• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኢትዮጵያ ኬኛ፣ ጣና ኬኛ!” ድንቅ መንፈስ!

October 12, 2017 08:26 pm by Editor 3 Comments

  • “ጣና ኬኛ!” መልዕክቱ ከእንቦጭ አረሙ በላይ ነው

  • የመለያየትና የመፈራረስን አደጋ ያከሸፈ መንፈስ

ከኦሮሚያ “ጣና ኬኛ!” እያለ የተመመው ወጣት ክፉውን የእንቦጭን አረም ነቃቅሎ እንደማያስወግድ ግልጽ ነው። ጥቂት ወጣቶች ተሸክመውት ጎጃም የገቡት የኢትዮጵያዊነት የአብሮነት የ”አንድ ነን” ግን መልዕክቱ ግን የእንቦጭ ተራ አረም አይደለም ኢትዮጵያን የማስወገድና የመታደግ መንፈስ የታመቀ መንፈስ አለው። ዛሬ ያየሁት ፍቅር፣ ዛሬ ያየሁት የአብሮነት፣ የህብረትና የአንድነት መንፈስ ከሰፊው የጣናን እንቦጭ አረም በላይ ነው።

“ጣና ኬኛ!” ብሎ ጎጃም የገቡትን ወጣቶች አደግድጎ በክብር ኩራት፣ በአባት አደር ወጉ ወገኖቹን ከደብረ ማርቆስ እየተቀበለ ተመልክተናል። ይቀጥልና እስከ ባህር ዳር ቄጠማ እያነጠፈ ለመቶ እንግዶቹ እልፍ አዕላፉ ለአቀባበሉ የሚያሸረግደ እንግዶቹን የሚቀበልበት ምክንያት ከጣና እንቦጭ በላይ የኢትዮጵያዊ መንፈስ ትንሳኤን ሲያበስረን መሆኑ ዛሬ በፈንጠዝያው መካከል ካልገባን፣ ነገ እውነቱ ሲገለጥልን ይገባናል!

“ጣና ኬኛ፣ ኢትዮጵያ ኬኛ” ይልሃል፣ ለአመታት ጀግናው ብርቱው ወገን … የተሸረበበትን የመነጣጠል መለያየት፣ የአድልኦ መንፈስ አሽቀንጥሮ፣ እንደ ስፖርቱ በአንዲት ሀገር ባንዴራ ማዕቀፍ ተከባብረን ተዋደን እንኖር ዘንድ ህዝብ መናገር፣ መመስከርና ማበሩን አላቆመም። የጎጃም ወገናቸው በነቂስ ወጥቶ ድጋፉን መስጠቱን የመመልከቱ ድንቅ የህብረት መንፈስ ትርጉሙ ከፍ ያለ ሀገራዊ መልክ አለው። በእርግጥም ለ200 ወጣት የኦሮሚያ ግዛት ተጓዥ በጎ ፈቃድ አድራጊ የጎጃም እንግዳ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞው ወጣት የጎጃም ወጣት ሽማግሌ በነቂስ ወጥቶ በክብር የተቀበለበት ሚስጥሩ ለመሰጠረው ግዙፍ ነው። ለእኔ ኢትዮጵያዊው ኦሮሞና አማራው ለአመታት በክፉዎች ከጫፍ እስከ ጫፍ የተረጨበትን የመለያየት መርዝ ስለማክሸፉ ምልክት ነው።

በህዝቦች መካከል ያለው፣ የቆየ የመደጋገፍ መንፈስ ይታይ ዘንድ ከጣናው የእንቦጭ አረም ከፍ ባለ ደረጃ ዛሬ ታይቷል። ክፉዎች ተስፋ ይቆርጡ ዘንድ ኢትዮጵያዊው ኦሮሞ “ጣና ኬኛ” ዘመቻ እያለ ጎጃም ሲገባ ህዝቡ በክፉ በደጉ እንደማይለያይና ህብረትና አንድነቱን ናፋቂ መሆኑን ማሳያ ሆኖናል። በእርግጥም በጣም ጥቂት ወጣቶች በአሸናፊነት መንፈስ ከኦሮሚያ ተመው ጎጃም ሲገቡ የጎጃም ሕዝብ በአንጻሩ መልዕክቱ ደርሶታል። ጎጃሜው ታጥቆ አሸርግዶ የኦሮሞ ወጣት ወንድም እህቱን  በክብር በባህላዊ እስክታ፣ ሆታ ጭፈራ ተቀብሏል። የአቀባበሉ መንፈስ ደግሞ የኢትዮጵያውያን አንድነት፣ የኢትዮጵያውያን የህብረት አብሮነት ፍላጎት ማሳያ ግልጽ መልዕክት ይመስለኛል።

ይህ የአብሮነት መንፈስ ደግሞ እነሆ የኢትዮጵያን ትንሳኤ መልክት ነው። ተስፋችን በሚሰራው ስራ ብን ብሎ ሲጠፋ “ኢትዮጵያ እንደሁ አትጠፋም!” የምንለውን አራቂ መንፈስ አስታውሶ ኢትዮጵያ በልጆቿ ህብረት እንደማትጠፋ በእውን ያሳየን መልዕክት ነው! የኦሮሞ ወጣቶች በጎ መንፈስና የጎጃም አማራው የአቀባበል ደስታ ፌሽታ ስነስርአትን ላስተዋለው የኢትዮጵያዊነት የህብረት አንድነቱን መንፈስ እንመሰክር ዘንድ ያስገድደናል። ይህ ግዙፍ መንፈስ ጣናን ከወረረውን እንቦጭ በላይ ስለ ከበበን ስለወረረን በጎ ተስፋ ሰጭ መንፈስ ይናገራል! ለአመታት ያንዣበብንን የመለያየት የመፈራረስ አደጋ ዛሬ በ200 በጎ አድራጊ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ ወጣቶች የከሸፈን ያህል ተደስተናል። ብቻ “በጣና ኬኛ” ድንቅ ዘመቻ ነፍሴ ከፍ ያለ ደስታን አግኝታለች!

“ኢትዮጵያ ኬኛ፣  ጣና ኬኛ …!” ድንቅ መንፈስ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ነቢዩ ሲራክ

ጥቅምት 3 ቀን 2010 ዓም

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    October 14, 2017 06:19 am at 6:19 am

    ሆ ብሎ ገባ ! አረም ቢወረው
    ያን ፌሶ ጥሊያን እንዲህ የነቀለው
    የአባቱን ጅብዱ በልጁ ዘመን የደገመው
    ልዩነህ ሲሉት አንድ ነን አለ መጣ እያገሳ
    የኢትዮጵያ ልጆች ይኽው ገጠሙ መሳ ለመሳ
    ጭፈራው ባሕል ቋንቋቸው ሀገር
    እምነታቸው ጽኑ ዓለም ምሥክር
    ወያኔ እና አረም አንድ እንቦጭ
    እንቦጭ ውሃ ህወሓት ደም መጣጭ
    ንቀል ጣል አለ መብቱን አወቀ ጣና ኬኛ
    ጨዋታው ደራ ውሉ ታወቀ ኢትዮጵያ ኬኛ!
    ፍቅር ሠላም ኅብረት ይበጀናል ለእኛ ።
    ***************
    ሥለሀገራቸው ደህንነት የሕዝብ አብሮ መኖር ቅን ያሰቡ ቀናው ይግጠማቸው!
    ከሸረኛ ምቀኛ ከፋፋይ አመጸኛ ተንኮለኛ ይሰውራቸው
    በቸር ይክረሙ።

    Reply
  2. Lemma says

    October 14, 2017 06:50 pm at 6:50 pm

    Endih yale Tiru melikt beergata metsaf neberebet.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    October 14, 2017 10:24 pm at 10:24 pm

    ጣና! ጣና!! አረ ጣና!!
    ያባይ ውልድ ያማራ ምንጭ ስብዕና
    በዕምቦጭ ተወረረ ይሉናል?? ወይ ፈተና!!!!
    ከሞኝ ሰፈር
    ይቆረጣል ሞፈር!!
    ወጣቱን ለቮሊንተር
    ብታሰልፈው ጥሩ ነበር
    ልብህ ባይቃዥ በሌላው አፈር!!
    ምንም ነውር የለውም መማማር!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule