• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኢትዮጵያ ኬኛ፣ ጣና ኬኛ!” ድንቅ መንፈስ!

October 12, 2017 08:26 pm by Editor 3 Comments

  • “ጣና ኬኛ!” መልዕክቱ ከእንቦጭ አረሙ በላይ ነው

  • የመለያየትና የመፈራረስን አደጋ ያከሸፈ መንፈስ

ከኦሮሚያ “ጣና ኬኛ!” እያለ የተመመው ወጣት ክፉውን የእንቦጭን አረም ነቃቅሎ እንደማያስወግድ ግልጽ ነው። ጥቂት ወጣቶች ተሸክመውት ጎጃም የገቡት የኢትዮጵያዊነት የአብሮነት የ”አንድ ነን” ግን መልዕክቱ ግን የእንቦጭ ተራ አረም አይደለም ኢትዮጵያን የማስወገድና የመታደግ መንፈስ የታመቀ መንፈስ አለው። ዛሬ ያየሁት ፍቅር፣ ዛሬ ያየሁት የአብሮነት፣ የህብረትና የአንድነት መንፈስ ከሰፊው የጣናን እንቦጭ አረም በላይ ነው።

“ጣና ኬኛ!” ብሎ ጎጃም የገቡትን ወጣቶች አደግድጎ በክብር ኩራት፣ በአባት አደር ወጉ ወገኖቹን ከደብረ ማርቆስ እየተቀበለ ተመልክተናል። ይቀጥልና እስከ ባህር ዳር ቄጠማ እያነጠፈ ለመቶ እንግዶቹ እልፍ አዕላፉ ለአቀባበሉ የሚያሸረግደ እንግዶቹን የሚቀበልበት ምክንያት ከጣና እንቦጭ በላይ የኢትዮጵያዊ መንፈስ ትንሳኤን ሲያበስረን መሆኑ ዛሬ በፈንጠዝያው መካከል ካልገባን፣ ነገ እውነቱ ሲገለጥልን ይገባናል!

“ጣና ኬኛ፣ ኢትዮጵያ ኬኛ” ይልሃል፣ ለአመታት ጀግናው ብርቱው ወገን … የተሸረበበትን የመነጣጠል መለያየት፣ የአድልኦ መንፈስ አሽቀንጥሮ፣ እንደ ስፖርቱ በአንዲት ሀገር ባንዴራ ማዕቀፍ ተከባብረን ተዋደን እንኖር ዘንድ ህዝብ መናገር፣ መመስከርና ማበሩን አላቆመም። የጎጃም ወገናቸው በነቂስ ወጥቶ ድጋፉን መስጠቱን የመመልከቱ ድንቅ የህብረት መንፈስ ትርጉሙ ከፍ ያለ ሀገራዊ መልክ አለው። በእርግጥም ለ200 ወጣት የኦሮሚያ ግዛት ተጓዥ በጎ ፈቃድ አድራጊ የጎጃም እንግዳ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞው ወጣት የጎጃም ወጣት ሽማግሌ በነቂስ ወጥቶ በክብር የተቀበለበት ሚስጥሩ ለመሰጠረው ግዙፍ ነው። ለእኔ ኢትዮጵያዊው ኦሮሞና አማራው ለአመታት በክፉዎች ከጫፍ እስከ ጫፍ የተረጨበትን የመለያየት መርዝ ስለማክሸፉ ምልክት ነው።

በህዝቦች መካከል ያለው፣ የቆየ የመደጋገፍ መንፈስ ይታይ ዘንድ ከጣናው የእንቦጭ አረም ከፍ ባለ ደረጃ ዛሬ ታይቷል። ክፉዎች ተስፋ ይቆርጡ ዘንድ ኢትዮጵያዊው ኦሮሞ “ጣና ኬኛ” ዘመቻ እያለ ጎጃም ሲገባ ህዝቡ በክፉ በደጉ እንደማይለያይና ህብረትና አንድነቱን ናፋቂ መሆኑን ማሳያ ሆኖናል። በእርግጥም በጣም ጥቂት ወጣቶች በአሸናፊነት መንፈስ ከኦሮሚያ ተመው ጎጃም ሲገቡ የጎጃም ሕዝብ በአንጻሩ መልዕክቱ ደርሶታል። ጎጃሜው ታጥቆ አሸርግዶ የኦሮሞ ወጣት ወንድም እህቱን  በክብር በባህላዊ እስክታ፣ ሆታ ጭፈራ ተቀብሏል። የአቀባበሉ መንፈስ ደግሞ የኢትዮጵያውያን አንድነት፣ የኢትዮጵያውያን የህብረት አብሮነት ፍላጎት ማሳያ ግልጽ መልዕክት ይመስለኛል።

ይህ የአብሮነት መንፈስ ደግሞ እነሆ የኢትዮጵያን ትንሳኤ መልክት ነው። ተስፋችን በሚሰራው ስራ ብን ብሎ ሲጠፋ “ኢትዮጵያ እንደሁ አትጠፋም!” የምንለውን አራቂ መንፈስ አስታውሶ ኢትዮጵያ በልጆቿ ህብረት እንደማትጠፋ በእውን ያሳየን መልዕክት ነው! የኦሮሞ ወጣቶች በጎ መንፈስና የጎጃም አማራው የአቀባበል ደስታ ፌሽታ ስነስርአትን ላስተዋለው የኢትዮጵያዊነት የህብረት አንድነቱን መንፈስ እንመሰክር ዘንድ ያስገድደናል። ይህ ግዙፍ መንፈስ ጣናን ከወረረውን እንቦጭ በላይ ስለ ከበበን ስለወረረን በጎ ተስፋ ሰጭ መንፈስ ይናገራል! ለአመታት ያንዣበብንን የመለያየት የመፈራረስ አደጋ ዛሬ በ200 በጎ አድራጊ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ ወጣቶች የከሸፈን ያህል ተደስተናል። ብቻ “በጣና ኬኛ” ድንቅ ዘመቻ ነፍሴ ከፍ ያለ ደስታን አግኝታለች!

“ኢትዮጵያ ኬኛ፣  ጣና ኬኛ …!” ድንቅ መንፈስ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ነቢዩ ሲራክ

ጥቅምት 3 ቀን 2010 ዓም

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    October 14, 2017 06:19 am at 6:19 am

    ሆ ብሎ ገባ ! አረም ቢወረው
    ያን ፌሶ ጥሊያን እንዲህ የነቀለው
    የአባቱን ጅብዱ በልጁ ዘመን የደገመው
    ልዩነህ ሲሉት አንድ ነን አለ መጣ እያገሳ
    የኢትዮጵያ ልጆች ይኽው ገጠሙ መሳ ለመሳ
    ጭፈራው ባሕል ቋንቋቸው ሀገር
    እምነታቸው ጽኑ ዓለም ምሥክር
    ወያኔ እና አረም አንድ እንቦጭ
    እንቦጭ ውሃ ህወሓት ደም መጣጭ
    ንቀል ጣል አለ መብቱን አወቀ ጣና ኬኛ
    ጨዋታው ደራ ውሉ ታወቀ ኢትዮጵያ ኬኛ!
    ፍቅር ሠላም ኅብረት ይበጀናል ለእኛ ።
    ***************
    ሥለሀገራቸው ደህንነት የሕዝብ አብሮ መኖር ቅን ያሰቡ ቀናው ይግጠማቸው!
    ከሸረኛ ምቀኛ ከፋፋይ አመጸኛ ተንኮለኛ ይሰውራቸው
    በቸር ይክረሙ።

    Reply
  2. Lemma says

    October 14, 2017 06:50 pm at 6:50 pm

    Endih yale Tiru melikt beergata metsaf neberebet.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    October 14, 2017 10:24 pm at 10:24 pm

    ጣና! ጣና!! አረ ጣና!!
    ያባይ ውልድ ያማራ ምንጭ ስብዕና
    በዕምቦጭ ተወረረ ይሉናል?? ወይ ፈተና!!!!
    ከሞኝ ሰፈር
    ይቆረጣል ሞፈር!!
    ወጣቱን ለቮሊንተር
    ብታሰልፈው ጥሩ ነበር
    ልብህ ባይቃዥ በሌላው አፈር!!
    ምንም ነውር የለውም መማማር!!!!!

    Reply

Leave a Reply to በለው! Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule