• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዐቢይ የዘመተው አማራን አስፈጅቶ ጦርነቱ ሲያልቅ ለራሱ ዝና/ኢጎ ነው” የ360 የማክሰኞ አጀንዳ

November 23, 2021 02:35 am by Editor 3 Comments

ከአሸባሪው ትህነግ ጋር የሚደረገውን የመጨረሻ ፍልሚያ አስመልክቶ ጠቅላዩ ይህንን ብለው ወደ ግምባር እንደሚዘምቱ አስታውቀዋል፤

“ጊዜው ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው። ከእንግዲህ እኔ መከላከያን በግንባር ሆኜ ለመምራት ከነገ ጅምሮ ወደ ትግሉ ሜዳ እዘምታለሁ። ታሪክ ከሚያደንቃቸው የኢትዮጵያ ልጆች አንዱ ለመሆን የምታስቡ ሁሉ ለሀገራችሁ ስትሉ ዛሬውኑ ተነሡ፤ ግንባር ላይ እንገናኝ”።

ይህ በዘመናዊ አገላለጽ የተጻፈ ብዙ ጊዜ ሲነገር ከነበረው የአጼ ምኒልክ የክተት ጥሪ ጋር የሚመሳሰል ነው። ጠቅላዩ ቃላቸውን ጠብቀዋል። “አንገቴን እሰጣለሁ እንጂ ተላላኪ መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ አይኖርም” ብለው ነበር። ምቾታቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ወደ ሌላ አገር አልሄዱም። ወይም ደንዝዘው አዲስ አበባ በመቀመጥ እንደነ ጋዳፊ ለመሆን አልፈጉም። በዘመናዊ ታሪክ አገሩን ለመታደግ ወደ ግምባር የዘመተ መሪ በሚል ታሪክ የሚስታውሳቸው ይሆናሉ፤ በጥቅማጥቅም ብለው ለነጭ የሚገዙ የአፍሪካ መሪዎችን ወቃሽ ውሳኔ ነው። ወደድንም ጠላን ጀግና ናቸው።

ይህ ግን የእነ እንትና ሠፈር የሚወደው ዓይነት ውሳኔ አይደለም። ጠቅላዩ ምዕራባውያኑ ከገመቱት አማራጮች የራሳቸውንና ምናልባትም ያልተሄደበትን ሦስተኛውን መንገድ ነው የመረጡት። ለእነ እንትና ግን ይህ በየቀኑ በቱቦ (ዩትዩብ) ለሚለቁት አሉባልታ አፍራሽ ውሳኔ ነው።

እነ እንትና በመረጃ ቲቪ በየቀኑ የሚተፉ የውርደትና የነውር ተምሳሌቶች ናቸው – ኤርሚያስ ለገሠ፣ ሃብታሙ አያሌው፣ ዘመድኩን በቀለ፣ …። አጀንዳ ፈጻሚዎች ናቸው። ለአማራ እንደቆሙ አስመስለው በየዕለቱ መርዝ የሚረጩ የወያኔ ሽርፍራፊ ሳንቲም ለቃሚዎች ናቸው። ከዲጂታል ወያኔ ጋር የዓላማ እና የግብ አንድነት አላቸው – ሁለቱም የሚከተሉት መርህ “እረኛውን ምታ መንጋው ይበተናል” የሚል ነው። ዐቢይን በተቻለ ሁኔታ ቀጥቅጥ፣ በሕዝብ አስጠላው፣ የአማራው ጨፍጫፊ አድርገህ ሳለው፣ … ከዚያ መንጋውን መበተን ይቀልላል።

የማክሰኞው የ360 አዳምጡን ባዮች እና የፖለቲካ ጠንቋዩ ዘመድኩን ውሎ በዐቢይ የመዝመት ውሳኔ ላይ ሆኖ የሚከተሉትን እንደሚሉ መገመት አያዳግትም፤

  • ዐቢይ የዘመተው የራሱን ዝና ከፍ ለማድረግ እና ኢጎ ለማርካት ነው
  • ኤርሚያስ፤ “ለዐቢይ ከምንም በላይ የራሱ ማንነት ይበልጥበታል፤ (ኢየሩስ/ብሩክ) ይህ ከዚህ በፊትም ተናግሬዋለሁ መረን የለቀቀ ናርሲሲዝም ነው፤ አሁን እዘምታለሁ ማለቱ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው፤ ራሱ የጻፈውን መመልከት ይበቃል፤ ለዝና፣ ለመደነቅ ብሎ ይህንን ውሳኔ እንደወሰነ ወደ በኋላ ላይ በአራት ከፍዬ እተነትነዋለሁ …”
  • ሃብታሙ፤ “እኔ ስለዚህ ሰውዬ የምለው ነገር ካጣሁ ቆይቻለሁ፤ እንደው ጠበል የሚወስደው ቢኖር ጥሩ ነው ብዬ ስናገር ማንም የሰማኝ የለም፤ በውነት ኢትዮጵያን ያከለ አገር በዚህ ዓይነት የወረደ ሰው መመራቷ መቀበል የማልችለው የውርደት ውርደት ነው” ይላል ሃብታሙ ኢንተርኔቱ ከሚቋጥበት ቤዝመንት ሆኖ፤
  • ዘመድኩን (ሃሳቡን ባጭሩ መጻፍ የማይችል መጻጉ ስለሆነ እኔም እንደሱ ላርዝመው)፤ “ዐቢይ ይምራን፤ ብልጽግና ተስፋችን ነው (ማሸሞሩ ነው)፤ ስነግርህ ስማ፤ እኔ ዘመዴ እንደሆንኩ የምትፈልገውን ሳይሆን የምትጠላውንና መስማት የማትፈልገውን ነው የምግትህ፤ ዐቢይ ሁለቱን ባለማተቦች አማራና ትግሬን አጣልቶ ኦሮሙማን ለማንገሥ ነው ከነሽመልስ ጋር እየጸለየ የሚሠራው፤ ለሱ ምን ጨነቀው ሃይማኖቱ አይደል፤ ኦርቶዶክስ ሲያፈርስ አማራን ያፈርሳል፣ ኢትዮጵያዊነት አብሮ ይፈርሳል፣ …”

በተለይ የዘመድኩን ነገር የሚገርም ነው። የትህነግ ሽፍቶችን “ባለማተቦች” እያለ ሲጠራቸው ቅንጣት ታህል አይሰቀጥጠውም። ይህንን ባለበት አፉ “ለዋልድባ አባቶች ገንዘብ እናሰባስብ” እያለ የኅሊናውን ወቀሳ ዝም ለማሰኘት የሚታትር የአእምሮ ስንኩል ነው። ቤተመቅደስ ገብቶ ካህናትን በግድ ሥጋ እንዲበሉ የሚያደርገውን፣ የካህን ሚስት ካህኑ ፊት የሚደፍረውን፣ ቤተመቅደስ ውስጥ እጅግ አስነዋሪ ተግባር የሚፈጽመውን፣ አማራውን በጾም በሬውን እያረደና ሥጋ እያስጠበሰ በግድ ብላ የሚል አረመኔ ለዘመድኩን “ባለማተብ” ነው። ለነገሩ ዘመድኩን ከስታሊን ገብረሥላሴ የሚለይበት እርሱ አማራ ነኝ ስለሚል እና ስታሊን ደግሞ ትግሬ ስለሆነ ነው። ከዚያ ሲያልፍ ሁለቱም የመርዝ ብልቃጡ መለስ ዜናዊ አምላኪዎች ነበሩ። ሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ።

እነዚህ እንግዴ ልጆች ዓላማውና ግቡ ምን እንደሆነ ግልጽ ባልሆነው የመረጃ ቲቪ እየቀረቡ የከረፋ ትፋታቸውን ይተፋሉ። ይችኑ ጠቅላዩን የማዋረድና የመንቀፍ አባዜያቸውን ልቡ ለታወረው ቴዎድሮስ ጸጋዬ ያቀብሉታል። እየተናበቡ አድማሳቸውን በማስፋት አማራን የሚደግፉና የሚጨነቁለት መስለው የሚቀበርበትን ጉድጓድ በየቀኑ ይምሱለታል። በእነርሱና መሰል ከንቱዎች አማራው ተከፋፍሎ ይኸው ለትህነግ ጥቃት ፍጹም ተጋላጭ ሆነ። አፋርም ተጠቅቷል። ነገርግን እንደ አማራው በነዘመድኩን እና ሃብታሙ ዓይነት ደናቁርት ስላልተከፋፈለ የአፋር ምድር ለትህነግ ረመጥ ሆነበት።

አንዲት ነገር እንደ ማሳሰቢያ ልስጣቸውና ላብቃ፤ በማክሰኞው የዐቢይ ወቀጣ ላይ ሌላ የሚወቀጥ ሰው ላቀብላችሁ – የአብኑ አቶ ክርስቲያን ታደለ! የጠቅላዩን ውሳኔ ተከትለው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና የአብን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ይህንን ነው ያሉት፤ “ለአገር አንድነትና ለሕዝብ ደኅንነት የምንሰስተው ሕይወት የለምና እኛም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዘምታለን። ሕዝቤ ሆይ ተከተል!”

አደራ ክርስቲያንንም አብራችሁ መውቀጡን እንዳትረሱ በተለይ “ባለማተቡ” ዘመድኩን እንዳትረሳ።

ለገሠ በቀለ     

“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Opinions Tagged With: ermias legesse, habtamu ayalew, operation dismantle tplf, zemedkun bekele

Reader Interactions

Comments

  1. Ashebir says

    November 23, 2021 09:01 am at 9:01 am

    ለግሰ በቀለ

    እነ ኤርምያስን የሚየሳስቱዋቸው እነማን መሰሉህ? “መንግሥት ወታደሮቹን አፈግፍጉ እያለ.በጁንታው ለምን ያስፈጀናል? እኛን ማጥፋት ፍልጎ ከሆነ፤ በአውሮፕላን ከላይ ቦንብ ጥሎ በቀላሉ ቢጨርሰን አይሻልም ወይ? እያሉ የሚቀልዱትን ከቁም ነገር እየቆጠሩ ነው። አይመስልም?

    Reply
  2. birru says

    November 23, 2021 02:03 pm at 2:03 pm

    የጠ/ሚ ጉዳይ ግራ እሚያጋባ ነው። ግንባር ሂደው ምን ሊሰሩ ? በዚህ ቀውጢ ጊዜ ባንከር ውስጥ ቁጭ ብለው የጦር መሀንዲሶቻቸዉን ይዘው፣የተበላሸውን ማስተካከል ሲገባ በግንባር መገኘት አደጋ መጋበዝ ይመስለኛል። በእኔ ግምት የጦርነቱ አጀማመር የተዋጣለት ነበር እላለሁ።እየቆየ የተበላሸው ለአፈጻጸሙ ትኩረት ባለመስጠቱና በሚገባ ባለመታቀዱ ይመስለኛል። ፈረንጆቹ “It is not how you start but how you finish” ይላሉ። የዶ/አቢይ አመራር አስቀድሞ ባዘጋጀው የኤርትራ ወዳጅነት ለዚህ ጦርነት ‘ ተስፈንጣሪ ‘ ጉልበት ሲያገኝ፣ ጦርነቱን በድልና በክብር ለመጨርስ ግን በብዙ የሚያሳፍሩ ምክንያቶች ሊጓተት ችሏል። የወያኔ ቅሬት የሆነው የዘር ተውሳክ ተጠራርጎ ከሰራዊቱ ዉስጥ ከጠፋ ዶ/ር አቢይ፣ ሌላ አድዋን የሚፈጥር አርሚ እንደሚገኙ አልጠራጠርም።

    Reply
  3. Ashebir says

    November 29, 2021 11:56 am at 11:56 am

    ከዚህ ጦርነት ጋር በተያያዘ፤ ካደርጓችው አስደናቂ ነገሮች፣- የዶ{ር አቢይ የሰሜን እዝ ሲጠቃ፡ ፓርላማ ቀርበው “እስከሚጨፈጭፉን አልነካናቸውም” ሲሉ፤ እንዴ! እስከምትጨፈጨፍ ምን ታደርግ ነበር? ብሎ የጠየቃቸው የለም። በግሌ እኔን ያሳቀኝ፣ ትግራይን ሲለቁ ተኩስ አቁሜአለሁ አገርም ለቅቄአለሁ አሉ። አገሩን ስትለቁ ተኩሱ እንደሚቆም የታውቀ ነውና ተኩስ አቁሜአለሁ ማለቱ ምን አስፈለገ? ብሎ የጠየቀ የለም። ከሁሉ የሚያስደንቀው ደግሞ “ወያኔ አመድ ሆኖ በኗል” ባሉ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ወደፓርላማ መጥተው ይህንኑ ፓርልማ ቀርበው በሽብርተኝነት ፈርጁልኝ ሲሉ፤ ምነው አመድ ሆኗል ብለው አልነበረም? ምን መጣ? ብሎ የጠየቀ የለም። ሌላም ደግሞ፤ የክተት አዋጅ አውጀው፤ ዋል አደር ብለው አንድ የስንዴ ማሳ እየጎበኙ ሳለ፤ ታጠቅ፤ ዝመት እትዮጵያ አያስፈልጋትም፤ ትራክተር፤ ማረሻ… ወዘተ ነው የሚያስፈልጋት ብለው ቁጭ አሉ። ማንም ምንም ያለ የለም። በመጨረሻ ቱመትኩ አሉና ቁጭ አሉ። ቀጥሎ ስየሚባለው መተንበይ አይቻልም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule