ጉብኝቱ “ከHR 128 … ውጪ ሊሆን አይችልም” ኦባንግ የአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል ሴናተር ጀምስ ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ በአዲስ አበባ ላይ ከኢህአዴግ ሹሞች ጋር መከሩ። አቶ ኦባንግ ሜቶ ጉብኝቱ “ከHR 128 የተያያዘ ነው፤ ከዚህ ውጪ ሊሆን አይችልም” ይላሉ። በያዝነው የአውሮጳውያን ዓመት (2017) መጀመሪያ አካባቢ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው የነበሩት ሴናተር ጀምስ ኢንሆፍ ከከፍተኛ የሕወሓት/ኢህአዴግ ሹሞች ጋር መነጋገራቸው ህወሓት የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የዜና አገልግሎቱ ውይይቱ መቼ እንደተደረገ ባይዘግብም ዜናውን ግን ጥቅምት 2/2010 በማለት ነው ያተተው። በውይይቱ ላይ ሴናተሩ ሌሎች የአሜሪካ እንደራሴዎችንና የሕግ መወሰኛ ምክርቤት አባላትን በመምራት እንደተገኙ ዜናው አስታውቋል። የውይይቱ ትኩረትም “በሠላምና ጸጥታ … [Read more...] about የሴናተር ኢንሆፍ ህወሓትን የመታደግ ዘመቻ ቀጥሏል!
Archives for October 2017
“ኢትዮጵያ ኬኛ፣ ጣና ኬኛ!” ድንቅ መንፈስ!
"ጣና ኬኛ!" መልዕክቱ ከእንቦጭ አረሙ በላይ ነው የመለያየትና የመፈራረስን አደጋ ያከሸፈ መንፈስ ከኦሮሚያ "ጣና ኬኛ!" እያለ የተመመው ወጣት ክፉውን የእንቦጭን አረም ነቃቅሎ እንደማያስወግድ ግልጽ ነው። ጥቂት ወጣቶች ተሸክመውት ጎጃም የገቡት የኢትዮጵያዊነት የአብሮነት የ"አንድ ነን" ግን መልዕክቱ ግን የእንቦጭ ተራ አረም አይደለም ኢትዮጵያን የማስወገድና የመታደግ መንፈስ የታመቀ መንፈስ አለው። ዛሬ ያየሁት ፍቅር፣ ዛሬ ያየሁት የአብሮነት፣ የህብረትና የአንድነት መንፈስ ከሰፊው የጣናን እንቦጭ አረም በላይ ነው። "ጣና ኬኛ!" ብሎ ጎጃም የገቡትን ወጣቶች አደግድጎ በክብር ኩራት፣ በአባት አደር ወጉ ወገኖቹን ከደብረ ማርቆስ እየተቀበለ ተመልክተናል። ይቀጥልና እስከ ባህር ዳር ቄጠማ እያነጠፈ ለመቶ እንግዶቹ እልፍ አዕላፉ ለአቀባበሉ የሚያሸረግደ እንግዶቹን የሚቀበልበት … [Read more...] about “ኢትዮጵያ ኬኛ፣ ጣና ኬኛ!” ድንቅ መንፈስ!
The TPLF: An Unreliable Ally in the War Against Terror
Congress should pass H.R. 128 and the Senate should pass S.R. 168. Neither should succumb to the deceptive games of the TPLF and SGR lobbying group! As a member of AMISOM TCC (African Union Mission in Somalia Troop Contributing Countries), the TPLF regime in Ethiopia has shamelessly used the war on terror to enrich its generals at the expense of thousands of poor Ethiopian troops. Based on accounts of the families of soldiers who fought Al Shabab for years, a substantial portion of the … [Read more...] about The TPLF: An Unreliable Ally in the War Against Terror
አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ?
የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው የዘመኑ “ሚዲያ” የአባዱላን ከአፈጉባኤነት መልቀቅ በሰበር ዜናነት ማናፈሱ ቆም ብሎ ላየው ራስን ትዝብት ላይ የሚጥል ነው። የአባዱላ መልቀቂያ ማስገባት “ምስጢር” በቅርቡ የሚለይለት ቢሆንም በህወሓት ተለክቶና ተጠፍጥፎ የተሠራ ድርጅትና ስብዕና ያለው ለዚህ ዓይነት የሞራል ልዕልና ይደርሳል ብሎ መገመት ህወሓትን ካለማወቅ ወይም ራስን ከመሳት የሚመነጭ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። በበርካታ የሙስና ተግባራትና ህይወት ማጥፋት አለበት እየተባለ የሚነገርለት አባዱላ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት ተማርኮ በሻዕቢያ ፈቃድና በህወሓት ፈጣሪነት አዲስ ስብዕና ተሰጥቶት ኦህዴድ የሚባል የጀመረ መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። ይህ ስብዕናው ህወሓት በህንፍሽፍሽ ልትበታተን ስትል የኦሮሞውን ክንፍ ይዞ መለስን የታደገ በመሆኑ ባለውለታነቱ ለማን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ … [Read more...] about አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ?
የአባዱላ መጨረሻ
አቶ አባዱላ ገመዳ ከሁለት ሳምንታት በፊት ለዓመታት ከተቀመጡበት የአፈ ጉባኤነት መንበር ላይ ለመልቀቅ መጠየቃቸው ከባለፈው ሳምንት ማብቂያ ጀምሮ ዋነኛ ርዕስ ሆኖ ዘልቋል። ከፓርቲያቸው ኢህአዴግ/ኦህዴድ እንዲሁም ከእራሳቸው አንደበት ዜናውን ለማስተባበል የተሰማ ነገር ስለሌለ ሥልጣን ለመልቀቅ መጠየቃቸው ሃቅ ወደ መሆኑ ያመዘነ በነበረበት ጊዜ ጥያቄ የማቅረባቸውን እውነትነት እራሳቸው አረጋጥጠዋል። ወታደራዊው መንግሥት አባዱላ መስራችና አባል የሆኑበት ኦህዴድ በሚገኝበት ኢህአዴግ ተሸንፎ ከተወገደበት ጊዜ አንስቶ በተለያዩ የወታደራዊና የሲቪል ሃላፊነቶች ላይ ቆይተዋል። አባዱላ ከትግል በኋላ ፓርቲውን የተቀላቀሉ በርካታ አመራሮች ባሉበት ኦህዴድ ውስጥ ተቀባይነት ካላቸው ቀደምት ጥቂት መስራች አባላት ውስጥ ቀዳሚው እንደሆኑ ይነገራል። ለዚህም ይመስላል በርካታ የኦህዴድ አባላትና … [Read more...] about የአባዱላ መጨረሻ
“እስከማውቀው አባዱላ በዚህ መልኩ አይዳፈሩም”፤ አባዱላ እና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እዉነት
በኦህዴድ አባላት ዘንድ “ጃርሳው” የሚል መጠሪያ ያላቸው አባዱላ ገመዳ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሰለቻቸው ከፍተኛ አመራሮች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱ ናቸው። "ንፍሮ እየበላሁ ከተራው ህዝብ ጋር መኖር ናፈቀኝ፤ ወደ ቤተ ክርስቲያን በነጻነት የምሄድበት ቀን መቼ ነው?" በማለት ለሚቀርቧቸው ሲናገሩ መቆየታቸውን በቅርብ የሚያውቋቸው ምስክርነት ይሰጣሉ። የጦር ሰራዊት መለዮ አውልቀው መከላከያ ሚኒስትር፣ ከዛም የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው የተሰየሙት አባዱላ፣ በኢህአዴግ አመራሮች የማይደፈሩ ቦታዎች ድረስ ዘልቀው በመግባት ከህዝብ ጋር በተደጋጋሚ የመከሩ፣ ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ከመጣ ጀምሮ ኦሮሚያ ላይየተሻለ ተቀባይነት ያገኙ ናቸው። በአቶ ደራራ ሞት እጃቸው አለበት በሚል የሚከሷቸው ያሉትን ያህል፣ በባህሪያቸው ሩህሩህ እንደሆኑ በቅርብ የሚያውቋቸው ይናገራሉ። አርሲና ባሌን … [Read more...] about “እስከማውቀው አባዱላ በዚህ መልኩ አይዳፈሩም”፤ አባዱላ እና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እዉነት
ሽሽት እና አባዱላ ገመዳ
ከሰሜን እና ከበስተ-ምስራቅ አቅጣጫ እየነፈሰ ያለው አውሎንፋስ መርከብዋን እያናጋት ይገኛል። ጫፍ ላይ ጉብ ያሉትን አስተናጋጆች እያንጠባጠበ የሚገፋው ሃይል እየበረታ መጥቶ፣ አሁን ከካፒቴኑ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ይመስላል። ይህ ሁላችንንም የሚያስማማን መራራ ሃቅ ነው። ችግሩ እዚህ ላይ አይደለም። ግን ... እየሰመጠ ካለው ከዚህ መርከብ ለማምለጥ የተገኘችውን ቀዳዳ እየተጠቀሙ የሚሾልኩትን ሁሉ "ጀግና" ብለን ለመጥራት እንደምን ይዳዳን? ራስን ማዳን እና ሃገርን ማዳን፤ በሰማይና በምድር መሃከል ያለ ርቀትን ያህል የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ዘንግተነው ከሆነ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህ ስራዓት "በስብሷል" ብሎ ከተናገረ 10 አመታት አልፈውታል። ከ 26 ዓመታት በኋላ ደግሞ እነሆ ህወሃት ከርፍቶ መርገፍ ጀመረ። ችግሮቹ ግን እጅግ እየተባባሱ እንጂ እየተሻሻሉ አልመጡም። ይህ ስርዓት ዛሬ … [Read more...] about ሽሽት እና አባዱላ ገመዳ
Chinese Investments in Africa: “Chopsticks Mercantilism”
In the early parts of the 21st century, China became an important source of finance for African development. The continent’s infrastructure was in disrepair; it had crumpled after decades of abject neglect and destruction from senseless civil wars. A substantial investment was – and still – needed to rebuild this infrastructure. According to a World Bank Report (2009), “the poor state of infrastructure in Sub-Saharan Africa—its electricity, water, roads and information and communications … [Read more...] about Chinese Investments in Africa: “Chopsticks Mercantilism”
አገርን ከጥፋት ህዝብን ከፍጅት ለማዳን ዛሬውኑ በጋራ እንነሳ
በአገራችን ውሰጥ የሰፈነው ከፋፋይ ሥርዓት እነሆ ህዝባችንን እርስ በርስ የሚያጋጭና የአገሪቱንም አንድነት ከፍተኛ አደጋ ላይ የጣለበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። ሕዝባችን በየዕለቱ ከአንድ ቀውስ ወደ ሌላ ቀውስ እየተሸጋገረ ይገኛል። የቀውሱ አድማስም በአንድ ቦታ የተወሰነ ሳይሆን በየጊዜው እየሰፋ ትላንት ሰላም ነው ይባል የነበረን ቦታ ዛሬ የቀውስ ማዕከል እያደረገው ሁሉንም የኅብረተሰባችንን ክፍል፣ ሁሉንም ቋንቋ ተናጋሪ እየነካ ይገኛል። በቀላል አነጋገር አገሪቱ ከዳር አስከ ዳር በቀውስ አየተናጠች መሆኗ በገሃድ አየታየ ነው። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ላለፉት 26 ዓመታት ሲካሄድ የቆየውን አመቃ፣ ምዝበራና ንቅዘት በመቃወም የተነሳው ህዝባዊ አንቅስቃሴ በዋናነት የሚጠቀስ ሲሆን፣ ይህን ተቃውሞ ተከትሎ የተከሰተው የሥርዓቱ ውስጣዊ መፈራረስ ያስከተለው መዘዝ መሆኑን መታዘብ ይቻላል። የዚህ ሁሉ … [Read more...] about አገርን ከጥፋት ህዝብን ከፍጅት ለማዳን ዛሬውኑ በጋራ እንነሳ
የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ፣ ተግዳሮቶቹና የመፍትሄ ኣሳብ
የሰው ልጅ ማህበራዊና ግላዊ ተፈጥሮ ስላለው ለማህበራዊ ኑሮውና ለግላዊ ኑሮው የተለያዩ ጠገጎችን እያበጀ ይኖራል። እነዚህ የሚሰራቸው ጠገጎች ለግል ህይወቱም ሆነ ለማህበራዊ ህይወቱ ወሳኝ ናቸው። ሰው የዚህን ዓለም ኑሮውን ለመግፋት ከሚያስችሉት መሳሪያዎች ኣንዱ እነዚህ ጠገጎቹ ናቸው። የሰው ልጅ በህይወቱ የሚፈጥራቸው እነዚህ ጠገጎች ሃይማኖታዊ ወይም ባህላዊ ወይም ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ትርፍ ያስገኙለታል። ታዲያ ይህ የሰው ልጅ በዓለም ላይ ከሚፈጥራቸው ጠገጎች መሃል ከፍተኛውና ጠንካራው ሃገር የሚባለው ጠገጉ ነው። በርግጥ ከዚህ ኣልፎ ዛሬ ጊዜ ሌላ ከፍ ያለ የጋራ የዓለም ጠገግ ህዝቦች ኣበጅተው ስያሜውን ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ብለውታል። ነገር ግን የሰው ልጅ ከቀን ተቀን ህይወቱ ጋር በጣም የተሳሰረው ጠገግ አገር ሲሆን ለዚህ ጠገግ የተለያዩ ስምምነቶችን ኣስፍሮ በዚህ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ፣ ተግዳሮቶቹና የመፍትሄ ኣሳብ