• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ውሉ ፈርሷል

January 14, 2020 01:52 am by Editor Leave a Comment

ባልተረጋገጠ የዶክትሬት ማዕረግ ራሱን የፒ.ኤች.ዲ. ዲግሪ ሸልሞ የሚጠራው ጸጋዬ አራርሣና ጓደኞቹ በቀጣሪያቸው ጃዋር መሃመድ መካከል የነበረው ውል መፍረሱን ራሱ ጸጋዬ ይፋ አደረገ። ጃዋር ያልተለመደ ተግባር እንዳላደረገ በቅርብ የሚከታተሉት ይመሰክራሉ።

በተለምዶ በእንግሊዝኛው “down under” ወይም “እንጦሮጦስ” ተብሎ ሊጠራ ከሚችለው አውስትራሊያ ያለማቋረጥ በጥላቻ የተሞላውን መርዝ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚያስተላልፍ ነው። ያለመታከት በአማርኛ፣ በእንግሊዝኛና በኦሮሚኛ ይጽፋል፤ በማንኛውም ሚዲያ ከተጠራ እምቢ ማለትን አያውቅም፤ በተለይ ጸረ-ኢትዮጵያ አቋም ባለው ሚዲያ ላይ ደጋግሞ ቢቀርብ አይጠግብም፤ ከጃዋር መሃመድ ጋር የገጠመው አገርንና ሕዝብን ሊያድን ለሚችል ትልቅ ዓላማ ሳይሆን በጥላቻ ሰላምና ዕረፍት ያጣችውን ነፍሱን በበቀል ለማርካት ነበር። ጸጋዬ ረጋሣ አራርሣ ይባላል፤ የጃዋር ሎሌ ሆኖ በታማኝነት አገልግሏል፤ ከእርሱም ጋር አብሮ ሕዝቅኤል ገቢሣ ሌላው ተጠቃሽ ነው።

ወደ አውስትራሊያ ለትምህርት ሄዶ በዘመናዊው የሃሜታ ሰፈር (ፌስቡክ) በወሬ ተጥዶ በመዋል ጥላቻን ሲሰብክና ሲያሰራጭ በመዋሉ ትምህርቱን መከታተል አቅቶት የተሰናበተው ጸጋዬ፤ ከሕዝቅኤልና መሰሎቹ ጋር በመሆን የጥላቻና የግጭት መልዕክቶችን ሲያሰራጭ ቆይቷል። ጃዋር ባቋቋመው ኦኤምኤን ላይ ያለመታከት በመቅረብ እንዴት አንዱ ማኅበረሰብ በሌላው ላይ መነሳት እንዳለበት በዝርዝር ሲያስረዳና ሲተነትን ሰንብቷ።

ጸጋዬ ከ“እንጦሮጦስ” ሆኖ በየዕለቱ በተደጋጋሚ ወደ አገር ውስጥ እሣት ይለኩሳል፣ ግልጽ ጦርነት ያውጃል፤ ጃዋር ደግሞ ከአገር ውስጥ ሆኖ በፖለቲካና በሰላማዊ መንገድ ትግል መካሄድ አለበት እያለ በስልት ግን እንደ ትህነግ/ህወሓት ካሉ የጥፋት ኃይሎች ጋር በመወገን ሕዝብ ያስጨርሳል፣ እሣቱን ያቀጣጥላል።

በተሃድሶ የተጀመረውን የዶ/ር ዐቢይን አስተዳደር ያለመታከት በመክሰስ ሥልጣን እንዲለቅ፣ ሕጋዊነት እንደሌለው፣ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ መዲና መሆን እንደሌለባት፣ ሁላችንንም የሚያስማማ አዲስ ዋና ከተማ መመሥረት እንዳለበት፣ የምኒልክ ቤተመንግሥትም መፍረስ እንዳለበት፣ ሌላ አዲስ ቤተመንግሥት መሠራት እንዳለበት፣ በደቡብና በአማራ ክልል የሚገኙ ማኅበረሰቦች “በክልልነት” ሽፋን አንዱ በሌላው ላይ መነሳት እንዳለበት፤ ወዘተ ማባሪያ የሌለው የጥፋት መልዕክቶችን ሲቀምም የሚውለው ጸጋዬ አራርሣ በጃዋር መሃመድ ላይ የሰላ ሒስ ሰንዝሯል።

ጃዋር መሃመድ በባህርዩ ሆነ በተግባሩ ወዳጅ የለውም። የ“ድምጻችን ይሰማ” ትግልን ለመቀልበስና በሥሩ ለማድረግ ሙከራ በማድረግ በጥሩ መስመር ላይ የነበረውን አካሄድ ለራሱ ጥቅም ለመዘወር በወሰደው አቋም ትግሉ ወደ ሜንጫ ትግል በመቀልበስ ካከሸፈው በኋላ ቀጣይ ፊቱን ያዞረው የኦሮሞ ሚዲያ ለመመሥረት ካሰቡ ጋር በመወዳጀት ነበር።

ኦኤምኤን ሲመሠረት ሃሳቡ የራሱ አልነበረም፤ እሱ ቢቀበለውና ቢያራግበውም ሃሳቡን በፋና ወጊነት የጀመሩት ሌሎች ናቸው፤ ሚዲያውን ሲጀምሩ ተባብረው “ኦሮሞ ፈርስት” በማለት ገንዘብ ለመሰብሰብ እንዲያመቻቸው ጃዋር የቀዳሚነቱን ሥፍራ በመውሰድ ሰሜን አሜሪካንና አውሮጳን ዞሩ። ዙረቱ ሲያልቅና ሚዲያው ሲመሠረት ጃዋር እያንዳንዱን አብረውት የነበሩትን ጓዶች ቀስ በቀስ ቀነጠሳቸው። ተቀንጣሾቹም በኦሮሞ መካከል ልዩነት ላለመፍጠር በሚል አፋቸውን ዘግተው እስካሁን አሉ፤ እነዚህ የቅርብ የትግል አጋሮቹና የዕድሜ እኩዮቹ ናቸው። ጊዜው ሲደርስ ይፋ የሚያወጡት ቢኖርም ጃዋር ግን ወዳጅ አልባ እንደሆነ አንድ ምስክር ሆነዋል።

ጸጋዬ፣ ሕዝቅኤልና መሰሎቻቸው በኦኤምኤን ላይ “ጃዋር እንዳለው” እያሉ የጃዋርን አቋም ሲያስተጋቡ ለዓመታት ቆይተዋል። አስፈላጊ ሲሆንም ጃዋር፤ ሕዝቅኤል ገቢሣን፣ በቀለ ገርባን ወደ ትግራይ እንዲዘምቱ በማድረግ ከህወሓት ጋር “የፍቅር ፎቶ በማስነሳት” አስጠቁሯቸዋል፤ ወይም በትህነግ/ህወሓት አነጋገር “አበስብሷቸዋል”። ጸጋዬም ወደ አገር ለመመለስ በሚከብደው መልኩ ከውጪ ሆኖ በየቀኑ መርዙን እንዲረጭ ጃዋር እስኪበቃው ተጠቅሞበታል። ጃዋር በፌስቡኩና በሚዲያው የማይናገረውን ጥላቻ በድፍረትና በወኔ የሰበከለት ጸጋዬ አራርሣ ነው። 

በፌዴራሊስት ስም ከህወሓት ጋር ሊፈጸም የነበረው “ጋብቻ” ገና ጥሎሽ ሳይጣል መፈረካከስ ሲጀምር በጃዋርና በሎሌዎቹ መካከልም ልዩነቶች እየሰፉ መጡ። በፊት እንደፈለጉ በጃዋር ሚዲያ ላይ ያለገደብ ይቀርቡ የነበሩት ሕዝቅኤልና ጸጋዬ ህወሓት ባዲስ መልክ በፈጠረችው “ኩሽ ሚዲያ” ላይ ዕለታዊ ደምበኞች መሆን ጀመሩ። ይባሱንም ብሎ ጃዋር የፖለቲካ ማርሹን ያልታሰበ መንገድ ላይ ቀየረ።

“ተከብቤአለሁ” በሚል የፌስቡክ ወሬ ለ86 ሰዎች በግፍ መሞት ተጠያቂ መሆን የሚገባው ጃዋር መሃመድ፤ በተለይ አሜሪካና አውሮጳ ደርሶ ከመጣ በኋላ “አገር አዳኝ” በመሆን በየሚዲያው ላይ መቅረብ ጀመረ። በኦነግ ሸኔ ላይ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ ሁሉም የኦሮሞ ድርጅቶች ተሰባስበው ሲወስኑ እርሱም አብሮ “ይውደም” አለ። ይህ የአቋም ለውጥ በተለይም ከዐቢይ መንግሥት ጋር ሆኖ መሥራት ከጥንስሱ ጀምሮ ለጸጋዬና ለሕዝቅኤል አልተዋጠላቸውም ነበር። ጃዋር ባለፈው ከአሜሪካ ዙረት በኋላ አውሮጳ ሲሄድ በቅርብ መረጃ ያገኝ ነበረው የጎልጉል ሰው በእነ ጸጋዬና ሕዝቅኤል የአቋም ግትረኝነት ባለመደሰት “ጽንፈኛ፣ አክራሪ” እያለ በመጥራት ጃዋር ሲያናንቃቸው እንደነበር ይጠቅሳል።

በኦነግ ሸኔ ላይ መንግሥት እርምጃ እንዲወስድ የኦሮሞ ድርጅቶች ከተስማሙ በኋላ ህወሓት የጠራው የፌዴራሊስቶች ግምባርም እነ ሕዝቅኤል ገቢሣና አስፋው ወዳጆ ያለ ልክ ጮኸውበት መሰነጣጠቅ የጀመረው ገና ስብሰባው ሳያልቅ ነበር። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ጃዋር “አንዱ የመጫወቻ ካርዴ” ያለው በፌዴራሊስት ግምባር ስም ለማ መገርሣን መሪ በማድረግ መቀሌ ላይ ሊቆረስ የታሰበው “ኬክ” በአቶ ለማ ከብልጽግና ጋር አብሮ ለመሥራት ሲከሽፍ ጃዋር አሰላለፉን ማስተካከል ገፋበት። በኦፌኮ አምኜ “ተጠምቄአለሁ” በማለት የመረራን ፓርቲ ተቀላቀለ። ህወሓትም ከብልጽግና ጋር አብሬ አልሠራም ብላ ስትወስን “መቃብርሽ መቃብራችን” ያሏት እነ ትዕግስቱ አወልና ዘርዓይ ወልደሰንበት “ደህና ሁኚ ፍቕሬ” አሏት።

በዚህ ሁሉ የፖለቲካ ውጣ ውረድ ውስጥ የመጫወቻ ካርዱ እያለቀበት የመጣው ጃዋር ከኦፌኮ ጋር በመሆን የፖለቲካና የምርጫ ተግባር ማካሄዱን በይፋ ጀመረው። ይህም ለእነ ጸጋዬ ሊቀበሉት የማይችሉት ዱብዕዳ ሆነባቸው። “የውሉ መፍረስ” በግልጽ የታየው ጸጋዬ በፌስቡክ ገጹ ላይ ሰሞኑን “ምንደኛ አክቲቪስት”፣ የተሸጡ አክቲቪስቶች፣ ወዘተ እያለ በአሽሙር ሲጎነትለው የቆየውን ጃዋር በግልጽ ስሙን በመጥራት “የኦሮሞ ሕዝብ መሥዋዕትነት የከፈለው የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች (እና የቀድሞ አክቲቪስቶች የነበሩትን እነ ጃዋር መሃመድ) በምሥጢር ከዐቢይ አሕመድ ጋር እንዲደራደሩ ለመፍቀድ ብቻ አይደለም” ብሏል። እንዲያውም ጃዋር የተቀላቀለው ኦፌኮ በቅርቡ ሐረርጌ ያደረገውን ፎቶ በመለጠፍ “ኦፌኮ ይህንን የሚያደርገው ለዐቢይ ጭምብል ለማድረግና ሕጋዊነት ለመሥጠት እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ” በማለት በቀለ ገርባን ከመረራ ጉዲናን ጋር አብሮ ወርፏቸዋል።

ጃዋር መሃመድ ከዚህ በፊት ሲናገር መለስ ዜናዊን እንደሚያደንቀው ገልጾ ነበር። በግልጽ በቃላት ባያስቀምጠውም የመለስን ማኪያቬላዊ አሠራርና በተፈለገው ጊዜ ፍሬቻ ሳያበሩ የመታጠፍ ባህርዩን እንደሚያደንቅ ንግግሩ ያሳብቅ ነበር። የመለስ ተማሪ የሆነው ጃዋር እንደ መምህሩ ምንም ወዳጅ የለውም፤ የእርሱን ጥቅም የሚያሳካ ከሆነ አምጣ የወለደችውንም እናቱን ሳይቀር አሳልፎ እንደሚሰጥ በቅርብ የሚያውቁት ይናገራሉ።

አሁንም እነ ጸጋዬ አራርሣንና ሕዝቅኤል ገቢሣን የበላቸው ይመስላል። “ፍቅራቸው” ያለቀ፤ ውላቸው የፈረሰ፣ ጋብቻቸው ያከተመ ይመስላል። በቀጣይ ደግሞ “ጤና ይስጥልኝ” ብሎ የተቀላቀለውን የኦፌኮ ፓርቲ መሪን ፕሮፌሰር መረራ ጉዲናን፤ “አልታዘዝም” ካለ ደግሞ በቀለ ገርባን ከመለስ በለመደው ስልት እንደሚቀነጥሳቸው የበፊት “አፈጻጸሙ” ሕያው ምስክር ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “የመረራን ፓርቲ የተቀላቀልኩት የሸዋን ድምጽ ለመሰብሰብ ነው” በማለት ጃዋር የተናገረውን ተመርኮዙ ያወጣውን ሪፖርት ማንበብ ይቻላል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ ባለፈው ሳምንት ጃዋር መሃመድ ኤል ቲቪ ላይ ከቤተልሔም ታፈሰ ጋር ባደረገው ጭውውት “አምባገነን ነህ ወይ?” በማለት ቤተልሔም ላቀረበችለት ጥያቄ “ማንም ሰው አምባገነን ነው” በማለት መመለሱ ይታወሳል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, Middle Column, omn

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule