• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ጋዜጣዊ መግለጫቸው

October 6, 2013 09:48 am by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ከአካላዊ እንቅስቃሴያቸው እና ድምፀታቸው ጀምሮ እስከ ሚቀልዷቸው ቀልዶች እና የሚያስተላልፏቸው መልዕክቶች በሙሉ የቀድሞውን ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሚያስታውስ መልኩ ያካሄዱት ጋዜጣዊ መግለጫ ባብዛኛው ተቃርኖ የበዛበት ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ከጥያቄ እና መልሱ አስቀድመው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መንግስት ያለውን መረጃ የተናገሩ ሲሆን እንዲሁ በደፈናው አሃዝ ሳይጠቅሱ የሃገሪቱ ምጣኔሃብት እያደገ መሆኑን፤ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፉ ካለፈው አመት የተሻለ መሆኑን እና በሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከጎረቤት ሃገራት ጋር ኢትዮጵያ ያላትን ግንኙነት ለማብራራት ሞክረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከኤርትራ በስተቀር ከሌሎች ጎረቤት ሃገራት ጋር ያላት ግንኙነት ስትራቴጂካዊ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይ የኢትዮጵያ መንግስት ከሶማሊያ መንግስት ጋር ያለውን ግንኙነት ዘርዝረዋል፡፡

እንደ እርሳቸው አገላለጽ የኢትዮጵያ መንግስት የሶማሊያ የፌዴራል መንግስት ከሃገሩ የክልል አስተዳደሮች ጋር ተስማምቶ እንዲሰራ ኢትዮጵያ የማደራደር ሚና እየተጫወተች እንደሆነ እና አልሸባብ የተባለውን አሸባሪ ሃይል ለማጥፋት በሶማሊያ ከሰፈረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ጦር ጋር በመተባበር ጥረት በማድግ ላይ ናት በማለት ሃገሪቱ በሶማሊያ ያላትን ዘርፈብዙ ጣልቃገብነት በሚያሳብቅ መልኩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ሃይለማሪያም እንዳሉት በኢትዮጵያ ብሎም ባጠቃላዩ ምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የደህንነት ችግር አለ፤ ነገርግን የእርሳቸው አስተዳደር በሶማሊያ የሚያደርገው ጣልቃ ገብነት ለድህንነት ችግሩ መባባስ አንዱ ምክንያት እንደሆነ ማመን የፈለጉ አይመስልም፡፡

ኤርትራን በተመለከተ በተለይ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቄ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል የመግዛት እቅድ አለን ማለታቸውን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ የኢትዮጵያ መንግስት ከዘጠኝ ዓመት በፊት ጀምሮ በሁለቱ ሃገራት መካከል ሰላም እንዲፈጠር ጽኑ አቋም እንደ ያዘ እና ጥረት እያደረገ ነው ያሉ ሲሆን፤ በኤርትራ በኩል ግን ይህ ዝግጁነት የለም ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ መብራት ከኢትዮጵያ እንገዛለን ማለታቸውን አስመልክቶ የራሳቸው ብቻ ፍላጎት ነው ያሉ ሲሆን፣ ምናልባትም አጣብቂኝ ውስጥ ስለሚገኝ ኑዛዜ ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ መንግስት ጋር ሰላም መፍጠር ይፈልጋል ብለው በተናገሩበት አንደበታቸው ጠቅላሚኒስትሩ የኤርትራ መንግስት ለራሱ ሳይሆን ሌሎችን ለመርዳት እየጣረ ይገኛል በሚል ለራሷ ክንፏ ተሰብሮ ሌላ ለመደገፍ እንደምትሄድ አሞራ መስለውታል፡፡

ሃገር ቤት ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች የሚያካሂዱትን የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተም ለቀረበላቸው ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስላቅ የተቀላቀለበት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ እንደ ሃይለማሪያም ንግግር ሃገር ውስጥ የሚገኙ የተቃዋሚ ሃይሎች በየሳምቱ በሚያደርጓቸው ሰላማዊ ሰልፎች ተደጋጋሚ ጥያቄ ነው የሚያነሱት፡፡  እርሳቸው እንዳሉ ለጥያቄዎቹ መንግስት ቀደም ብሎ መልስ የሰጠባቸው ስለሆነ ተጨማሪ ከመንግስት የሚመጣ ነገር የለም፡፡

ሰልፎቹ በዚህ ሁኔታ የሚቀጥሉ ከሆነም የሆነ ግዜ መንግስት ሊያስቆመው እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሃገርቤት ተቃዋሚዎች የሚያሰሟቸው ጥያቄዎች የራሳቸው እንዳልሆኑ እና እንደ እርሳቸው አባባል በተለያዩ ሃገሮች ያሉ ሌሎች ሃይሎች የሰጧቸው የቤት ስራዎች ናቸው፡፡

በዚህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር፤ ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ እና አንድነት ፓርቲ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞች እንዲፈቱ፣ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንዳይገባ፣ የኑሮ ውድነት የመሳሰሉት ጉዳዮች እንዲሻሻሉ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች መልስ አያገኙም ማለት ነው፡፡

በውጭ ካሉ የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ በተመለከተ ግንቦት ሰባት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ባጭሩ ህልም ነው፤ ማለም ይችላሉ ያሉ ሲሆን በፓርቲያቸው ውስጥ መሰንጠቅ ስለመኖሩም ለተነሳው ጥያቄ ምኞት ነው መመኘት ትችላላችሁ የሚል ድፍን ያለ መልስ ሰጥተዋል፡፡

ሌላው በተቃርኖ የታጀበው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ሙስና እና ኢንቨስትመንትን በተመለከተ የቀረበላቸው ሲሆን መንግስታቸው የሙስና ቀዳዳን እያጠፋ ተወዳዳሪነት የሰፈነበት አንቨስትመንት እንዲኖር ያበረታታል ብለው የተናገሩ ሲሆን፡፡

ሙስና ውስጥ የገቡ ባለሃብቶችን መንግስት እየተከታተለ እንደሆነ እና ሙስና ጋር ያልተነካኩ ባለሃብቶች ይህ ሊያሰጋቸው እንደማይገባ የገለፁ ቢሆንም በመቀጠል ደግሞ እስካሁን ስርቆት የፈፀሙ ባለሃብቶች ካሁን በኋላ ቢያቆሙ ጥሩ ነው በማለት ከዚህ ቀደም ለተፈጸሙ ዝርፊያዎች እውቅና ሰጥተዋል፡፡

እንዲሁም የቁጠባ ቤቶችን በተመለከተ የወጣው መመሪያ የቁጠባ ቤት ተመዝጋቢዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ ነው መቆጠብ የሚችሉት መባሉ የሌሎች የግል ባንኮችን ተወዳዳሪነት ይቀንሳል መባሉ የተሳሳተ ትንተና የተካሄደበት ትችት ነው ያሉ ሲሆን ባንኩ ሰዎች ከሚቆጥቡት 20 በመቶ ገንዘብ ላይ 80 በመቶ ጨምሮ ስለሚያበድራቸው  ተጎጂ እንደሆነ ለማብራራት ሙከራ አድርገዋል፡፡

ነገርግን በዚህ መልሳቸው ባንኩ 80 በመቶ ብድር ሲሰጥ ጎን ለጎን በብቸኝነት ኢንቨስትመንት እያካሄደ ስለመሆኑ የሰጠውን ብድር መልሶ ከወለድ ጋር እንደሚያገኘው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘነጉት ይመስላል፡፡

በመሰረተ ልማት ላይ ስለሚገኙ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለተጠየቁት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ከፖለቲካዊ ችሎታቸው ይልቅ የምህንድስና ሙያ እውቀታቸውን ተጠቅመው ለማብራራት ሙከራ ያደረጉ ሲሆን እዚህም ላይ ግራ አጋቢ መልሶች እና ማብራሪያዎች ሰጥተዋል፡፡

የተፋሰስ ችግር በመኖሩ የአስፋልት መንገዶችን እያበላሻቸው መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀድሞ ነገር መንገዶቹ ሲሰሩ ተፋሰሱንም አብሮ መስራት ለምን እንዳልተቻለ አልጠቆሙም፡፡

በተመሳሳይ መልኩ የመብራት ችግር በተለይ በመኖሪያ አካባቢዎች መብራት የሚቋረጠው አዳዲስ ማሽን ቤቶች በብዛት ስለሚከፈቱ እና በየአካባቢው ያሉ ማከፋፋያዎች ለእነዚህ የሚሆን ሃይል የመሸከም አቅም ስለሌላቸው ነው በሚል ቴክኒካል መልስ የሰጡ ሲሆን እንደ ቃሊት አካባቢ ለሚገኙ የኢንዱስትሪ አካባቢ የሚባሉ አካባቢዎችም ችግሩ ተመሳሳይ እንደሆነ ነው ያብራሩት፡፡

የሞባይል ኔትዎርክ መጣበብ ችግርም ተጠቃሚ ከታቀደው በላይ ስለበዛ ነው ያሉ ሲሆን ይህ የእቅድ እና ነባራዊ ሁኔታ አለመጣጣም እንዲሁም በተደጋጋሚ የሚያነሱት የአፈጻፀም ችግር በቀድሞውም ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሰጥ የነበረ ሲሆን ይህ የማቀድ እና የማስፈጸም ችግር ከመንግስት ብቃት ማነስ ጋር ስለመያያዙ ማንሳት የፈለጉ አይመስሉም፡፡

ባጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ  አስተዳደራቸውን ምዕሉ በኩለሄ አይነት አድርገው የሳሉት ሲሆን ለተፈጠሩ ችግሮች ሁሉ ሰበብ አስባብ ከመደርደር የዘለለ መልስ አልሰጡም፡፡

ከአጠቃላይ መግለጫው ግን አንድ ነገር በእርግጠኝነት እንድንገነዘብ አድርገውናል፤ ኢህአዴግ ሌላው ቢቀር የአቀራረብ ለውጥ እንኳ እንደማይኖረው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule