አመጹ ከካምፕ ወደ ካምፕ እየተዛመተ ነው በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን ተመዝግበው በትግራይ-ኤርትራ ድንበር ዳርቻ በስደት ማቆያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ የኤርትራ ተወላጅ ስደተኞችና በኢህአዴግ መካከል የተፈተረው አለመግባባት ተካሯል። የሰው ህይወት ማለፉና ነጻ እንቅስቃሴ መከልከሉ ተሰምቷል፤ እስካሁን ስድስት ሞተዋል፤ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ በርካታዎች ቆስለዋል። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውና በአውሮፓ ተቀምጠው ጉዳዩን የሚከታተሉ የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት ኦክቶበር 5 ቀን 2013 ምሽት ላይ በትግራይ ማይ ዓይኒ ወረዳ በሚገኝ የስደተኞች ካምፕ የተቀሰቀሰው ረብሻና ተቃውሞ ወደ ሌሎች ካምፖችም ተዛምቷል። በተለይም በትላንትናው እለት ሽሬ አካባቢ በሚገኘው አድ ሃሪሽ ካምፕ የተነሳው ተቃውሞ ጋብ ሊል የቻለው ኢህአዴግ ሃይል በመጠቀሙ እንደሆነ ተመልክቷል። በዚህም የሃይል ርምጃ … [Read more...] about በትግራይ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ ዓመጽ ተካሯል
Archives for October 2013
መንገድ ወድቆ አየሁት
ርሃብ፣ ድካም እና ሰቆቃው ለላፉት 12 ወራት ተፈራርቀውበታል። አንዴ በሰሃራ በረሃ ሌላ ግዜ ደግሞ በሜዲትራንያን ባህር የሰው አእምሮ ሊቀበለው የማይችል ስቃይ አልፎ እግሩ አውሮፓን ምድር ከረገጠ እነሆ አንድ ሌሊት አለፈ። ሰነድ ገብረጻድቅ ይባላል። ፊቱ እጅግ ተጎሳቅሏል። ከሰውነቱ ላይ አጥንቶቹ ይቆጠራሉ። ወጣቱ ተስፋ ወዳደረገባት የአውሮፓ ምድር ለመግባት የተነሳው ከአመት በፊት ነው። እንብርቱ የተቀበረችበትን ሃገር ተሰናብቶ ከወጣ ጀምሮ የደረሰበት መከራ ይህ ነው አይባልም። ሰነድን እመንገድ ወድቆ ነበር ያገኘሁት። ለጥቂት ደቂቃ አነጋገርኩት። ንግግሩ የሚረብሽ ነው። አጭር የቪዲዮ ቆይታችንን ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ። ከ 300 በላይ የኢትዮጵያውያ እና የኤርትራ ተወላጆች የፈጀው የላምፔዱሳ እልቂት በአለም አቀፍ ዜና እየታወጀ ባለበት ሰዓት፤ ሌላ መርከብ ከሊቢያ ተነስታ … [Read more...] about መንገድ ወድቆ አየሁት
አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!
‹‹ ዲሞክራሲ የሚመሠረተው መንግስት ሕዝቡን ሊያገለግል የቆመ ነው በሚል መሠረት ሃሳብ ላይ ነው፡፡ ይህም ማለት ሕዝብ መንግሥትን ለማገልገል የተፈጠረ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር ህዝብ የአንድ ዲሞክራሳዊ አገር ዜጋ እንጂ ተገዥ አይደለም፡፡ መንግስት የህዝብን መብት በሚያስጠብቅበት ወቅት ህዝብ ደግሞ በልዋጩ ለመንግስት ታማኝነቱን ይገልፃል፤በጨቋኝ ሥርዓት ግን መንግስት ራሱን ከህዝብ በማግለል ታማኝነትን ከህዝብ ይሻል ፤መንግስት ውሳኔ የሚወስነው ተገቢውን የህዝብ ድጋፍና ተሳትፎ ሳያገኝ ከሆነ የህዝብ ታማኝነት መመኘት ከንቱ ቅዠት ይሆናል፡፡ ›› (what is democracy) ከሚለው መፃፍ የተወሰደ ነው፡፡ ጥላቻ ሁለተኛ ከባዱ የሰው ልጅ ስሜት ነው፤ፍቅር የመጀመሪያ ነው፡፡ ጥላቻ በፍራቻ በእውቀት ማነስና በተጠራጣሪነት የሚመጣ ነው፡፡ ጥላቻ ይቅር ባይነትና መግባባትን ያሣጣል፡፡ … [Read more...] about አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!
የምርትና የሕዝብ እድገት እሽቅድድም
እአአ በ1798 (ከሁለት መቶ አሥራ አምስት ዓመታት በፊት) መምሬ ቶማስ ሮበርት ማልቱስ የሚባል የ32 ዓመት የብሪታንያ ቄስ የዘመኑን የነገረ ንዋይ አስተሳሰብ የለወጠ አዲስ ሀሳብን የያዘ መጽሐፍ አሳተመ፤ ሀሳቡ በጣም ግልጽ ነበረ፤ የሰው ልጆች ቁጥር እድገት መጠኑ እያጠፈ የሚሄድ ነው፤ የሕዝብ ቁጥር 1፣ 2፣ 4፣ 8፣ 16፣ 32፣ 64፣ 128፣ እያለ የሚጨምር ነው፤ ከእርሻ የሚገኘው ምርት ደግሞ የእድገቱ መጠን አያጥፍም፤ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8፣ 9፣ 10፣ እያለ የሚሄድ ነው፤ የመምሬ ማልቱስን ሀሳብ በሌላ መንገድ ካየነው የበላተኞች ቁጥር እያጠፈ ሲያድግ የምግቡ አቅርቦት የሚያድገው ግን በጣም በዝግተኛ ፍጥነት ነው፤ የሚል ነው፤ እንግዲህ የሕዝብ ቁጥርና የምርት አቅርቦት እኩል መጓዝ ሲገባቸው የሕዝቡ ቁጥር እየቀደመ ስለሚገኝ፣ መምሬ ማልቱስ የደረሰበት … [Read more...] about የምርትና የሕዝብ እድገት እሽቅድድም
መሬት የማን ነው?
አገር ማለት በአባቶች፣ በአያቶችና በቅድማያቶች አጥንትና ደም ተገንብቶ የታጠረ መሬት ነው፤ የዶር. በድሉ ዋቅጅራን ዋይታ እየኮረኮረ የሚያወጣውና የሚያስተጋባው የፍቅር ስሜት ምንጭ ነው። የተከሰከሰውና ተፈረካክሶ አፈር የሆነው አጥንትና የወረደው የአያቶችና የቅድማያቶች ደም እየፈሰሰ መሬቱ ላይ በሚገኙ ወንዞች ውስጥ ሁሉ ገብቶአል፤ እንዲያውም እነዚህ ወንዞች ወስደው በቀይ ባሕር፣ በሜዲቴራንያን ባሕርና በሕንድ ውቅያኖስ ጨምረውታል፤ ይህ በአጥንትና በደም የታጠረ መሬት የማን ነው? በመሬቱ ላይ የባለቤትነት መብትን ለማስከበር ከውጭ ኃይሎች ጋር የተጋደሉት ጥንታውያን ነፍጠኞች ቅድሚያን የሚያገኙ ይመስለኛል፤ እነዚህ ጥንታውያን ነፍጠኞች ብቻቸውን አልነበሩም፤ ለምግብ የሚሆናቸውን ሁሉ የሚያመርቱ ገበሬዎች ነበሩ፤ ለልብስ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ የሚፈትሉና የሚሸምኑ ባለሙያዎች ነበሩ፤ … [Read more...] about መሬት የማን ነው?
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ጋዜጣዊ መግለጫቸው
ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ከአካላዊ እንቅስቃሴያቸው እና ድምፀታቸው ጀምሮ እስከ ሚቀልዷቸው ቀልዶች እና የሚያስተላልፏቸው መልዕክቶች በሙሉ የቀድሞውን ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሚያስታውስ መልኩ ያካሄዱት ጋዜጣዊ መግለጫ ባብዛኛው ተቃርኖ የበዛበት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ከጥያቄ እና መልሱ አስቀድመው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መንግስት ያለውን መረጃ የተናገሩ ሲሆን እንዲሁ በደፈናው አሃዝ ሳይጠቅሱ የሃገሪቱ ምጣኔሃብት እያደገ መሆኑን፤ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፉ ካለፈው አመት የተሻለ መሆኑን እና በሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከጎረቤት ሃገራት ጋር ኢትዮጵያ ያላትን ግንኙነት ለማብራራት ሞክረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከኤርትራ በስተቀር ከሌሎች ጎረቤት ሃገራት ጋር ያላት ግንኙነት ስትራቴጂካዊ መሆኑን ጠቅሰው፤ … [Read more...] about ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ጋዜጣዊ መግለጫቸው
በታሪክ ውስጥ የሚሰሩ ስትራቴጂያዊ ስህተቶች
አምስተርዳምጉባዔላይለጥናትየቀረበጽሁፍ! 1.0 መግቢያ የታሪክ ግዴታ ሆኖ የሰው ልጅ እንደማህበረሰብ ከተደራጀና፣ ስልጣንና ሀብት በጥቂት ሰዎች ቁጥጥር ስር መውደቅ ከጀመረ ወዲህ የአንድ ህዝብ ዕድልና የወደፊት ጉዞው፣ ታሪክ የመስራትና ያለመስራት ችሎታው በመጀመሪያ ደረጃ ሊወሰን የሚችለው ስልጣንን በቁጥጥራቸው ውስጥ ባስቀመጡ ጥቂት ሰዎች አማካይነት ነው። በታሪክ ውስጥ አንድ ህዝብ ከአንድ አገዛዝ ቁጥጥር ውጭ በሆነ መንገድ የራሱን ህይወት በነፃ ያደራጀበትና ታሪክ የሰራበት በተለይም ቀደም ብለው በነበሩ ስርዓቶች ውስጥ አልነበረም። እንደሚታወቀው የአንድ አገዛዝ ምንነት የሚታወቀው ታሪክ ለመስራት ባለው ችሎታና አገርን ጥበባዊ በሆነ መልክ በማስተዳደር ረገድ ነው። አንድ አገዛዝ ታሪክን እንዲሰራ ከፈለገ ደግሞ ንቃተ-ህሊናው በጣም ወሳኝ ነው። በታሪክ ውስጥ በአንድ ማህበረሰብ … [Read more...] about በታሪክ ውስጥ የሚሰሩ ስትራቴጂያዊ ስህተቶች
ኢትዮጵያን እንደገና ማነጽ
መግቢያ የዛሬው የመወያያ ሃሳብ ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ ኣዲስ የማህበራዊ ፖለቲካ መዋቅር በማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው። ይህ መዋቅር ኢትዮጵያን ወደ ኣዲስ ኪዳን የሚጋብዝ ነው። ኢትዮጵያ የገጠማት የከፋ ችግር በኣብዛኛው ከታችኛው የማህበራዊ ፖለቲካ (socio politics) መዋቅር ጋር የተገናኘ በመሆኑ በዚህ ላይ ኣማራጭ ሃሳብ ማምጣት በተለይ ይህ የኣሁኑ ትውልድ የሚጠበቅበት ይመስላል። ያለፉትን ችግሮች ኣስር ጊዜ እያወጣን ብናወርዳቸው ድካም ብቻ ይሆንብናልና። በተለምዶ ያ ትውልድ እያልን የምንጠራው ቀዳሚው ትውልድ ኣንድ የሆነ ሼል ሰብሮ የወጣ ነበር። ያ ትውልድ ለዘመናት የነበረውን ዘውዳዊ ኣገዛዝ ደፍሮ የጠየቀ፣ የፍትህና የእኩልነትን ጥያቄዎች ኣንግቦ ግንባሩን ለጥይት የሰጠ በመሆኑ ታሪክ ሁልጊዜም ያ ትውልድ..........እያለ ሲያስታውሰው እንዲሁ ይኖራል። (ሙሉውን … [Read more...] about ኢትዮጵያን እንደገና ማነጽ
ተስፋዬ ገ/አብ እንደ “ካቡጋ”
በጋዜጠኛነት ስም መድረክ በማበጀት በኢትዮጵያዊያን ሚዲያ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና ህዝቧ እርስ በርስ እንዲባላ ተልዕኮውን ሲያስፈጽም የነበረው ተስፋዬ ገብረ አብ በሰነድ የተረጋገጠ ማንነቱ ገሃድ ሆነ። ዜናውን የሰሙ እንዳሉት ተስፋዬ ካሁን በሁዋላ "በቁሙ ሞተ" ነው የሚባለው ሲሉ ተደምጠዋል። በኢትዮጵያ የኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት ይሰሩ እንደነበር የገለጹ የጎልጉል መረጃ ሰጪ "ተስፋዬ አስቀድሞም ቢሆን ሆን ብሎ በተቀነባበረ ስልት ጦርነቱ ሊጠናቀቅ ሲል ወታደር እንዲሆን የተደረገ የሻዕቢያ ሰላይ እንደነበር ይታወቃል" በማለት ለጎልጉል ተናግረዋል። "ተስፋዬ አሁንም በደም ከሚገናኛቸው የህወሃት ሰዎችና የደህንነት የላይኛው መረብ ጋር ግንኙነት አለው" ያሉት እኚሁ ሰው አጋጣሚው “በወያኔ ላይ ጠጠር የሚጥል ሁሉ …” በሚል ጭፍን አመለካከት በጅምላ ለምንነዳ ወገኖች ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ … [Read more...] about ተስፋዬ ገ/አብ እንደ “ካቡጋ”
ድሆችን ያፈናቀለው “ኢንቨስትመንት” ዕዳ ዋጠው
"መሬታችንን ለምን እንነጠቃለን?” በማለት የጠየቁ ተገድለዋል። ተገርፈዋል። ታስረዋል። አሁን ድረስ እስር ላይ የሚገኙ አሉ። ባዕድ እንኳን ባልሞከረው የከፋ ጭካኔ በከባድ መሳሪያ በተደገፈ የጦር ሃይል የተወለዱበትን መሬት እንዲለቁ የተገደዱ አዛውንቶች ላይ የተፈጸመው ግፍ እስከ ወዲያኛው የሚያሽር አይደለም። በሌሊት እርቃናቸውን ከሚያርፉበት ታዛ ስር ነፍጠኛ ሰራዊት እንዲከባቸው እየተደረገ የተፈጸመው አስነዋሪ ግፍ ጊዜ የሚጠብቅ እንደሆነ በየጊዜው የሚገለጽ ነው። “የዘራሁትን ሳላነሳ በዶዘር ማሳዬን ጠረጉት፣ በዶዘር እርሻዬ ውስጥ ገብተው አረሱት፣ መሬቴን ለምን ትወስዳላችሁ? የት ልትወስዱኝ ነው? ያሸተውን በቆሎዬን መነጠሩት። ምን ላደርግ እችላለሁ። መሳሪያ የያዙ ወታደሮች ከበውኛል፣ ጠዋት ስነሳ ማሳዬ ባዶ ሆኖ አገኘሁት … " ይህ ሁሉ የበደል ሰቆቃ ነው። በምስል ተደግፎ የቀረበ … [Read more...] about ድሆችን ያፈናቀለው “ኢንቨስትመንት” ዕዳ ዋጠው