባለቤት ጃዋር መሃመድ ለድርጅቱ በጀት እንዲመደብና በቋሚነት እንዲረዳ ለመንግሥት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ታወቀ። የጎልጉል የኦዲፒ የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የድጎማ ጥያቄው ውድቅ መደረጉ ጃዋር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና በኦዲፒ ላይ የጥላቻ ሪፖርት ተጠናክሮ እንደሚሠራ መናገራቸውን አመልክተዋል። በተያያዘ ጃዋር የሚመራው ኦ.ኤም.ኤን. ለሸዋ ተወላጅ ኦሮሞዎች መድረክ እንደማይሰጥና ኦነግ በንጹሃን ላይ እየፈጸመ ያለውን ግድያም ሽፋን እንዲሰጥ እንደማይፈቅድ ተገልጿል።

እንደ መረጃ አቀባዮቹ ከሆነ ጃዋር ለሚመራው “የትግል ሚዲያ” ከፍተኛ በጀት የጠየቀው ሚዲያው ለተገኘው ለውጥ ትልቁን ሚና ተጫውቷል በሚል ነው። ኦ.ኤም.ኤን. በትግሉ ወቅት የአንበሳውን ድርሻ በመጫወቱ የኦሮሚያ ክልልም ሆነ መንግሥት ሊደጉመው እንደሚገባ በተደጋጋሚ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ የተደረገው በሥራ አስፈጻሚ ውሳኔ ነው።

ጃዋር ድጎማው እንደማይሰጠው ከተገለጸለት በኋላ በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ በስፋት የአየር ሰዓት እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ኦ.ኤም.ኤን. የሚሠሩ እንደነገሯቸው የመረጃው ክፍሎች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ አስታውቀዋል።

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዓለም ሰላም የኖቤል ተሸላሚ መሆናቸው ይፋ መሆኑንን ተከትሎ የዓለም ሚዲያ ሰፊ ሽፋን ቢሰጡትም ኦ.ኤም.ኤን. ግን ቀዳሚ ዜና እንኳን ያላደረገው በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ታውቋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ታላቅ ሽልማት አስመልክቶ በተለያዩ የኦሮሚያና የክልል ከተሞች የተደረገውን የድጋፍና የደስታ መግለጫ ሰልፍ ኦ.ኤም.ኤን. በተመሳሳይ የሚገባውን ሽፋን እንዳልሰጠው መረጃ የሰጡት ክፍሎች ገልጸዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያም ጃዋር መሃመድ በስፋት ሲወገዝ ተሰምቷል።

ጃዋር በፌስቡክ ገጹ የእንኳን ደስ አለህ አጭር መልዕክት ከመለጠፉ በዘለለ የተገኘውን ዜና ሁሉ “ሰበር” ለማለት የማያቅማማው ኦ.ኤም.ኤን. ለዜናው ጆሮ ዳባ ማለቱ በተለያዩ የኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ ጉምጉምታ እንደፈጠረ ጎልጉል ያናገራቸው አስረድተዋል።

ኦ.ኤም.ኤን. አገር ውስጥ በአንድ ጎረምሣ ስም ተመዝግቦ የሚሠራ ተቋም ሲሆን የድርጅቱ ገንዘብም በዚሁ ወጣት ስም በተከፈተ አካውንት እንደሚንቀሳቀስ የሚዲያው ምንጮች ይናገራሉ። ጃዋር በዜግነት ኢትዮጵያዊ ባለመሆኑ አንድ በገንዘቡ ላይ እንደፈለገ እንዲናኝ የተፈቀደለት ወጣት መሰየሙን የገለጹት ምንጮች ኦ.ኤም.ኤን. ነጻነት የሌለበት፣ ገቢና ውጪው የፋይናንስ ደንብን በአግባቡ የማይከተል ድርጅት እንደሆነ ጠቁመዋል።

ከወራት በፊት ራሳቸውን በዩቲዩብ ይፋ ያደረጉ ይህንኑ የተዝረከረከና አንድ ሰው እንዳሻው ለፈለገው ተግባር የሚጠቀምበት ሚዲያ ወደ ህግ ለማቅረብ እንደሚሠሩ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

በሚሊዮን ብሮች የሚገመቱ እጅግ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን የሚሸምተውና “ቱጃር” የሚባለው ጃዋር መሃመድ አቋሙን ግልጽ አድርጎ ወደ ፖለቲካ የማይገባው በዚሁ የሚዲያ ነጋዴነት ለመቀጠል ሲል የቀድሞ የቦርድ አባላትን ማሰናበቱን የሚገልጸው የኦ.ኤም.ኤን. ባልደረባ “ጃዋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ አነጣጥረው ዘመቻ ለሚያካሂዱ የሚዲያ አውታሮችና የፌስቡክ አርበኞች ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ድጋፍ የማድረግ ዕቅድ መንደፉን አስቀድሜ አውቃለሁ” ሲል ተናግሯል። ይሁን እንጂ እነማን እንደሆኑ የሚዲያ አውታሮቹን በስም አልጠራም። ከዕቅዱ ሌላ አንዳንዶቹን በድብቅ ቀጥተኛ ድጋፍ እያደረገላቸው እንዳለ ይነገራል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኦነግ-ሸኔ ባለፈው ቅዳሜ በምስራቅ ጉጂ ዞን ስለገደላቸው ስድስት ንጹሃን ዜጎች ኦ.ኤም.ኤን. ዘገባ አላቀረበም። አባቱ የተገደሉበት ሀጻን “አባቴ ገጠር ካለው ቤቱ ለሥራ ሄዶ ቁርስ እየበላ ሳለ የኦነግ ታጣቂዎች ገብተው ገድለውት ሄዱ” ሲል ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ (ቪ.ኦ.ኤ.) ቢናገርም ለኦ.ኤም.ኤን. የዜና ፍጆታ ብቁ አለመሆኑ በኦሮሞዎችም ሆኑ በሰላም ወዳድ ዜጎች መነጋገሪያ መሆኑ ታውቋል።

የኦ.ኤም.ኤን. ባለቤት ጃዋር መሃመድ የቅማንት ዜና ላይ ሙጥኝ በማለት የህወሓት አጀንዳ አስፈጻሚ መሆኑና ዘንድ “እረኛውን ግደል፣ መንጋው ይበተናል” የሚለውን የዲጂታል ወያኔ ዓላማ መደገፉ፣ ዝምታን በመረጡት አብዛኛው የኦሮሞ ተወላጆና ነዋሪዎች ዘንድ እየተብሰለሰለ ያለ ጉዳይ እንደሆነ በርካቶች እየተናገሩ ነው።

ጃዋር የአሜሪካ ዜግነቱን እንደሚመልስ (ቀድጄ እጥለዋለሁ እስከማለት) በተደጋጋሚ ቢናገርም እስካሁን እርሱም ሆነ ቤተሰቡ የሚታወቁት በአሜሪካ ዜግነት ነው። በአሜሪካ አገር የተከፈተው ኦ.ኤም.ኤን. በሕግ የተመዘገበው በትርፍ አልባ ድርጅት ስም ሲሆን እኤአ ከ2014 እስከ 2017 አምኖ ለአሜሪካ መንግሥት ሪፖርት ያደረገው የድርጅቱ አጠቃላይ ገቢ ከ2.8 ሚሊየን ዶላር በላይ (በብር እስከ 100 ሚሊየን) ነው። ይህ የ2018 ዓም የድርጅቱን ገቢውን ሳይጨምር ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የኦ.ኤም.ኤን. የቀድሞ የቦርድ አባልትም ሆኑ መረጃ ያላቸው ወገኖች አስተያየት መስጠት ከፈለጉ ለማስተናገድ ዝግጁ ነው። ጃዋርን በስልክ ለማግኘት የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ሙከራ ቢያደርግም ሊሳካለት አልቻለም።

በተያያዘ ዜና በምን ምክንያት እንደሆነ በውል ባይታወቅም ቀደም ሲል የኦነግ-ሸኔ ወታደሮችን ጫካ ድረስ እየሄዱ ሲያደራድሩና ሲያስማሙ የነበሩት እንዲሁም ወደ ካምፕ እንዲገቡ በማድረጉ ውስጥ ቀዳሚ የነበሩት በቀለ ገርባ በቅርቡ ኢትዮ ፎረም ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ “ሸኔ የሚባል ቡድን የለም” ሲሉ ተደምጠዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Ethiopia, Full Width Top, funds, jawar, Middle Column, omn

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule