• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኢትዮጵያ ኬኛ፣ ጣና ኬኛ!” ድንቅ መንፈስ!

October 12, 2017 08:26 pm by Editor 3 Comments

  • “ጣና ኬኛ!” መልዕክቱ ከእንቦጭ አረሙ በላይ ነው

  • የመለያየትና የመፈራረስን አደጋ ያከሸፈ መንፈስ

ከኦሮሚያ “ጣና ኬኛ!” እያለ የተመመው ወጣት ክፉውን የእንቦጭን አረም ነቃቅሎ እንደማያስወግድ ግልጽ ነው። ጥቂት ወጣቶች ተሸክመውት ጎጃም የገቡት የኢትዮጵያዊነት የአብሮነት የ”አንድ ነን” ግን መልዕክቱ ግን የእንቦጭ ተራ አረም አይደለም ኢትዮጵያን የማስወገድና የመታደግ መንፈስ የታመቀ መንፈስ አለው። ዛሬ ያየሁት ፍቅር፣ ዛሬ ያየሁት የአብሮነት፣ የህብረትና የአንድነት መንፈስ ከሰፊው የጣናን እንቦጭ አረም በላይ ነው።

“ጣና ኬኛ!” ብሎ ጎጃም የገቡትን ወጣቶች አደግድጎ በክብር ኩራት፣ በአባት አደር ወጉ ወገኖቹን ከደብረ ማርቆስ እየተቀበለ ተመልክተናል። ይቀጥልና እስከ ባህር ዳር ቄጠማ እያነጠፈ ለመቶ እንግዶቹ እልፍ አዕላፉ ለአቀባበሉ የሚያሸረግደ እንግዶቹን የሚቀበልበት ምክንያት ከጣና እንቦጭ በላይ የኢትዮጵያዊ መንፈስ ትንሳኤን ሲያበስረን መሆኑ ዛሬ በፈንጠዝያው መካከል ካልገባን፣ ነገ እውነቱ ሲገለጥልን ይገባናል!

“ጣና ኬኛ፣ ኢትዮጵያ ኬኛ” ይልሃል፣ ለአመታት ጀግናው ብርቱው ወገን … የተሸረበበትን የመነጣጠል መለያየት፣ የአድልኦ መንፈስ አሽቀንጥሮ፣ እንደ ስፖርቱ በአንዲት ሀገር ባንዴራ ማዕቀፍ ተከባብረን ተዋደን እንኖር ዘንድ ህዝብ መናገር፣ መመስከርና ማበሩን አላቆመም። የጎጃም ወገናቸው በነቂስ ወጥቶ ድጋፉን መስጠቱን የመመልከቱ ድንቅ የህብረት መንፈስ ትርጉሙ ከፍ ያለ ሀገራዊ መልክ አለው። በእርግጥም ለ200 ወጣት የኦሮሚያ ግዛት ተጓዥ በጎ ፈቃድ አድራጊ የጎጃም እንግዳ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞው ወጣት የጎጃም ወጣት ሽማግሌ በነቂስ ወጥቶ በክብር የተቀበለበት ሚስጥሩ ለመሰጠረው ግዙፍ ነው። ለእኔ ኢትዮጵያዊው ኦሮሞና አማራው ለአመታት በክፉዎች ከጫፍ እስከ ጫፍ የተረጨበትን የመለያየት መርዝ ስለማክሸፉ ምልክት ነው።

በህዝቦች መካከል ያለው፣ የቆየ የመደጋገፍ መንፈስ ይታይ ዘንድ ከጣናው የእንቦጭ አረም ከፍ ባለ ደረጃ ዛሬ ታይቷል። ክፉዎች ተስፋ ይቆርጡ ዘንድ ኢትዮጵያዊው ኦሮሞ “ጣና ኬኛ” ዘመቻ እያለ ጎጃም ሲገባ ህዝቡ በክፉ በደጉ እንደማይለያይና ህብረትና አንድነቱን ናፋቂ መሆኑን ማሳያ ሆኖናል። በእርግጥም በጣም ጥቂት ወጣቶች በአሸናፊነት መንፈስ ከኦሮሚያ ተመው ጎጃም ሲገቡ የጎጃም ሕዝብ በአንጻሩ መልዕክቱ ደርሶታል። ጎጃሜው ታጥቆ አሸርግዶ የኦሮሞ ወጣት ወንድም እህቱን  በክብር በባህላዊ እስክታ፣ ሆታ ጭፈራ ተቀብሏል። የአቀባበሉ መንፈስ ደግሞ የኢትዮጵያውያን አንድነት፣ የኢትዮጵያውያን የህብረት አብሮነት ፍላጎት ማሳያ ግልጽ መልዕክት ይመስለኛል።

ይህ የአብሮነት መንፈስ ደግሞ እነሆ የኢትዮጵያን ትንሳኤ መልክት ነው። ተስፋችን በሚሰራው ስራ ብን ብሎ ሲጠፋ “ኢትዮጵያ እንደሁ አትጠፋም!” የምንለውን አራቂ መንፈስ አስታውሶ ኢትዮጵያ በልጆቿ ህብረት እንደማትጠፋ በእውን ያሳየን መልዕክት ነው! የኦሮሞ ወጣቶች በጎ መንፈስና የጎጃም አማራው የአቀባበል ደስታ ፌሽታ ስነስርአትን ላስተዋለው የኢትዮጵያዊነት የህብረት አንድነቱን መንፈስ እንመሰክር ዘንድ ያስገድደናል። ይህ ግዙፍ መንፈስ ጣናን ከወረረውን እንቦጭ በላይ ስለ ከበበን ስለወረረን በጎ ተስፋ ሰጭ መንፈስ ይናገራል! ለአመታት ያንዣበብንን የመለያየት የመፈራረስ አደጋ ዛሬ በ200 በጎ አድራጊ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ ወጣቶች የከሸፈን ያህል ተደስተናል። ብቻ “በጣና ኬኛ” ድንቅ ዘመቻ ነፍሴ ከፍ ያለ ደስታን አግኝታለች!

“ኢትዮጵያ ኬኛ፣  ጣና ኬኛ …!” ድንቅ መንፈስ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ነቢዩ ሲራክ

ጥቅምት 3 ቀን 2010 ዓም

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    October 14, 2017 06:19 am at 6:19 am

    ሆ ብሎ ገባ ! አረም ቢወረው
    ያን ፌሶ ጥሊያን እንዲህ የነቀለው
    የአባቱን ጅብዱ በልጁ ዘመን የደገመው
    ልዩነህ ሲሉት አንድ ነን አለ መጣ እያገሳ
    የኢትዮጵያ ልጆች ይኽው ገጠሙ መሳ ለመሳ
    ጭፈራው ባሕል ቋንቋቸው ሀገር
    እምነታቸው ጽኑ ዓለም ምሥክር
    ወያኔ እና አረም አንድ እንቦጭ
    እንቦጭ ውሃ ህወሓት ደም መጣጭ
    ንቀል ጣል አለ መብቱን አወቀ ጣና ኬኛ
    ጨዋታው ደራ ውሉ ታወቀ ኢትዮጵያ ኬኛ!
    ፍቅር ሠላም ኅብረት ይበጀናል ለእኛ ።
    ***************
    ሥለሀገራቸው ደህንነት የሕዝብ አብሮ መኖር ቅን ያሰቡ ቀናው ይግጠማቸው!
    ከሸረኛ ምቀኛ ከፋፋይ አመጸኛ ተንኮለኛ ይሰውራቸው
    በቸር ይክረሙ።

    Reply
  2. Lemma says

    October 14, 2017 06:50 pm at 6:50 pm

    Endih yale Tiru melikt beergata metsaf neberebet.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    October 14, 2017 10:24 pm at 10:24 pm

    ጣና! ጣና!! አረ ጣና!!
    ያባይ ውልድ ያማራ ምንጭ ስብዕና
    በዕምቦጭ ተወረረ ይሉናል?? ወይ ፈተና!!!!
    ከሞኝ ሰፈር
    ይቆረጣል ሞፈር!!
    ወጣቱን ለቮሊንተር
    ብታሰልፈው ጥሩ ነበር
    ልብህ ባይቃዥ በሌላው አፈር!!
    ምንም ነውር የለውም መማማር!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule